ፋሲል ከነማ ደጋፊዎች አሳፍሮ ከባህርዳር ወደ ጎንደር በማምራት ላይ ያለ አውቶብስ…

ፋሲል ከነማ ደጋፊዎች አሳፍሮ ከባህርዳር ወደ ጎንደር በማምራት ላይ ያለ አውቶብስ ተገልብጦ በሰው ህይወት እና አካል ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።

https://www.youtube.com/watch?v=pJpzsue5H3c&t=917s

የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ደጋፊዎቹ ትናንት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 12ኛ ሳምንት በባህርዳር ከተማ እና ፋሲል ከነማ መካከል ከተደረገው ጨዋታ በኃላ ወደ ጎንደር እየተመለሱ ጣራ ገዳም በሚባል አካባቢ ሲደርሱ ነው የመኪና አደጋው ያጋጠማቸው።

በአደጋውም የሁለት ደጋፊዎች ህይወት ሲያልፍ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ደጋፊዎች ላይም የተለያየ መጠን ያለው የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

በተሽከርካሪ አደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ደጋፊዎች በጎንደር ሆስፒታል እና በአዲስ ዘመን ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ መሆኑን የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ አስታውቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አትሌት ደራርቱ ቱሉ በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን አከባቢውን በመወከል የቦርድ አባል ሆና ተመረጠች
Share