April 1, 2019
8 mins read

መጪው የኢትዮጵያ አገር አቀፍ እና የወረዳ ምክር ቤት ምርጫ ማስተላለፍ እና የሽግግር መንግስት ማቋቋም ሃሳብ ለማቅረብ

EPRDF Election1

Ghion/March 22, 2019 Ghion2008@gmail.com

አገራችን አሁን ያለችበት ወቅት አገር አቀፍ ሆነ የወረዳ ምክር ቤት ምርጫ ማካሄድ አገሪቱን ለከፋ አደጋ መጋበዝ ነው:: የሚቀጥለውን አገር አቀፍ ምርጫ እንዲተላለፍ በማድረግ የሽግግር መንግስት ማቋቋም መፍትሄ ሊሆን ይችላል የሚል እምነት አለኝ:: ምርጫው የሚተላለፍ ከሆነ ገዢው ፖርቲ ፖርላማውን መበተን እና የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት እና ስልጣን ለማጋራት ሥራ ቢጀምር::
እንደ አንድ የጨነቀው ኢትዮጵያዊ የሚከተለውን ሃሳብ ማቅረብ እወዳለው:: ይህ ሃሳብ ዳብሮ ለአገራችን አማራጭ መፍትሄ ከሆነ ከሚል እሳቤ የመነጨ ነው:: በተጨማሪ የውይይት ሃሳብ ሊሆን ይችላል የሚል እምነት አለኝ:: በተረፈ አገራችን በምርጫ ምክንያት ከሚመጣ የከፋ አደጋ ይጠብቃታል::

1. አንጋፋ ፖለቲከኞችን (ከ 60 አመት እድሜ በላይ የሆኑ) በክብር እንዲሸኙ ማድረግ:: አንጋፋ ፖለቲከኞች በገዛ ፈቃዳቸው ከፖለቲካ አመራርና አባልነት ጡረታ እንዲወጡ ማበረታታት:: • ከውጪ ወደ ሃገር የተመለሱ እና አገር ውስጥ ላሉ አንጋፋ ፖለቲከኞች (ከ 60 አመት እድሜ በላይ የሆኑ) ከፖለቲካ በገዛ ፈቃዳቸው ጡረታ ከወጡ o የአገራችን አቅም ባገናዘበ መልኩ መንግስት ጡረታ የሚጦሩበት ገቢ መስጠት o ቤት ለሌላቸው በሕይወት እስካሉ ድረስ የሚኖሩበት የመንግስት ቤት ወይም በስጦታ መልክ መኖሪያ መስጠት ቢቻል:: ይህንን መንገድ ለሚከተሉ ከ2-3 ወር ባለ ጊዜ ውስጥ ከፖለቲካ አመራር ለቀው ለመንግስት ማሳወቅ አለባቸው:: በዚህ ጊዜ ውስጥ ያላመለከተ ከእድሉ ተጠቃሚ አይሆንም::

2. የፖለቲካ ፓርቲዎችን በተመለከተ በየክልሉ ብዙ ደጋፊ ይኖራቸዋል ተብለው የሚታሰቡ ከ 2-3 ፓርቲዎች ለምሳሌ : • ትግራይ – 2 ፓርቲ (ሕወአት (TPLF), አረና (ARENA)) • አፋር – 2 ፓርቲ (የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ANDP), የአፋር አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር (ARDUF)) • አማራ – 2 ፓርቲ (የአማራ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ADP), አብን (NAMA))
• ኦሮሚያ – 3 ፓርቲ (የኦሮሞ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ODP), የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (OLF), ኦፌኮ (OFC)) • ሶማሌ – 2 ፓርቲ (የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ESPDP), ኦጋደን ብሔራዊ ነጽነት፡ ንባር (ONLF)) • ቤን ሻንጉል ጉሙዝ – 2 ፓርቲ (የቤንሻንጉልና ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲዊ አንድነት, 2nd Party) • ደቡብ (የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ, 2nd Party) • ጋምቤላ – 2 ፓርቲ (የጋምቤላ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ, 2nd Party) • ሐረር – 3 ፓርቲ (Harari People’s Democratic Party (HPDP), የኦሮሞ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ODP), የዜግነት ፖለቲካ ፖርቲ) • ድሬ ዳዋ – 3 ፓርቲ (የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ESPDP), የኦሮሞ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ODP), የዜግነት ፖለቲካ ፖርቲ)) • የዜግነት ፖለቲካ – 1 ፓርቲ (በምሥረታ ላይ) • አዲሳ አበባ – ሁሉም ፖርቲዎች

3. የወረዳ, የህዝብ ተወካዮችና ክልል ምክር ቤት ወንበር ድልድል
• የክልል እና ወረዳ ምክር ቤት መቀመጫ በክልሉ ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እኩል ወንበር:: እዲሁም የዜግነት ፖለቲካ ለሚያራምዱ 5% መቀመጫ መስጠት::
• ለፌድራል ህዝብ ተወካዬች በክልሉ ለሚንቀሳቀሱ ፖርቲዎች እኩል ወንበር:: ክልሉ ከ100 በላይ የፌድራል ወንበር ካለው የዜግነት ፖለቲካ ለሚያራምዱ 5% መቀመጫ መስጠት::
• አዲስ አበባን በተመለከተ የከተማውን ህዝብ ብሔር ስብጥር በሚመጥን መልኩ የከተማው ምክር ቤት, የፌድራል እና ወረዳ ምክር ቤትን ወንበር ማከፋፈል:: ለእያንዳንዱ ብሔር በክልላቸው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እኩል ማካፈል::

• ድሬ ዳዋ: 3 የፌድራል መቀመጫ አላት:: ለሶማሌ (ESPDP), ኦዴፓ እና የዜግነት ፖለቲካ ፖርቲ ማካፈል:: የከተማና ወረዳ ምክር ቤት ወንበር ለሶማሌ (ESPDP), ኦዴፓ እና የዜግነት ፖለቲካ ፖርቲ እኩል ማካፈል::
• ሐረር: 2 የፌድራል መቀመጫ አላት:: Harari People’s Democratic Party (HPDP) ኦዴፓ ማካፈል:: የከተማና ወረዳ ምክር ቤት ወንበር ለHPDP, ኦዴፓ እና የዜግነት ፖለቲካ ፖርቲ እኩል ማካፈል::
• ደቡብ ክልል: የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ በክልሉ ለሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝብ ብዛትን ያማከለ ተመጣጣኝ የክልል እና የፌድራል ምክር ቤት መቀመጫ እንዲሰጥ:: እዲሁም የዜግነት ፖለቲካ ለሚያራምዱ 5% መቀመጫ መስጠት::

4. መንግስትን ማን ይምራ የፌድራል ምክር ቤት አብላጫ ድምፅ ያገኘ ግንባር ወይም ጥምረት ምክር ቤቱ የሚጠይቀውን ወንበር መጠን ካሟላ ካቢኔ ማዋቀር ይችላል:: በተጨማሪ ይህ ግንባር ወይም ጥምረት የግድ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የአማራና ኦሮሞ ፖለቲካ ፓርቲ ሊኖሩት ይገባል:: የአማራና ኦሮሞ ፖለቲካ ፓርቲ የሌለው ግንባር ወይም ጥምረት መንግስት እንዲመሰርት መፈቀድ የለበትም:: መንግስትን የሚመራው ካቢኔ አወቃቀር የእያንዳንዱን የግንባሩን ወይም ጥምረት አባል ፓርቲ የፓርላማ መቀመጫ ቁጥርን ያማከለ ሊሆን ይገባል::

5. ፓርላማው አገሪቷ የተሟላ ዲሞክራሲያዊ ተቋም እንዲኖራት ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት በተቀመጠው ጊዜ መንግስት ፍኖተ ካርታውን መተግበሩን መቆጣጠር ከዋና ስራዎቹ አንዱ እንዲሆን::

6. የፌድራል ምክር ቤት፣ የከተማና ወረዳ ምክር ቤት የ5 አመት እድሜ እንዲኖረው ቢደረግ::

7. የአዲስ አበባ የስራ ቋንቋን በተመለከተ ከአማርኛ በተጨማሪ ኦሮሚኛ፣ ትግሪኛ እና ሶማሊኛ እንዲካተቱ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት::

አመሰግናለው Ghion2008

2 Comments

  1. ቀላል፣ ገራገርና የማይረባ ሃሳብ ነዉ።
    ጸሃፊዉ ግን ለድካሙ ልመሰገን ይገባል።

  2. i like it but i don’t agree harer and dridewa b/c meles new le oromo ena sumalie yakafelachew evnji ketema asetedadere ketebalechi lehulum like addis abeba mehon new yalebat yemitekimatim endeza sitihon new yemitadeg lielaw oromiya kilel yalew hulum amhara and guragie tegerie mekoter ena mewokel alebet betami bizu hizeb new oro sayehon oro teblo yetkoter lielaw benshangul yalew amhara huulum mewokel alebet mikiniyatum kebenshangule hizib amhara yebeletal 75% hizibu amhara huno eyale wekilena yelewm yepoletica wekilena …….////deniberun endegena or kilelochi endegena bikelelu yeshallal esum wana angebegabi new DR abey yeserawn or yakuakuamewn komision tebeye anikebelim mikiniyatum ahunim egnan ayewokilum amhara yelebetim amhara yelielebetin serge ena milashi ayetenewal

Comments are closed.

Previous Story

ሱስ ጎርፍ መጣ ደሞ! – በላይነህ አባተ

Next Story

ቋንቋ ለብልሆች የመግባቢያ መሣሪያ፤ ለደናቁርት ግን ሕዝብ መከፋፈያ – በገ/ክርስቶስ ዓባይ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop