ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ በጀርመን በርሊን ከተማ ተካሄደ

ዘጋቢ በየነ መስፍን ከጀርመን

እ.ኤ.አ በሜይ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጀርመን በርሊን ከተማ የኢትዮጵያውያን የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አባላት አንድነት ድርጅት (ኢ.ፕ.ኮ.) በጠራው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ-ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ፓርቲ /ኢሕአፓ/፣የሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት /ሞረሽ/ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አመራር እና አባላትም በሰልፉ ላይ ተገኝተዋል።

መነሻውን ”ቬንደርሸር ማርክት አንድ” /Werderscher Markt 1/ ከሚባለው የከተማው ክፍል በማድረግ በተለያዩ መፈክሮችና የኢትዮጵያ ባንድራ በማሸብረቅ ጉዞውን ወደ ቻንስለር አንጌላ ሜርክል ጽ/ቤት አድርጓል።
”በአማራ ህዝብ ላይ የሚደረገው የዘር ማጥራት ዘመቻ ይቁም!”
”የህሊና እስረኞች ይፈቱ!”
”የሃይማኖት ነፃነት ይከበር!”
”ከአባይ በፊት ዘረኝነት ይገደብ!”
”የጀርመን መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ለአፋኙ የወያኔ አገዛዝ የሚያደርጉትን የገንዘብ ድጋፍ ያቁሙ!”
”ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር!” የሚሉ መፈክሮች በሰፊው የተደመጡ ሲሆን ከአንድ ሰዓት ተኩል የእግር ጉዞ በኋላ ተሰላፊው በመጀመሪያ በጀርመን ፓርላማ /Bundestag/ ፊት ለፊት በኋላም በጀርመን ቻንስለር ጽ/ቤት ፊት ለፊት በመሰባሰብ የተለያዩ መፈክሮችን ያሰማ ሲሆን ከአንድ ወር በፊት በኢ.ፕ.ኮ. አማካኝነት በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን የዘር ማጥራት ወንጀል የሚቃወሙ ቁጥራቸው ከሶስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ጀርመናውያንን ፊርማ የያዘውን ሰነድ ለቻንስለሯ ጽ/ቤት ገቢ የተደረገ ሲሆን የኢ.ፕ.ኮ. ሊቀ መንበር፣እንዲሁም የኢሕአፓ ተወካይ፣የሞረሽ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ተወካዮች አጠር ያለ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ይህ ከሶስት ሰዓት በላይ የፈጀ የተቃውሞ ሰልፍ በሠላምና በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኦሮሙማው አጥፊ ዘረኛ ስትራቴጂን ቆሞ ማየት ወይስ ታግሎ ማስቆም!? - Hiber Radio

1 Comment

  1. this is the best article,I don’t mind to take my time to read such a pleasure news.

Comments are closed.

Share