August 8, 2013
3 mins read

የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ቃለ ምልልስ ከጀርመን ድምጽ ራድዮ ጋር

[jwplayer mediaid=”6117″]

የጀርመን ድምጽ ራድዮ ጋዜጠኛ ሸዋዬ ለገሰ የዘ-ሐበሻ እና የጤና አዳም ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ ሔኖክ ዓለማየሁን አነጋግራዋለች። ቃለምልልሱ በጀርመን ድምጽ ራድዮ ላይ ተላልፏል። የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች እንድተከታተሉት እዚህ በማምጣት አካፍለናችኋል።

ስለጤና ጉዳይ የሚቀርቡ መረጃዎችን ምን ያህል ህዝብ እንደሚያገኛቸዉ፤ ወይም ለምን ያህል ህዝብ እንደሚደርሱ መገመት ይቸግራል። ነገር ግን አንድ ነገር ግልጽ ነዉ ሰዎች ለጤና ይዞታቸዉ ትኩረት መስጠትን ችላ ሊሉ አይገባም።
ጤና-ነክ ጉዳዮችን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ለማቅረብ መጣር የእኛን ኅብረተሰብ ሊነቃ ይችላል የሚል እምነት ያላቸዉ ወገኖች ራሱን የቻለ የጤና ድረገጽ ከፍተዉ መረጃዎችን ሲያሰራጩ ወራት ተቆጥረዋል።
ዘመኑ የቴክኒዎሎጂ ነዉ የመረጃ፤ በአንዱ ጓዳ የተከሰተዉን ሌላዉ ባለበት ሆኖ ሊሰማዉ መንገዱ ተመቻችቷል፤ ለብዙሃኑ። በዘመነ ኢንቴርኔት ምስጢር የለም፤ ራዲዮና ቴሌቪዥን ዜናዎችን አልተከታተልኩም፤ የጤና ጉዳይ መረጃዎችን እንደልቤ አላገኝም ከሚባልበት ጊዜ ልንሻገርም ዳርዳር እያልን ይመስላል። አፍሪቃ ዉስጥም ቢሆን ይህ ዛሬ ብዙም የሚወራለት የራቀና ያልተደረሰበት ጉዳይ አይደለም።

ዛሬ ይላል የጤና አዳም ድረገጽ አንቀሳቃሽ፣ ዛሬ ሰዎች ለራዲዮና ቴሌቪዥኑ ጊዜ ቢያጡ እንኳ ከያሉበት በእጅ ስልካቸዉ በየመንገዱም ቢሆን የሚሹትን መረጃ ማንበብ ይችላሉ። የተለያዩ ወቅታዊ ዜናዎችን ከመዘገብ በተጓዳኝ ሄኖክ ዓለማየሁ ለጤና ጉዳይም ትልቅ ትኩረት መስጠቱን የሚያንቀሳቅሰዉ ድረ ገጽ ዘሃበሻ ይናገራል። ለጤና መረጃዎችን የምታጋራዉን ድረገጽም እዚያዉ ላይ ታዝላ ነዉ ያስተዋልኳት። አዘጋጅዋ ለጤና ጉዳዮችን ትኩረት መስጠት ይገባል በሚል ለኢትዮጵያዉያን አንባቢዎቹ መረጃ በመስጠት ለማበረታታት ታስቦበት የተጀመረ መሆኑን ነዉ የሚናገዉ፤
ጋዜጠኛ ሄኖክ እንደሚለዉ ባላቸዉ መረጃ መሠረት በርካታ የድረገጹ ጎብኚዎች የሚገኙት እዚያዉ ሰሜን አሜሪካ ነዉ። ከኢትዮጵያስ ጎብኚዎች ይኖሩት ይሆን? ዝርዝሩን ከድምጽ ዘገባዉ ያድምጡ፤
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ

(ምንጭ፡ የጀርመን ድምጽ ራድዮ)

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop