አበራ ለማ፡ ለባሉ ግርማ፡ አስቦ ወይንስ ሌላ? (ከማተቤ መለሰ)

ከማተቤ መለሰ

 

አቶ አበራ ለማ፡ ሰሞኑን ”የማይጮኹት ባሉ ግርማን የበሉ ጅቦች” በሚል እርዕስ የጻፈውን በኢትዮ ሚዲያ ድህረ ገጽ ላይ ሳነብ” በአቆማዳው ገመሰኝ” ቢለው ተው ወንድሜ በውስጡ ዲንጋይ ይኖርበታል አለው የሚባለው ብሂል ነው። በሃሳቤ የመጣብኝ። እውነት ከ30 አመት በፊት አድራሻው ስለጠፋው ስለ ብርቅየው የብዕር ሰውና ንጹሁ ኢትዮጵያዊ ሰለ አቶ ባሉ ግርማ ተቆርቁሮ ያነሳው ሃሳብ ቢሆን በበኩሌ እሰየው ነበር።

 

ግን በእርግጠኝነት መታከኪያ ፈልጎ እንጅ ለባሉ ግርማ ተቆርቁሮ አይደለም። አበራ ለማ በተፈጥሮው የሚጨነቀው ለጥቅሙና ለጥቅሙ ብቻ እንጅ ለሰው እንዳልሆነ አሁን የምንኖረው አብረን አንድ አገር ማለትም ኖሮዌይ ስለሆነ በቅርበት የማውቀው በቤተሰቡ ላይ ሳይቀር የፈጸመውና የሚፈጽማቸው ዲርጊቶች ማረጋገጫዎች ናቸው። በአስነዋሬ ምግባሩም መንስኤ ነው በሚኖርበት ሃገር ከማህበረ ሰቡ ተገልሎ ያለው።

 

አበራ ለማ የግል ስብናውን ለመገንባት በጣረበት፡ በዚያ ዝባዝንኬ መጣጥፉ፡ የአለቃው አለቃ የነበሩትንና እውቁን ጋዜጠኛ ዛሬም ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት በብዕራቸው በመታገል ላይ ያሉትን። አቶ ሙሉጌታ ሉሌን የሚከስበት ጭብጥ፡ ሰለ ባሉ ግርማ ፕሬዘዳንት መንግስቱ ሃይለማርያም አናግረውታል የሚል ነው። አቶ ሙሉጌታ ተጠርተው ከሆነም በአንድ እርዕሰ ብሄር የነበራቸውን ክብር ማሳየቱ እንደተጠበቀ ሆኖ፡ ለአቶ ባሉ ግርማ መገደል ምክናያት ነው የሚለውን ነጥብ አላመላከተንም።

 

ከዚህም በላይ፡ አቶ ክፍሉ ታደሰ፡ ”በያ ትውልድ” መጻፋቸው እንደገለጹት አበራ ለማ ኢህአፓ ነህ በማለት የገደለውና በእነ እርገጤ መድበው የክስ መዝገብ ተራቁጥር 27 ላይ ስሙ ተጠቅሶ በሌለበት የተከሰሰበት ሟች ሰው አይደለምና ነውን? የሚለውን ጥያቄ ካነሳን፡ ዛሬ አበራ ለማ የሟች ወንድማችንን የአቶ ባሉ ግርማን አጽም መታከክ የፈለገበት ምክናያት ሰባዊነት ሳይሆን፡ ከወያኔ ጋር ያለው የጥቅም ግንኙነት መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ መስታዋት ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በሳዑዲ ውስጥ በወገኖቻችን ላይ የሚደረገውን ግፍ ለማስቋም በጋራ እንቁም

 

ሌላው አበራ ለማ በጽሁፉ፡ ባሉን የበሉ ጅቦች ሲል፡ ምን ለማለት ነው የሚለው ጥያቄም መታለፍ የሌለበት ነው። በእሱ ቤት ቅኔ መሆኑ ነው፡ ድንቄም ተቀኘች? እሱ በሁለተኛ ቋንቋው ሲቀኝ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ለሆኑት ጎጃሞች፡ አይገባቸውም ብሎ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ምክናያቱም ሰማቸውን በመደርደር የአንድ መንደር ሰዎች እያለ በፍጹም ጭፍን ጥላቻ የሚያብጠለጥላቸው፡ ትውልደ ጎጃሞችን ነው። ከጅብ ጋር ለማዛመድ የሞከረበት አንደምታም፡ በጅምላ አንድን ህዝብ እንደህዝብ ማዋረዱ ነው፡ በእሱ ቤት። ኢትዮጵያ ውስጥ ጌቶቹ የኦህዴድ ካድሬዎች አማረኛ ተናጋሬውን እየመረጡ በመግደል፣ በማሰርና በማፈናቀል፡ ከግፎች ሁሉ የከፋ ግፍ እየፈጸሙበት ነው። ሐገር ጥለን በመሰደድ እንኳን በሰላም እንዳንኖር፡ እንደ አበራ ለማ አይነት ሰዎች፡ በእየወሩ ሃገር ቤት በመመላለስ፡ ከአለቆቻቸው መመሬያ እየተቀበሉ፡ ተሰዶ ለወገኑ ነጻነት ከምር

2

የሚታገለውን ኢትዮጵያዊ በመዝለፍና በማሸማቀቅ ስራ ላይ ተጠምደዋል፡ በአበራ ለማ ያልተገራ ስድ አንደበት የሚዘለፉ አቶ ሙሉጌታ ሉሌ። ብቻ አይደሉም፡ ነጻነቴን እሻለሁ በማለት ወያኔን የሚቃወም ሁሉ እንጅ። ለዚህ ማስረጃው ኖረዌይ በሚኖሩ የነጻነት ታጋዮች ላይ በእየ ጊዜው የሚፈጽመው ድርጊት ነው።

 

ዛሬ 30 አመት በሗላ፡ በባሉ ግርማ ሰበብ፡ የተሳበው የጭዋታ ካርታም፡ ሰለ እውነት ለእሱ በመቆርቆር ሳይሆን። ወያኔ ከጀግኖች ሁሉ የላቀውን ጀግናና እውነተኛውን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ፡ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን፡ በማፈኑ፡ ከሃገር ቤት ጀምሮ በመላው ዓለም ተበትኖ የሚኖረው ኢትዮጵያውያን  በጋራ ለመታገል ያለውን ፍላጎት ማሳየቱ ወያኔን ያልተጠበቀ የብራ መብረቅ የወረደበት ታክል ስላስደነገጠው፡ መላ እንዲፈልጉ ካድሬዎቹን በማራወጥ ላይ ሲሆን፡ አበራ ለማም በድርሻው ይህንን የትግል ግለትና የአንድነት እንቅስቃሴ አቅጣጫ ያስቀይስልኛል ሲል ያሰበውን፡ ለጌቶቹ መታያ ይሆን ዘንድ ያቀረበው መሆኑን ልብ ልንልለት ይገባል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመተማው “የዘር-ፍጅት” ትርክት በደህንነት ተቋሙ የተቀናበረ ነበር (ዋዜማ ራዲዮ)

 

በተረፈ አገራችንን ጥለን ተሰደናል፡ በእያለንበት ደግሞ የምናገኛትን ዳቦ በሃገር ናፍቆት እንባ እያራስን እንዳንበላ፡ በእየ ሳምንቱ እየተመላለሱ ተጭነውት የሚመጡ መርዘቸውን  እየደፉበን ያሉ እንደ እነዚህ አይነት አስመሳይ ምንደኞች በእየቦታው እየፈሉ ነው፡፡ ጎበዝ ምን ይሻላል? ከዚህ በሗላ ጨረቃ ላይ አንወጣ፣ የት እንድረስ? አሞትን ኮስተር፣ ትንፋሽን ክትት አድርጎ ከምር ከመታገል በቀር።

 

ቸር እንሰንብት

 

ሃምሌ 6 ቀን 2006

 

 

 

 

 

 

 

13 Comments

  1. የአቶ አበራን ትህፉ ለምን አላየነዉም ወይም attached አላደርከዉም? እዉነተ ክሆነ አያይዘ አሳየን. አለበለዚያ ስለምን ዕንደምታወራ አለገባጝም.

  2. አቶ ማተቤ – ሰው የመሰለውን ነገር ከአጋጣሚ ጋር አሳፍቶ በለጣጠፈው ነገር እንዲህ የሚያስመርር ነገር ሊኖር አይገባም። ጨረቃ ስለውጡም ከሃበሻው አተካራ አይድኑም። ቴክስት እናረግለዋታለን! ሃሜት የተባለውን ጽሁፍ አንብቤዋለሁ። ለብስጭትና ቁጣ የሚያበቃ አይደለም። የባዕሉ ግርማ ሞት የጎዳው ሃገርን ነው። ልክ እንደዛሬው ለመኖር ሰውን ያዘው ጥለፈው የሚባልበት ጊዜ ስለነበር ለባዕሉ ግርማ ህልፈት ደርግ ቀዳሚው ተጠያቂ ቢሆንም ለሞቱ የሌሎች እጅ እንደነበረበት አመላካች ነገሮች አሉ። እርስዎም እንደ ጲላጦስ ከደሙ ንጽህ ነኝ ብለው እጅዎን አይታጠቡ። ሰለሌላው ሰውም አይከራከሩ።

  3. Thank you Ato Matebe. It was sickening to see such a man so bitter like Abera lema who is ordinary by any litrary standard to come out of his foxhole and throw blanket attack on individuals with no concrete evidence and try to hide behind truly famous names like bealu girma. He is also appearing to show his own form of ‘deformed’ racism that you can read between the lines. That is stinky charcater from a black man like him . I have to say he is neweregna. how come that this kind of person live with other people with any sense of decency without recieving some punch and how on earth did he take the courage to write at all while his mind is filled with utterlack of logic and is blind?The letter that bealu girma wrote to AAU about him was nothing special (bimaru anikawemeim) but that would not reduce the litrary giant that bealu was. he was also trying to imply that bealu hates the group that he hates. bealu is an indepndent person. he has his own intellectual yardstick and would not go so low as abera to throw a blanket hate on a certain ethnic group. Abera is gutter mind and bitter. But the way he was trying to imply scores of people as criminals as if he were not another opportunist hiding behind ordinary pen is astounding.

  4. አይ ማተቤ መለሰ አለህ እንዴ? በአርቲስት ዳምጠው አየለ የመሸኛ ፈንድሬዚንግ ላይ ልትሠራ የሞከርከውን አሳፋሪ ድርጊት ኖርዌይ ያለን ኢትዮጵያውያን የምንረሳው የመስልሃል? በፍጹም!!!!!! የዳምጠውን ዝግጅት በቅናት መንፈስ ተነሳስተህ ልትረብሽና ባቶ አበራም ላይ የመግደል ሙከራ ስታደርግ እጅ ከፍንጅ ተይዘህ ከዝግጅቱ ቦታ ተባረህ የነበርክ መናኛ ሰው አይደለህምን?ይህን አሳፋሪ ድርጊትህንም የኢትዮጵያ ኮሚኒቲና DCESON ተገቢውን እርምጃ ሊወስዱብህ አጀንዳ እንደተያዘብህ አናውቅምን? ፖሊስም በበኩሉ በሠራኸው በዚህ አሳፋሪ ወንጀል ምክንያት እወህኒ ሊወረውርህ መዘጋጀቱን ምነው ደበቅኸንሳ???
    የደራሲ በዓሉ ግርማን ሕለፈት ምስጢር በሚመለከት አቶ አበራ የጻፈው በመረጃ የተደገፈ ጽሑፍና ያንተ የስም ማጥፋት ተራ ዘመቻ ጭርሱኑ አይገናኙም፡፡ ባንተ የመሃይም ግንዛቤ ስለጅብ ማውራት ማለት ሁሌም ስለጎጃሜ ማውራት ማለት ነው፡፡ እንዲህም አድርጎ ቅኔ መፍታት የለም!!!!! አቶ አበራ የሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ወዳጅና እቅርብ ሰው እንደሆነ፤ የሥነ ጽሁፍ ሥራዎቹን ያነበብን ሁሉ እናውቀዋለን፡፡ በዚህም በሚኖርበት ማህበረ ሰብ ውስጥ ከሁሉም ጋር በወዳጅነት የሚኖር መልካም ሰነ ምግባር ያለው ወገናችን ነው፡፡ በእርግጥ ነውርን በነውርነቱ ሲያይ ፊት ለፊት ሂዶ የሚያጋልጥና አካፋን አካፋ የሚል የብእር ሰውነት ጥንካሬ ያለው ብርቱ ሰው ነው፡፡ እንዳንተ ያለው ተላላኪና ትናንት የወያኔ አግር አጣቢ የነበርከው ሰው፤ እማያውቁት አገር ሂዶ ቁርበት ካሰነጠፈው ጅብ በምን ትለያለህ?
    ”ላላወቀሽ ታጠኚ” እንዲሉ እዚሁ በብዙ ብዙ ነውሮችህ የምናውቅህ ገበናህን እንደሸፈንልህ ብትኖር ይበጅህ ነበር፡፡ ካልሆነ ግን አንተን ማሰተወዋቅ ግድ ሊለን ነው፡፡ እዚህ በስደት ጥያቄ የሚንከራተቱ ወንድሞችና እህቶችን በገንዘባቸውና በጾታቸው ምን ያህል እንደሸቀልክባቸው የያንዳንዱን ተጠቂ ስም እየጠቀስን ልናጋልጥህ እንችላለን፡፡ DCESON ካመራር አባልነትህ በዚሁ ወራዳ ምግባርህ ምክንያት እንዳባረረህ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ ስንቶቹን አሳይለም ጠያቂ እህቶቻችንን ነው በዚያ በተለከፍክበት ስም አይጠሬ ክፉ በሽታ የበከልከው? ለአሳይለም ኬዝህ ዋሽተህ ያቀረብከውና ዩቲዮብ ላይ ያሰለቀቅኸው የ30 ሚሊዮን ኢንቬስተርነት የውሸት ታሪክህንና ሌሎቹንም ብዙ ብዙ ስላንተ ማለት ይቻላል፡፡ ስለዚህ ያለቅምህና ያለችሎታህ ብዙ ባትንጠራራና የመልካም ሰውን ስም እያጎደፍህ ከጎኑ ፎቶ ፎግራፍ ለመነሳት ባትሞክር መልካም ነው፡፡ መቼም ያቺን ለወራት አደብ ያሰገዛችህን የፍንጫ ላይ ታሪካዊ ፊርማ አትረሳትም!!!!!!
    ደምለው

  5. አይይይይ ሰደት አግዳሚ ወንበር ነው አሉ;
    ዝም ብለህ የ ሰው ሰም አታጥፋ
    አበራ ኢትዮፕያችን ካፈራችው ድንቅ ሰው አንዱ ነው;
    እዚህ አገር ሰለ ኢትዮፕያ የሚናገር ሰው ጥሩ ብንባል
    አንዱ አቶ አበራ ነው(አንተ ማን ነህ?)

  6. MATEBE shame on you for delebrately confuse people. Writer Abera has nevr ever conotate GOJAMES as HAYENA. THIS is your dirty creation. THE mressage of o his researched article and your message are entirely different. TO get and understand his great investigative article you must go back to WASHERA.

  7. ጎበዝ እኛ እትዮጵያውያኖች ከመቸውም በጠነከረ መልኩ አንድ ሆነን በመሃላችን የሚሹለከልኩትን በቃችሁ ማለት መቻል አለብን እንደ ጋሽ አበራ ያሉ ለወያነ እጅ መንሻ የሚሆን የቢት ስራ ይዘው ሲመጡ በቃችሁ እንበላቸው!
    እኒም አንዳርጋቸው ጽጊ ነኝ!!

  8. መልእክቱን ሳይሆን መልእክተኛው መግደል ይሉሃል ይሄ ነው!!!

    ይህንን ብሽቅ ጽሁፍ ከሚጽፉ ምን አለ ጊዜዎትን ከጽሁፍ አቅራቢው የሚመጣጠን ጥናት ማድረግ ላይ ቢያውሉት እና አስተማሪ ይዘት ያለው ጽሁፍ ይዘው ቢቀርቡ!!!!

  9. To Matebe Melese,
    I carefully read Abera Lema’s amazingly beautiful analysis with reference to Baalu Girma’s disappearance before and after your comment. I found out that your comment and defamation against the personality and highest professional standard that Abera Lema portrayed in his article is a CHARACTER ASSASINATION.
    Abera Lema is a wonderful person, well educated, and a person of high moral standard. Additionally, I closely known him with his social and his political activity where he has no match or association as you tried to defame him. Moreover, Abera Lema’s article has never called upon any tribal or racial identity of the people of with whom Baalu Girma communicated the day he disappeared.
    But your comment is aimed to attack the truth about the committed crime against Baalu Girma while wrapping the crime under the auspices of tribal kebele (village) protection and with irrelevant issues. Almost all issues raised by Abera Lema are well referenced and supported with a good evidences where no village politics is evinced. Instead, we must give a credit to Abera Lema as a well versed and articulate writer for his inclusive advocacy of all victims. For instance his article named all victims such as ( ጸጋዬ እንደሻው፣ ተፈራ አሥማረ፣ ላእከ ማርያም ደምሴ፣ ሞገስ ደምሴ፣ አበራ ለማና የማነ ቸርነት) where ethnic backgrounds of each victims are never mentioned negatively or positively. Additionally, Abera Lema has never mentioned any names of locations of the people that might be associated to the disappearance of Baalu Girma.
    Therefore, your comment against Abera Lema is nothing but a self revelatory guide to one or more JIBOCH (hyenas) hidden out here among innocent/ victims. I am deeply saddened by the heinous crime committed against exceptionally talented Ethiopians such as Baalu Girma. Also, it is very sad to see a comment like yours that attacked the very politically sensitive, social fabrics, and the very backbone of the Ethiopian unity.
    Best regards,
    Merew

  10. This pathetic and idiot person ABERA LEMA accusation to the good Ethiopian Mulugeta Lule is very funny and shallow and looks like የሰፈር አሮጊቶች የቡና ወሬ his main evidence that link Mulugeta Lule to the murder or death of BEALU was the meeting happened between Mulugeta Lule an Mengistu a day before Bealu disappearance kkkkk a normal person would think there could be billions of reasons about that meeting unrelated to BEALU

    The witness about this meeting was a derg official who have no courage to give his name and how someone can use the gossip and accusation of a person who does not have a courage to stand by his comments ????????????

    obviously ABERA LEMA is mad at Mulugeta for he wrote a book against DERG and he even trashed the book kkkk ONE should remember that ABERA is accused of killing youths accused of being EPRP or ehapa

    The main reason for ABERA LEMA article targeting Mulugeta LULE is to silence Mulugeta Lule ብእር ወይም እጅ and on the way he want to make happy TPLFites as these guy is the most opportunist person this country has ever seen and i even feel sorry for him harbouring that much strong hate to someone he can not hide his hate

    the timing of this article is questionable all freedom loving Ethiopians are mourning the illegal detention of ANDARGACHEW and this stupid and evil ABERA LEMA came up with this sensational topic to divert public attention and criticizing one of the BEST ETHIOPIAN EVER and there is no way ABERA will silence the pen of MULUGETA

    SHAME ON ABERA and LONG LIVE TO THE GOOD ETHIOPIAN MULUGETA LULE

Comments are closed.

Share