የሞረሽ እንቅስቃሴ ላልተገለጸለን አንዳንድ ነጥቦች

ከሞረሽ ደጋፊ፣ ረቡዕ ሰኔ ፫ ቀን ፪ሺህ፮ ዓ.ም.


ሞረሽ ወገኔ በወያኔ ዘረኛ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ እቅድና እንቅስቃሴ መሠረት፣ በአገራችን በኢትዮጵያ በአማራ ጎሳ ላይ በየአቅጣጫው እየደረሰ ባለው መጠነ ሰፊ ጉዳት ምክንያት ብሶት የወለደው ድርጅት ነው። በሀገራችን ታሪክ ብዙ ሳንጓዝ «አምባገነን» የሚባለው የወታደራዊው ደርግ የግዛት ዘመን ሳይቀር፣ ጎሳዎችን ሳይለይ በፖለቲካ አመለካከት ምክንያት ኢትዮጵያውያንን በግድያ ንብረታቸውንም ለመንግሥት በማድረግና በመውረስ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰባቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የአማራው ጎሳ አባላት እንደሌሎች ኢትዮጵያውያን ተጠቂ የነበሩ መሆናቸው የሚካድ አይደለም። በኢሕአፓም ሆነ በሌሎች የተቃውሞ ትግሎች የተሳተፉ፣ መስዋዕትነት የከፈሉ፣ በደርግ በኩልም በመሆን በተቃዋሚዎቹ ዒላማ ተደርገው የተገደሉ የዚሁ ጎሳ አባላት ብዙ ናቸው። ከዚያ በፊት የነበረውንም የቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት «ፍትሐዊ አይደለም» ብለው ከተነሱት የእንቅስቃሴ መሪዎችና ሰለባዎች ውስጥ ከአማራው ጎሳ የተወለዱ፣ ብዙ ለፍትሕ የቆሙ እንደነበሩ፣ ወያኔዎች ሳይቀር ይመሰክራሉ። ለአብነትም እነ የንዋይ ወንድማማቾች ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ እና ግርማሜ ንዋይ፣ ዋለልኝ መኮንን እና ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል። እነዚህ «የኢትዮጵያ አስተዳደር ትክክል አይደለም» በሚል መስዋዕትነትን የከፈሉ ከአማራ ጎሳ የተወለዱ ኢትዮጵያውያኖች እንጂ «አማራ ነን» በሚል የተንቀሳቀሱ አልነበሩም።


ወያኔዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥር አናሳ መሆናቸውን ስለሚገነዘቡ፣ በስልጣን ይቀናቀነኛል የሚሉትን ወገን ሌሎችን አስተባብሮ ማጥቃት እንደ ስትራተጂ የሚጠቀሙበት ነው። በመሆኑም በኢትዮጵያ ተፈጥረው ለነበሩ ችግሮች ብቻ ሳይሆን ያልነበረ ችግርን እንደነበረ አድርጎ፣ ለዚህም የአማራውን ጎሳ ተጠያቂ ማድረግ፣ የአጭር ጊዜ ፍላጎቱን እንደሚያሳካለት በማሰብ ነው። ስለሆነም በትላልቅ ጎሳዎችም ሆነ በአናሳ ጎሳዎች እንዲጠላና ዘመቻ እንዲካሄድበት፣ ከፍተኛ የሆነ የጥፋት ሥራ ሠርቷል። የዋህ የሆኑ የዚህ የወያኔ እኩይ የሆነ አስተሳሰብ ሰለባ የሆኑ ጎሳ አባላትም ለዘመናት አብረዋቸው የኖሩ የአማራ ጎሳ ተወላጂ የሆኑ ጎረቤቶቻቸው ላይ ከ«ውጡልን» አንስቶ እስከ ግድያ የሚደርሱ ብዙ በደሎች ሲደርስባቸው በጥቃቱ በመተባበር ወይም ዝም በማለት አሳልፈዋል፣ ወይም በማሳለፍም ላይ ናቸው። ይህንን በአማራው ጎሳ ላይ ያነጣጠረ ጭፍን ጥላቻ ማንኛውም ፍትሕን የሚሻ ዜጋ ሁሉ ሊቃወመውና ሊያስቆመው ይገባ ነበር። ሆኖም ግን ወያኔ አገሪቱን ከተቆጣጠረ ጀምሮ በአማራው ጎሳ ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት በተጠናከረ መልኩ ሲፈጸም እናያለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰሞነኛ ጉዳዮችን በወፍ በረር አንቀጾች ስንቃኛቸው - ከይሄይስ አእምሮ


በተደራጀ ኃይል ጥቃት የሚደርስባቸው ተጠቂዎች ከሚደርስባቸው ጥቃት ሲሸሹና የመጠቃት ፍራቻ ሲኖራቸው በጋራ መከላከልን መሻት ተፈጥሯዊ ክስተት ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ዘርን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጀት መኖር እንደሌለበት የሞረሽ ወገኔ መሥራቾች ጠንቅቀው ያውቃሉ። የፖለቲካ ድርጅቶች ዘርን መሠረት ሲያደርጉ የእድገት ደረጃን ያለማወቅና ሰዎችን አንድ የሚያደርጋቸው ቀለማቸው፣ ቋንቋቸው ወይም ባህላቸው ብቻ ሳይሆን አመለካከታቸው መሆኑን አለመገንዘባቸውን የሚያሳይ ነው። የሞረሽ መሥራቾች የወያኔን የጎሳ ፖለቲካ ቢቀበሉት ኖሮ ቀደም ብለው የፖለቲካ ድርጅት በመሠረቱ ነበር። ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ መጠበቅም ባላስፈለገ ነበር።


ሞረሽ እንደ መርህ በየትም ቦታ የተረገጠች ፍትሕን ትክክል አይደለም ብሎ ያምናል፣ እንዲስተካከልም ድምጽ ያሰማል። በመሆኑም በኦሮሞም፣ በጋምቤላም፣ በሶማሌም፣ በትግሬም ወይም በሌሎች ጎሳዎች በገዢውም ሆነ በሌላ ሥልጣን ፈላጊ ቡድን የሚደርሰውን ጥቃት ሁሉ አጥብቆ ይቃወማል። ሞረሽ ኢትዮጵያ የብዙ ጎሳዎች ደሴት እንደመሆኗ መጠን አንዱ ጎሳ ተጎድቶ ወይም አንዱ ጎሳ የሌለበት ኢትዮጵያ አትኖርም ብሎ ያምናል። ስለሆነም የአማራ ጎሳ የሌለባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትባልም፣ የኦሮሞ ጎሳ የሌለባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትባልም፣ የትግሬ ጎሳ የሌለባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትባልም እንዲሁም ሌሎች ጎሳዎች የሌሉባት ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ አትባልም። በመሆኑም አንዱ ሲበደል ተበዳዩ ብቻ ሳይሆን ሌላውም ሁሉ ቁጭቱን ሊገልጽና ድርጊቱን ሊቃወመው ይገባል። ያ ሲሆን የሚፈራው ሥልጣን የያዘው ሳይሆን ሕዝብ ይሆናል ማለት ነው። ትክክለኛው ፍርሀትም ይሄው ነው።


ሞረሽ በዚህ መርሁ የማንኛውም ጎሳ አባላት በግልም ይሁን በቡድን መበደል የተቃውሞ ድምጹን አጉልቶ ያሰማል። ሌሎች ጎሳዎች በዛ ያሉ ድምጽ የሚያሰሙ ቡድኖችና ድርጅቶች ቢኖሯቸውም የአማራው ጎሳ ግን በታላቁ የኢትዮጵያ ልጅ በፕሮፌሰር አሥራት ተጀምሮ ከነበረው መአሕድ በስተቀር ለጎሳው አቤቱታ የሚያሰማ፣ እየደረሰበት ያለውን ጉዳት የሚቃወም፣ የተሰባሰበ ቡድን የለውም። በሌላ በኩል ግን በወያኔ መንግሥት አስተባባሪነት በአማራው ጎሳ ላይ በየቦታው እየደረሰ ያለው ጉዳትና ጥቃት ለመለካት የሚያስቸግር ነው። በመሆኑም ሞረሽ ወገኔ በአማራው ጎሳ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለማሳወቅ አቅሙ የፈቀደውን ትግል የሚያደርግ ከመሆኑም በተጨማሪ ሌሎች አግባብነት ያላቸው መንገዶችን በመጠቀም በደል የሚፈጽሙትና የሚያስፈጽሙትን ከሕግ ፊት ለማቅረብ የበኩሉን ጥረት ያደርጋል። ሞረሽ ወገኔ ለአማራው የሚመኘውን ሰብአዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሌሎች መብቶች ለማንኛው የሀገሪቱ ጎሳ አባላት እንደሚመኚና ለተፈጻሚነቱም ድምጹን በማሰማት የመታገያ ስልቱ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል። በዚህ አጋጣሚ ሞረሽ ሊገልጸው የሚፈልገው ነገር ቢኖር አሁን ባለበት ሁኔታ የሲቪክ ድርጅት እንጂ የፖለቲካ ድርጅት አለመሆኑን ነው። እንደ ሞረሽ እምነት የጥቁሮችን መብት በማስከበር በእንቅስቃሴ ውስጥ ነጮች እንደተሳተፉና መስዋዕትነት እንደከፈሉ ሁሉ የአማራው ጎሳ የሚደርስበትን በደል «አግባብ አይደለም» ለማለትና የሚደርስበትን በደል ለማስቆም የየትኛውም ጎሳ አባላት ተሳትፎ ማድረግ አግባብነት አለው ይላል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የቅማንት የማንነት ጥያቄ ወይንስ የሕወሓት ግልጽ ወረራ? - ብሥራት ደረሰ


የሀገራችን ታሪክ እንደማንኛውም ሀገር ታሪክ መልካምም መጥፎም ገጽታ ይኖረዋል። የሰው ልጅ የሠራው ሥራ የሚገመገመውም በወቅቱ ባለው መለኪያ እንጂ ዘመናትን አሻግሮ በማይመሳሰሉ ዘመናት ባሉ መለኪያዎች መሆን የለበትም። ያለፈውን መልካም ነገር መሠረት አድርጎ ከተሠሩ ስህተቶች ተምሮ መልካም ነገርን ማምጣትና በእጁ ያለውን የአሁኑን ጊዜ በሚገባ በመጠቀም ወደፊት የሚፈጠር እውነታን መቀየርና የሚጻፍ ታሪክን መልካም እንዲሆን ማድረግ ተገቢ ነው። ይህ ለጋራ ዕድገት የተሻለ ነገርን ያመጣል። ያለፈ አፈ ታሪክ ላይ በማተኮር እድገት አይመጣም። እድገት የሚመጣው በአግባቡ የተተለመ ራዕይ ላይ በማተኮርና ተገቢውን በመተግበር ነው። በጥላቻ እድገት አይመጣም። ጥላቻ የሚያመጣውን ውጤት ለማየት ብዙ መመራመር አያስፈልግም። በዓለም ላይ ያሉ ትላልቅ ችግሮች የጥላቻ ውጤቶች ናቸው። ሞረሽ ይህንን ጠንቅቆ ያውቃል። በአማራው ላይ በወያኔ መሪነት በመጀመሪያ በሌሎች ጎሳዎች ጥላቻ እንዲደርስበት ከዚያም በመቀጠል በንብረቱና በሕይወቱ ላይ ጉዳት እንዲደርስበት ሲደረግ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ ተቆጥሯል። ልብ እንበል፥ በእናት ማህጸን ውስጥ ያሉ ያልተወለዱ ጽንሶች፣ ምንም የማያውቁ ሕጻናት ሳይቀር ታርደው እንዲገደሉ ተደርጓል። ሠርተው ከመብላት ውጭ ምንም የፖለቲካ አስተሳሰብና የሥልጣን ፍላጎት የሌላቸው ገበሬዎች ከኖሩበትና ሀብትና ንብረት ከአፈሩበት ቦታ ያለምንም ነገር ባዶ እጃቸውን ተፈናቅለው ቤት አልባ መንገድ ተዳዳሪ ለማኞች እንዲሆኑ ተደርገዋል። ይህንን ድርጊት በተደራጀ መልኩ መቃወምና ማስቆም የግድ ይሆናል። ለዚህም ነው ሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት የተቋቋመው። በመሆኑም ሞረሽ በወያኔ የፖለቲካ ፍልስፍና መሠረት የተፈጠረ ሳይሆን በወያኔ እኩይ ሥራ ምክንያት መጠነ ሰፊ የሆነ የጥፋት ዘመቻ እየደረሰበት ያለውን የአማራ ጎሳ ለመታደግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ የተቋቋመ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  መሬት የማነው? - ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

3 Comments

  1. I give green light for any religious/ethnic based civic groups that struggle for others too but I’m totally against such political parties. Religious or ethnic based political party can’t produce true democratic inclusive system, can never!!! So stop ethnic politics, join semayawi/andenet/G7 or form your own multinational political party and Obang Metho’s SMNE!! Such are our only hopes!!

  2. የሞረሽ ድርጅት በ አማራ ስም ቢቐቐምም ኢትዮጵያዊ ነው ተብሎአል፡ ያ ከሆነ ችግር የለም። የማውቀውን ልንገራችሁ፡አማራ ምን ያህል በደል እንደሚደርስበት፡ወደ ደቡብ ጎንደር ይዣችሁ ልሂድ፡ደብረ ታቦር በምኖርበት ወቅት በከተማዋ የሚሰሩ ፎቆች ሲሚንቶ ከመሰቦ መቀለ ካለው ፋብሪካ ብቻ እንዲገዛ የከተማዋ አስተዳደር ያዛል፡እዛ ከሚሰራ አንድ ወገን ጋር በጉዳዩ ስንወያይ የሚከተለውን ምስጢር ነገረኝ፡” ሐዲሽ ሐለፎም የተባለ የትግራይ ሰው የደቡብ ጎንደር ኮሚኒከሽን ቢሮ ሀላፊ ተብሎ በተሰጠው ሽፋን በዞኑ አድራጊ ፈጣሪ ዋና የሕወሀት ባለስልጣን ያዘዘውን የዞኑ አስተዳዳሪና ከንቲባው ወዘተ. ተግባራዊ ከማድረግ በቀር ባዶ ቀፎዎች ናቸው አለኝ።” አንድ የ አማራ ተወላጅ በትግራይ ውስጥ ሀላፊ ሊሆነ ቀርቶ ተራ ሰራተኛ መሆንም እንደማይችል ሳስበው አማራው በከፋ የመብት ረገጣ ውስጥ መግባቱ ቆረቆረኝ። ታድያ ሞረሽ ኢትዮጵያዊነትን መሰረት አድርጎ አማራውን ለማዳን ከተንቀሳቀሰ በደሉን የቀመስኩኝ ስለሆነ ድርጅቱ ቢበረታታ መልካም ይመስለኛል

  3. Why only AMHARA people are not allowed to have their own party to protect Amharas from the planned persecution from OLF TPLF and SHABIA ? Why it is illegal for Amharas to organize themeselves under their ethnic while it is a known fact that Amharas are not racist people who want to cecede from the rest of Ethiopia
    Amharas need to organize to protect themselves from their deadly enemies like OLF and TPLF who openly declared the poor AMHARA people as their enemies

    Those of you who pretend like Amharas and speak against the creation of an AMHARA party or something are OLFites and TPLFites who want to kill defenceless Amharas with impunity and you don’t like organization like MORESH and brave people like TEKLE YISHAW who dare to be a voice for the voicless AMHARA men,children, and women who are being persecuted in all corners of the country for the crimes they did not comment

    AMHARA people will remember MORESH and TEKLE YISHAW for their bravery and of ourse ATo TEKLE YISHAW will be the target of OLF and TPLF for the years to come to silence him as they did to other AMHARA elites

Comments are closed.

Share