ጁነዲን ሳዶ ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት ነው ተባለ

(ዘ-ሐበሻ) ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች ላይ በሰፊው እየተወራ የሚገኘው የአቶ ጁነዲን ሳዶ በወያኔ ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እየገለጹ ነው። እነዚህ ለአቶ ጁነዲን ቅርብ ነን ያሉ ወገኖች “የወሬው ምንጭ ሁሌም ሕዝብን በወሬ ማራበሽ የሚወደው የወያኔ መንግስት ነው” ይላሉ።
ወጣቱ የፖለቲካ ተንታኝ ጃዋር መሀመድ በፌስቡክ ገጹ “ጁነዲን ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት ነው” ሲል በተለይ በአያንቱ ድረገጽ ላይ የወጣውን ዜና አስተባብሏል። አያንቱ ድረ ገጽ Gurmessaa Beekamaa የተባሉ ሰው በፌስቡክ የለጠፉትን ዜና “ይህ ዜና ከነፃ ምንጮች አልተረጋገጠም” በሚል በማቅረብ ዜናው እንዲቀጣጠል ያደረገ ቢሆንም፤ ድረገጹ ከሰዓታት በኋላ ደግሞ ጁነዲን በሕይወት ስለመኖራቸውና ስላለመኖራቸው የተምታታ መረጃዎች እየደረሰን ነው በሚል ጉዳዩን እያጣራ እንደሚገኝና የዜናው ምንጭ ናቸው የተባሉት ግለሰብም ስለጁነዲን ተጨባጭ ማስረጃቸውን እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
የወያኔ ሚዲያ እንደሆነ የሚነገርለት ኢትዮቻናል የተባለውና በሃገር ቤት የሚታተመው ጋዜጣ ከዚህ ቀደም ጁነዲን ሳዶ ወደ ኬንያ ጠፍተዋል በሚል ሃሰተኛ ዜና ማሰራጨቱ የሚዘነጋ አይደለም ያሉት እነዚሁ የጁነዲንን ሞት የሚያስተባብሉ ወገኖች አሁንም ተገደሉ ብሎ የሚያወራው ራሱ ወያኔ፤ የሕዝቡን የአስተሳሰብ አቅጣጫ ለመቀየር ነው ይላሉ። በተለይ በነፃው ፕሬስ ላይ ለረዥም ዓመታት የሰሩ አንድ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት “የወያኔ መንግስት ሃሰተኛ ዜናዎችን በመፈብረክ ሚዲያዎች ተአማኒነት እንዲያጡ ለማድረግ ሲጥር ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በነፃ ጋዜጦች ስም የራሱን ጋዜጦች በማሳተም ሃሰተኛ ዜናዎችን እያቀረበ በራሱ ቴሌቭዥን ደግሞ ‘ነፃ ጋዜጠኛ የሚባሉት እንዲህ እያሉ የውሸት ዜና እየጻፉ ነው’ የሚል ፕሮፓጋንዳ በመሥራት ራሱ በከፈተው ነፃ ጋዜጣ ሌላውን ነፃ ጋዜጣ ሲያሰደብና ተአማኒነት እንዲያጡ በማድረግ ቆይቷል። አሁን ደግሞ እንዲህ ያለው ዜና፣ ባለፈው ዓመት መንግስቱ ኃይለማርያም በዙምባብዌ ሞቱ የሚሉት ዜናዎች በራሱ በወያኔ ተዘጋጅቶ በፌስቡክ የሚለጠፈው ፌስቡክ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ለውጥ እንደሚያመጡ ስለሚያውቅ መንግስት ሕዝቡ ፌስቡክ ላይ የሚጻፉ መረጃዎችን እንዳያምን ለማድረግ ነው የተዘጋጀ ድራማ ነው” ይላሉ።
የጁነዲን ሳዶ ባለቤት በወያኔ መንግስት ሽብርተኛ ተብለው የታሰሩ ሲሆን ይህን ተከትሎም ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል። ጁነዲን የሕወሓት ተለጣፊ ከሆነው ኦሕዴድ ጋር በሚሰሩበት ወቅት በአውስትራሊያ እና በሚኒሶታ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሟቸው እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኤርሚያስ አመልጋ በመጨረሻም "ለጊዜው" ተፈታ

9 Comments

  1. I do not care whether this guy is alive or dead!!!! he killed in one way or another his own oromo people. He is not an important man by any measurement. He was a puppet and mule of the Woyanes.

  2. who cares about the death of that stupid ex-TPLF’s slave. is he so important? at the end of the day all TPLF’s slaves will be eaten by the devile weyanes

  3. Oh guys, you lie yourself and you blame woyane; you kill yourself, you blame woyane. You blame woyane everything ? you are against yourself

  4. **ወጣቱ” የሜንጫ ፖለቲካ ተንታኝ” የኦሮሞ ሙስሊም ነጻ አውጭ የኢህአዴግ የውስጥ ሠርሳሪና ሚስጥር አቀባያችን አቶ ጁነዲን ሳዶ አልሞቱም ሲል አስታወቀ። አሃ! ወያኔ ውስጥህን አጥራ በለው !ያልነው ይህን ነበር። ይህ ትፋትን በዌአኔ እያሳበቡ ዙሪያውን ከበው ሜንጫ የሚስቡ ባንዳዎች በህዝብ ላይ አላቸውን የሽብር ብቻ ሳይሆን የመተላለቅ ኣላማ ለማሳካት በንጹሁ የኢትዮጵያ ሙስሊም የመብት ጥያቄ ላይ ሠርገው በመግባት ትግሉ አንዲከሽፍ ሕዝብ ሙስሊሙ በሀገሩ አሸባሪ አፍራሽ ጸረ ሕዝብ እንዲባል የነዙት የአክራሪነት ፉከራና ቅስቀሳ የግብፅን ዓይነት መተራመስና መተላለቅ ለመካሔድ ይጠቅማቸው ዘንድ…ከአሜሪካ እስከ ደቡብ አፍሪካ ያደረጉት አጥፍቶ መጥፋት ቅስቀሳ ኢትዮጵያ ቅኝ ገዢ ሀገር ናት የሚለው “የየጀዋሪያን”ስብከት (ጃዋራዊ ሀረካት) በቀላሉ የሚታለፍ አደለም ፡” ክርስቲያን ኦሮሞን አጥፍተው አማራንና አማርኛን ሠርዘው የሙስሊምን ቁጥር ከፍ ለማድረግ የኦሮሞ ሙስሊም ተገንጥሎ ፖለቲካውን ኢኮኖሚውን መከላከያውን ሲቆጣጠር የሃይማኖት ጥያቄ ይፈታል የሚለው ትንታኔና ኦሮሞ በአንድ ወቅት ፺ከመተ ህዝብ አልቆ ሴቶቹ ቱታቸው ተቆርጦ አሁን የኢትዮጵያን ከፍተኛውን የህዝብ ቁጥር ለመያዝና ሀገሪዩተን ግማሽ መሬት በወያኔ ለመያዝ በቃ!? አሁን ሀገር ማጥፋትና የመሸጥ ዓላማቸው በበይና በተመልካች መካከል ያለው አለመመጣጠን ወደ ሃይማኖት ተለውጦ ሲያጣላቸውና አንዱ ንጹሕ የሀገር አሳቢ ሌላው አሸባሪ አተራማሽ ገንጣይ እየተባባሉ የውሸት አርዕስት እየፈጠሩ ሕዝብ ያጫርሳሉ ጥቂቶች ባለሀብት ባለንብረት ሆነው አብዛኛው ገና ከልመና አልወጣም ግን በባዶ ሆዱ ያለመጫሚያ ሲያንዛርጥ ይውላል ያድራል ለመሆኑ ይህ ነጻ ወጣ የተባለው ብሔርና ገና ነጻ ትወጣለህ የሚባለው ሕዝብ የየት ሀገር ህዝብ ይሆን? አሁን ምጣዱ ግሏል የሚጥደው ማነው? በለው!

  5. KKKKKKKKKKKKKKK Mote, Kome men yanegagerale demo YEMUTA belo malef newenjie. wey Good sento besewe hager eytarede balebet seat sebelanasetaet yenore sew mote yewerale behoes enQwan.

Comments are closed.

Share