May 12, 2013
4 mins read

ሁለት እግርና አንድ እጅ አልባዋ የዋና ሻምፒዮን

ካዬላ ዊህለር

ከኡመልኸይር ቡሎ
ካዪላ ዊህለር የተወለደችው ሁለት እግርና አንድ እጅ ሳይኖራት ነው:: ሐኪሟም ዋናን እንደ አንድ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንድትጠቀም ይመክራት ነበር። በእዚህ መሠረት ባደረገችው ጥረት ዊህለር ግን በ16ዓመቷ በዋና የዓለምን ሪከርድ ለመስበር ችላለች፡፡
ሲ ኤን ኤን እንደዘገበው ታዳጊዋ በብራዚል ሜክሲኮና ኔዘርላንድ ውድድሯን ያደረገች ሲሆን፤ በ2016 ፓራኦሎምፒክ ለመወዳደር እቅድ ይዛለች። በ2013 በተካሄደው50 ሜትር የሴቶች ሻምፒዮን ተወዳድራ አዲስ ሪኮርድ አስመዝግባለች፡፡
«ነገሩን ሁሉ ለመግለፅ አስቸጋሪ ነው። ስሟ ሲጠራና ዩናይትድ ስቴትን መወከሏን ሳውቅ በጣም ተገረምኩ፣ ማመን አቃተኝ፣ ከደስታ ብዛት የምይዝ የምጨብጠውን አጣሁ። ይች እኮ የእኔ ድንቅ ልጅናት አልኩኝ» ይላሉ እናቷጆሲ ዊህለር፡፡
«ሁሌም ምንም ማድረግ የማትችይው ነገር የለም እያልን እንነግራታለን። ነገር ግን ነገሮችን ላንቺ ማድረግ እንዲመቹ ማመቻቸት ይጠበቅብናል ስለምንላት እርሱዋም በጥረቷ ቀጠለች» ሲሉ አክለዋል።
ዊህለር በማትዋኝባቸው ጊዜያት ቤዝቦል እና ቦውሊንግ በመጫወት ጊዜዋን ታሳልፋለች በትምህርቷም ከፍተኛ ውጤት የምታስመዘግብ የደረጃ ተማሪ ስትሆን፤ በኮምዩኒቲ ኮሌጆች አድቫንስድ ኮርሶችን ትወስዳለች፡፡ ንቁ ተሳተፎም ታደደርጋለች፡፡
በእዚህ ዓመት ባስመዘገበችው ከፍተኛ የአትሌቲክስና የአካዳሚክ ውጤት «ስኩላ ስቲክ» የተባለ የክብር ስያሜ አግኝታለች፡፡
በርግጥ ዊህለር በ2012ም ፓራኦ ሎምፒክ ለመወዳደር ተመርጣ ነበር። ነገር ግን እንዳጋጣሚ ሆኖ አብሯት የሚወዳደር ሰው ባለመኖሩ ሳትወዳደር ቀርታለች። ምክንያቱ ደግሞ በፓራኦሎምፒክ የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች የሚመደቡት እንደ አካል ጉዳታቸው ደረጃ በመሆኑ በእርሷ የጉዳት ደረጃ የሚወዳደር ሰው ባለመኖሩ ነው፡፡
« አምና በፓራኦሎምፒክ አልተወ ዳደርኩም ነበር። ምክንያቱም በእኔ ምድብ የምትወዳደር ሌላ ሴት ተወዳዳሪ አልነ በረችም። የእኔ ምድብ ኤስ ዋን ሲሆን፤ በእዚህ ምድብ የሚካተቱ ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ናቸው» ትላለች ዊህለር።
«ሃገሬን በመወከል መወዳደር እፈል ጋለሁ። አዲስ ሪኮርድ ማስመዝገብና ሜዳሊያ ማግኘት በጣም የሚያስደስትና የሚያስገርም ነገር ቢሆንም እኔ ግን ከውድድሩ ባሻገር አርዓያ በመሆን እዚያ ቦታ መገኘት እፈልጋለሁ» ብላለች።

piremier legue
Previous Story

የ2012/2013 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ አስሩ መጥፎ የተጫዋች ዝውውሮች

Next Story

የአቶ አስገደ ልጆች ምን ወንጀል ሠሩ? (አሕለፎምና የማነ አስገደ) – ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop