የፍትህ ሚ/ሩ ብርሃን ኃይሉ ከስልጣናቸው ተባረሩ

አቶ ብርሃን ኃይሉ ስዊድናዊያኑ ጋዜጠኞች በይቅርታ ተለቀዋል በሚል መግለጫ የሰጡ ዕለት የተነሱት ፎቶ ነው።(ዘ-ሐበሻ) በዚህ ዓመት ማርች 2005 ዓ.ም ባህርዳር ላይ በተደረገው የኢሕአዴግ ጉባኤ ላይ ከ255ቱ የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚዎች መካከል ብአዴንን ጥላቸው አድርገው በድጋሚ ተካተው የነበሩት የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ሃይሉ የአቶ መለስን የሕወሓት የበላይነት ሌጋሲ አስፈጻሚው ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ ፊርማ መባረራቸው ተሰማ።
ቃሊቲን ጨምሮ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞች በሃሰተኛ ሕወሓት ሠራሽ ክሶች ወደ ዘብጥያ ሲወረወሩ ይህን ሃሰተኛ ክስ በማስፈጸም ታማኝነታቸውን ሲያሳዩ የከረሙት አቶ ብርሃን ሃይሉ ከስልጣናቸው መነሳት አሁንም ለሆዳቸው አድረው ከመንግስት ጎን በመቆም የሕወሓትን የበላይነት ለማንገሥ እየሰሩ ላሉት ባልሰልጣናት ትምህርት ይሆናቸዋል የሚሉ አስተያየቶች እየተሠነዘሩ ነው።
በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ በአንካሳ ሕግ እስር ቤት ለሚማቅቁት ወገኖች አናካሳውን ሕግ በማስፈጸም ረገድ ተጠያቂ እንደሆኑ በህዝብ ዘንድ የሚመሰከርባቸው አቶ ብርሃን ሃይሉ ከዚህ ቀደምም በፈረሰው ማስታወቂያ ሚ/ር በሚኒስትርነት ማዕረግ በመሥራት የሕወሓት መንግስት የነደፈውን የመናገር መብትንመንፈግን ሲያስፈጽሙ ቆይተዋል።

ሚንስትሩ እ.አ.አ በ2005 ዓ.ም. በማስታወቂያ ሚንስትርነት ሲሰሩ ነበር። ሆኖም ማስታወቂያ ሚንስትር እንዲፈርስ ሲደረግ፤ በቀጥታ ሌላ ሹመት በማግኘት የፍትህ ሚንስትር ሆነው ኢህአዴግን በታማኝነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

ከሰሞኑ የባልስልጣናት በሙስና መታሰር፤ የአቶ ብርሃን መባረር ኢሕአዴግ ውስጥ ያለውን ሽኩቻ ያሳየ ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪዎ አብዛኛው የኢሕ አዴግ ባልስልጣናት በሙስና ተጨማልቀው እያለ እነዚህ አሁን የታሰሩትን፤ ሁሉም የኢሕ አዴግ አመራሮች የአምራርነት ብቃት የሌላቸው መሆኑ እየታወቀ ጊዜ ጠብቆና ባልስልጣናቱ ለምን? ማለት ሲጀምሩ እንደብርሃን ኃይሉ ከስልጣን ማሰናበት የተለመደ የወያኔ የፖለቲካ አካሄድ ነው ሲሉ ሃሳባቸውን ይሰነዝራሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  13ቱ ሙስሊም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች 3ት የመከላከያ ምስክራቸውን አሰሙ፤ ሙሐመድ ሰዒድ እርቃኑን ተገርፏል

አቶ ብርሃን ኃይሉ ሥልጣን ላይ በነበሩ ጊዜ ስለ እስክንድር ነጋ ጠረጴዛ እየመቱ የተናገሩትን ለግንዛቤ እንደሚከተለው ቪድዮውን አቅርበነዋል።

6 Comments

  1. let him go hell and i would not mind to be the first person to open the hell get for him…

  2. TPLF must be joking. Do you guys think only these guys have been corrupting? all
    TPLF officials and puppets of the TPLF are all corrupt. They should be fired.

  3. Hodam amahra who surrendered to woyane .thugs , I hate such soft -headed low life people of Behanes’ like.

  4. መልሰው ይሾሙታል የሚጠቅማቸው ከሆነ፣ በተለይም ለ ህውሀት ታማኝ ከሆነ

  5. wusha !!!!!!!!!!!!!!! balege!!!!!!!!!!!!!! minister of JUSTICE? what a name for a such stupid chigeram.

  6. What goes around it comes around,he was suppose to be the smart one and sold his soul and pride for his own benefit

Comments are closed.

Share