የሎሬት ህመሙ ቢያመኝ!

የሎሬት ህመሙ ቢያመኝ …
———–//———
ይሞላ ብዪ ስኳትን ፣
ህልሜ እልም እያለ ቢፈትነኝ
ለህሊናየ አድር ብዪ ስማስን ፣
ድካሙ ቢሸበርክኝ
ተስፋ አልቆርጥም ባልኩ በተጋሁ፣
ህመሙ ቢደቁሰኝ
ብላቴን ጌታ ታወሰኝ ፣
ጸጋየ ህመሙ ዘልቆ ወጋኝ
የጸጋየ ህመሙን ታመምኩ
መላ ቅጡን አስጠፋኝ ።
ውስጤ ቢደማ ቢታወክ ፣
የጸጋየ ሮሮ በአይነ ህሊናየ መጣብኝ
የመጨረሻው እስትንፋስ ቃሉ ፣
ሎሬት ህመሙ አመመኝ
“እኔ ለእኔ ኑሬ አላውቅም ” ብሎ ያለን
የስንብት ጸጸት ቃሉን አዘከረኝ ፣
……. …….. ……. ……… …….. ……
የጸጋየ ጸጸት …
“የማይሰማ ወጨት ጥጄ –
እፍ ስል የከሰመ ፍም፣
ውርዴም ይፈወሳል ብዬ –
የሰው እከክ ስዘመዝም፣
በሰው ቁስል መቁሰል በቀር –
እኔ ለኔ ኖሬ አላውቅም፡፡
የማይነጋ ህልም ሳልም –
የዘመን ደዌ ሳስታምም፣
የማያድግ ችግኝ ሳርም –
የማይድን በሽታ ሳክም፣
የሰው ህይወት ስከረክም –
እኔ ለኔ ኖሬ አላውቅም፡፡ ”
…… …….. ……. …….. …… ….. ……
ባይሰማ ባያየኝ አባት አለም ፣
ተስፋው በኖ የተለየንን
የቅኔው አባት መምህሩን ፣

የጥበብ ሎሬት ፈላስፋውን
ድካም ልፋቱ መና ቀርቶ የታየውን ፣
“ግዴለም በተስፋ እንኑር አልኩት !” ጸጋየን
መላው ጠፍቶ ቢጨንቀኝ ፣
በተስፋ እኖር መስሎኝ ሳታልላት ደካማ ነፍሴን …
* ብላቴን ጌታ ጸጋየ ፣ ነፍስህን አራያ ገነት ያኑራት: (
በተጎዳ ስሜት … ይህችን ታክል ካልኩ ይብቃኝ! :(
ነቢዩ ሲራክ

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከብሔረሰብ በዓል ወደ ለታላቁ ሩጫ! - በእውቀቱ ስዩም

3 Comments

  1. እንዴት ልብን የፈተሸ ህይወት የሆነ ትርጉም ነው። „የሎሬት ህመም ቢያመኝ“ አዎን የቅኔው ንጉሥ ህመም ቢያመን እንድን ነበር። ሥርዬትን ማዬት እንችል ነበር። ከሁለገብ ራህብ እንፈወስ ነበር። ፍላጎታችን ተወልዶ ማዬት እንችል ነበር። እኛና እኛ እንሆን ነበር። ኢትዮጵያዊነትን የተረጎመ ቅኝት ነው። ጋሼ ጸጋዬ አንድ ሰው ብቻ አልነበረም ህዝብ ነበር እንጂ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ የቅኔው ልዑል ፍሬ የሆኑት ገጣሚ ነብዩ ሲራክ።

  2. ግሩም ድንቅ ግጥም ነው ። ነብዩ ሲራክ በርታ አድናቆቴን ዘወትር ከአንተ ዘንድ ነው።በርቱ ጸሐፍት ነህና።

Comments are closed.

Share