ስለሺ ደምሴ እና ፈንድቃ የባህል ቡድን በሚኒሶታ የኢትዮጵያን ሙዚቃና ዳንስ አስተዋወቁ (ሙሉውን ቪድዮ ይዘናል)

/

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ The Cedar Cultural Center’s የ”African Summer series” በሚል የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራትን ሙዚቃዎችና ባህል ባሳየበት በዚህ የበጋው ወራት ዝግጅቶች ኢትዮጵያን በመወከል አርቲስት ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) እና ፈንድቃ የባህል ቡድን ረቡዕ ጁላይ 10 ቀን 2013 በተዘጋጀው ወርክሾፕ ላይ ዝግጅታቸውን በማቅረብ የሃገራቸውን ሙዚቃ፣ ዳንስ እና ባህል አስተዋውቀዋል።
በዚህ በርከት ያሉ የውጭ ሃገር እና ኢትዮጵያውያን ዜጎች በተገኙበት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) እና ፈንድቃ የአዝማሪ ባህል ቡድን በሚኒያፖሊስ የኢትዮጵያን ሙዚቃና ባህል በሚገርም መልኩ አቅርበው ከታዳሚው አድናቆትን አግኝተዋል። ጋሽ አበራ ሞላ በክራሩ አስቂኝ ግጥሞችን በመደርደር ህዝቡን ሲያዝናናው ያመሸ ሲሆን ፈንድቃዎች ደግሞ በውዝዋዜ፣ ትግርኛውን፣ አማርኛውን፣ ኦሮሚኛውን፣ ወላይትኛውን፣ ጉራጊኛውን እና ሌሎችንም ሲያስነኩት ነበር። ይህ 1:20 ደቂቃ ቪድዮን ዘ-ሐበሻ ቀርጻዋለች። ቪድዮውን ለእረፍት ቀንዎ ማየት ከፈለጉ ይኸው። ላላዩት ቢያሳዩት፤ በተለይም በውጭ ሃገር የሚያድጉ ህጻናትና ወጣቶች ቢያዩት መልካም ነው እንላለን። ወደ ቪድዮው፦

ተጨማሪ ያንብቡ:  በእምነት ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በአስቸኳይ ይቁሙ! - ኢሰመጉ

2 Comments

  1. Gashe abera mola and Fendikas, It is a wonderful show. You are the Ethiopian beautiful culture ambassaders. Shame to woyane who are working day and night to destroy Ethiopianism and failed badly.
    Ethiopia lezelalem bekiber tinurelen.
    Proud Ethiopian
    Jos

  2. IT IS A WONDERFUL PERFORMANCE EVER WHICH SHOWS THE REAL ETHIOPIAN TRADITION AND SO LEGENDARY I LOVE IT GOD BLESS YOU ALL

Comments are closed.

Share