አቶ መለስ ዜናዊ በአፍሪካ የጋራ መገማገሚያ መድረክ ላይ የፈፀሙት አሳፋሪ ወንጀል ሲጋለጥ…(በትረ ያቆብ)

በ በትረ ያቆብ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአፍሪካ ምድር ላይ ሰላምና ብልፅግና እዉን ያደርጋል ተብሎ በአፍሪካ ህብረትና በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋት ታምኖበት የተቋቋመዉ እና “የአፍሪካ የጋራ መገማገሚያ መድረክ” (African Peer Review Mechanism) የተሰኘዉ ተቋም በአጭር ጊዜ ዉስጥ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ የተነሳለትን አላማ እንደሳተ እና ከጥቅም ዉጭ እንደሆነ እየተነገረ ነዉ፡፡ በተያያዘም በተደራጀ የሙስና ሰንሰለት ተጠልፎ የግለሰቦች ኪስ ማድለቢያ እንደሆነም እየተገለፀ ይገኛል፡፡ ከዚህ ብዙ አፍሪካዉያንን ካሳዘነ ጉዳይ ጋር በተያያዘም በቀዳሚነት የቀድሞዉ የሀገራችን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና ፓርቲያቸዉ ህወሐት/ኢህአዴግ አብረዉ እየተወነጀሉ ነዉ፡፡

ይህን አሳፋሪ የአቶ መለስን እና የፓርቲያቸዉን ተግባር በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ መረጃ የደረሰኝ ከሶስት ወር በፊት ሲሆን ፡ መረጃዉን ለጓደኛየ የላከችለት አንዲት በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ጥናት ያካሄደችና ብዙ ዘገባዎችን የሰራች አፍሪካዊ ጋዜጠኛ ነበረች፡፡ የላከችዉም ኢትዮጵያዉያን ሊያዉቁት ይገባል በሚል ነበር፡፡ ባደረግኩት መጠነኛ ጥናት እንደተረዳሁት ጉዳዮ ባልታወቀ ምክንያት ተዳፍኖ እንዲቆይ ህብረቱ ብርቱ ጥረት ያደረገ ሲሆን ፤ ህወሃት/ኢህአዴግም ጉዳዮ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀሮ እንዳይደር ብዙ ጥሯል፡፡ ያም ሆኖ ግን ጉዳዩን በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎች ከዚህ በፊት በአንዳንድ የአፍሪካ ሚዲያዎች አማካኝነት ለህዝብ ይፋ ሊሆኑ ችለዋል፡፡ ነገር ግና እስከ አሁን ግልፅ በሆነ መንገድ መረጃዉ ለህዝብ እንዳልደረሰ ይነገራል፡፡

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት “የአፍሪካ የጋራ መገማገሚያ መድረክ” (African Peer Review Mechanism) የተቋቋመዉ በ2003 ዓም ሲሆን ፤ የተቋሙ አላማም የእያንዳንዱን የሕብረቱ አባል ሀገር አጠቃላይ የፖለቲካ ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ በተመለከተ በገለልተኝነት ጥናት እና ግምገማ ማድረግ እንዲሁም ከዚህ በመነሳት የፖሊሲ አቅጣጫችን ለኃብረቱ በማቀበል ኔፓድ ግቡን እንዲመታ ማድረግ ወይንም የአፍሪካን ሰላም እና ብልፅግና ማረጋገጥ ነዉ፡፡ በተለይም ተቋሙ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ፣ በመልካም አስተዳደር ፣ ሙስና እና የሀብት አጠቃቀም ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል፡፡ ተቋሙ በእነዚህ እስትራቴጅክ የአፍሪካ ሀገራት ችግሮች ላይ መስራትና ለዉጥ ማምጣት ከተቻለ አፍሪካን ካለችበት ኋላ ቀርነትና ድህነት ማዉጣት ይቻላል የሚል እምነት አንግቦ የተነሳ ነዉ፡፡

ተቋሙ የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት መሪዎችን አቅፎ የያዘ ሲሆን ፤ የተቋሙ ፖሊሲ እንደሚጠቁመዉ በዋና ማስተባበሪያ ፅሕፈት/ቤቱ ስር በየሀገራቱ የሚቋቋሙ በገለልተኝነት የየሀገራቱን ሁኔታ የሚገመግም እና የሚተነትን ገለልተኛ አካላት አሉት፡፡ የእነዚህን አካላት ጥናትን መሰረት በማድረግም የየሀገራቱ መሪዎች በየጊዜዉን እየተገናኙ ይመካከራሉ ፤ ፖሊሲዎችን ይነድፋሉ ፣ መፍትሄ ያፈላልጋሉ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ክልል መፍትሔ አይደለም! - አንዱ ዓለም ተፈራ

ከእጄ የገቡት መረጃዎች እንደሚያስረዱት የአፍሪካ የጋራ መገማገሚያ መድረክ አጀማመሩ የተሳካ የሚባል ነበር፡፡ በአጭር ጊዜ ዉስጥም በርካታ ሀገራትን በአባልነት ማቀፍ ችሎ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ብዙም ሳይቆይ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ምንም እንኳን ከተቋሙ ምስረታ ጋር በተያያዘ ትልቅ ድርጃ የነበራቸዉ ሰዉ የነበሩ ቢሆኑም እንዲህ አይነት ገለልተኛ ተቋም በሚያፈቅሩት መንበራቸዉ ላይ የሚፈጥረዉን አደጋ ከጅምሩ በመረዳት በተቋሙ ላይ ጥቃት እንደሰነዘሩበት እነዚህ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

እዚህ ላይ ለምን እና እንዴት ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነዉ፡፡ የተቋሙ ፖሊሲ እና ህግ ሶስት የተቋሙ ንዑሳን ክፍሎች በየአንዳንዱ ሀገር ይደነግጋል፡፡ ከነዚህ ዉስጥ “የአፍሪካ የጋራ መገማገሚያ መድረክ የብሄራዊ አስተዳደር ጉባኤ” የተባለዉ የተቋሙ ዋና እስትራቴጅክ አካል ሲሆን ፤ ተግባሩም ግምገማና ጥናት በሚወክሉት ሀገር ላይ በማካሄድ ሪፖርት እንዲያዘጋጁና ለተቋሙ የበላይ አካል ማቅረብ ነዉ፡፡

የተቋሙ ፖሊሲ እና ህግ ይህ ንዑስ ክፍል የሚያካሂደዉ ጥናትና እና ግምገማ ነፃና ገለልተኛ እንዲሆን እና የሚያዘጋጀዉ ሪፖርትም ትክክለኛ ፣ ታማኝ እንዲሁም የሀገራቱን እዉነተኛ ገፅታ የሚያሳይ እንዲሆን በማሰብ ንዑስ ክፍሉ ፍፁም ከመንግስት ገለልተኛ እንዲሆን በግልፅ ደንግጓል፡፡ በዚህም መሰረት ክፍሉ  ከፖለቲካዉ ገለልተኛ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ፣ ከተለያዩ ሲቪክ ማህበራትና ተቋማት የተዉጣጡ ግለሰቦችን ፣ ምሁራንን ፣ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችን የሚወከሉ ፖለቲከኛዎችን እና የመሳሰሉትን የሚያቅፍ ሲሆን ፤ ተቋሙን የሚመሩ ግለሰቦችም ፍፁም ከመንግስት ገለልተኛ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ይሁንና ይህ የተቋሙ ፍፁም ገለልተኛ መሆን በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና በፓርቲያቸዉ ፍፁም አልተወደደም ነበር፡፡ በህዝባቸዉ ላይ የሚፈፅሙትን ዘግናኝ ወንጀል ለዓለም ህብረተሰብ አጋለጡብኝ በሚል እንደ ሂዉማን ራይቶች ያሉን አለም አቀፍ ተቋማትን አይን ላፈር ያሉት እና በሀገሪቱ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ ሲቪክ ማህበራትን ጉሮሮ ያነቁት አቶ መለስ ያንን መሰል ጠንካራ ተቋም በፍፁም የሚታገሱት አልሆነም፡፡ በተለይም በተቋሙ የሚካሄደዉ ጥናት እና የሚዘጋጀዉ ሪፖርት የኢትዮጵያ መንግስት ከሀያላኑ ሀገራትና እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዲሁም ከተለያዩ ምዕራባዊ ተቋማት በሚያገኘዉ ብድርና እርዳታ ላይ ችግር የሚፈጥርባቸዉ በመሆኑ ተማቋሙን በመዳፋቸዉ ጠልፎ ለመጣል እንዲንቀሳቀሱ እንዳስገደዳቸዉ የተለያዩ መረጃዎች ይጠቁማሉ ፡፡ እናም አቶ መለስ ጊዜ አላባከኑም ነበር ፤ በፍጥነት በሀገር ዉስጥ በተቋቋሙት የተቋሙ ንዑሳን ክፍሎችን ዉስጥ ጣልቃ በመግባት ተቀዋማቱን በቁጥጥር ስራቸዉ እንዲዉሉ ለማድረግ ደፋ-ቀና ይሉ ጀመር፡፡ በመጨረሻም ጥረታቸዉ ሰምሮ ተቋማቱን በመዳፋቸዉ ማስገባት ቻሉ፡፡ በተለይም “የአፍሪካ የጋራ መገማገሚያ መድረክ የብሄራዊ አስተዳደር ሸንጎን” የህዝብ ዉክልና በማሳጣት በኢህአዴግ የፖለቲካ ካድሬዎች እንዲሞላ በማድረግ እና የተመረጡ ካድሬዎችንም በመሪነት ቦታ ላይ በማስቀመጥ መንግስት በሀገሪቱ ላይ የሚፈፅመዉን ወንጀል በማጋለጥ የህብረተሰቡ ድምፅ ይሆናል ተብሎ የተጠበቀዉን ተቋም ጠመዘዙት፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ያለ ርዕስ የተጻፈ ወቅታዊ ማስታወሻ - ዳግማዊጉዱካሣ

በወቅቱ ይህ አቶ መለስና ህገ-ወጡ ፓርቲያቸዉ የፈፀሙትን እኩይ ተግባር የአፍሪካ ህብረትና አባል ሀገራት ሊታገሉት እና ለምን ሲሉ ሊጠይቁ ይገባ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ያለመታደል ሆኖ ያንን ያደረገ አካል አልነበረም፡፡ እንዴዉም ብዙ የአፍሪካ መንግስታት በሀገራቸዉና በህዝባቸዉ ላይ የሚፈፅሙትን አሳፋሪ ተግባር ለመሸፈን ሲሉ የእነ አቶ መለስን ተግባር እንደ ጥሩ ተሞክሮ በመዉሰድ በየሀገራቸዉ ተግባራዊ ያገርጉት ጀመር፡፡ ይህም ተጠናክሮ ቀጥሎ በስተመጨረሻ ተቋሙን የፖለቲከኞች መሰብሰቢያ እና መፈንጫ አደረገዉ፡፡ በጉጉት ይጠበቅ የነበረዉ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከሸፈ፡፡ ከታለመለት መስመር ወጣ፡፡

አቶ መለስ እዚህ ላይ ብቻ አልተገቱም ፤ ጥረታቸዉን አጠናክረዉ በመቀጠል በስተመጨረሻ በተቋሙ አህጉራዊ ዋና ማስተባበሪያ ፅህፈት/ቤት ዉስጥ የራሳቸዉን ሰዉ ህገ-ወጥ በሆነና በሚያሳፍር መንገድ አስርጎ እስከማስገባት ደረሱ፡፡ ይህንንም በማድረጋቸዉ ተቋሙን በመዳፋቸዉ አስገብተዉት እንዲቆዩ እስችሏቸዋል፡፡

በአቶ መለስ አሻጥር የተቋሙ አሀጉራዊ ፅ/ቤት ሐላፊ ሆነዋል በሚል በተለያዩ የተቋሙ የቀድሞ ባለስልጣናትና አፍሪካዊ ጋዜጠኞች የሚወነጀሉት ግለሰብ አቶ አሰፋ ሽፋ በመባል የሚታወቁ የኢህአዴግ ሰዉ ሲሆኑ ፤ ሰዉየዉ ከህግ ዉጭ ለረጅም ጊዜ በስልጣን ላይ ቆይተዋል፡፡  ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ የቀድሞ  የተቋሙ ባለስልጣን የነበረ ሰዉ ለአንድ ጋዜጠኛ ሲናገር “ምንም እንኳን የማስተባበሪያ ፅ/ቤቱ ሐላፊ በየአመቱ በጠቅላላ ጉዳኤ የሚመረጥ ቢሆንም ይህ አሰራር ግን በአቶ አሰፋ ላይ አልተተገበረም ነበር፡፡” ሲሉ ይናገራሉ፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት አቶ አሰፋ ወደ መንበረ ስልጣኑ የመጡት ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ የተቋሙ የኢትዮጵያ ተወካይ በነበሩትና በመንግስት ታማኝነታቸዉ በሚታዎቁት በአቶ ንዋይ ገብረአብ  ተፅፎ በወቅቱ የፓነሉ (Panel of Eminent Person) ሰብሳቢ ለነበሩት ለፕሮፌሰር ሳዌር በተላከ ደብዳቤ ብቻ ነበር፡፡ ይህ አሰራርም ከተቋሙ ፖሊሲ ጋር ፍፁም የሚጋጭ ነበር፡፡

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አቶ መለስ ይህንን ህገ ወጥ ተግባር በሚፈፅሙበት ወቅት የዚህን ትልቅ ራዕይ ሰንቆ የተነሳ አሀጉራዊ ተቋም ጠቅላላ ጉባኤ በሊቀመንበርነት ይመሩ የነበረ ሲሆን ይህም ለአላማቸዉ መሳካት ሳይጠቀሙበት አልቀሩም፡፡ በተያያዘም አንዳንድ አፍሪካዊ ጋዜጠኞች ሰዉየዉ በተቋሙ ዉስጥ የነበራቸዉ ተቀባይነትም በተወሰነ መንገድ ጠቅሟቸዋል ሲሉ ይናገራሉ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የማለዳ ወግ ...ዞን 9 ኞችን አደግፋለሁ !አግብቷቸው ስለጦመሩ መብታቸው መገፈፍ የለበትም (ነቢዩ ሲራክ)

አቶ አሰፋ ሽፋ የመጡበት መንገድ ከዚህም በላይ አስገራሚ ነበር፡፡ ጉዳዩን ሲከታተሉ በነበሩ አፍሪካዊ ጋዜጠኞች የወጣዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ሰዉየዉ ማስትሬት አለኝ ብለዉ የትምህርት ማረጃ ለተቋሙ አቅርበዉ አቅርበዉ ነበር ፣ ያቀረቡት ማስረጃም  ደቡብ አፍሪካ በሚገኝ አንድ ዩኒቨርሲቲ እንደተማሩ ያትታል፡፡ ሆኖም ግን ጋዜጠኞቹ ወደ ተባለዉ ዩኒቨርስቲ በመሄድ የሚመለከታቸዉ አካላትን ሲጠይቁ ያገኙት መልስ የሚያስደነግጥ ነበር፡፡ ዩንቨርስቲዉ እንዲህ የሚባል ሰዉ አላስተማርኩም በማለት አቶ አሰፋ ያቀረቡት ማስረጃ የሀሰት እንደነበር ገልጠዋል፡፡

ይበልጥ የሚያሳፍረዉ ግን አቶ ሽፋ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ የተፈፀሙ አስነዋሪ ተግባራት ናቸዉ፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሰዉየዉ እንዳሻቸዉ የፈለጉትን ያህል ዶላር እየመዠለጡ ያሻቸዉን ከማድረግ ባለፈ ተቋሙንም ለከፋ ሙስና አጋልጠዉታል፡፡ ተቋሙን ጠያቂ የሌለበት ቤት አስመስለዉት አልፈዋል፡፡ በዚህም አልበቃ ብሎ ሰዉየዉ የፈለጉትን ያህል እስኪበቃቸዉ እንዲመዘብሩ ኮንትራታቸዉ እየተራዘመ በስልጣን ላይ ለተከታታይ አመታት እንዲቆዮ የተደረገ ሲሆን ፤ ይህም የተቋሙን አሰራር የተላለፈ ነበር፡፡ እዚህ ላይ አቶ መለስ ይህንን አሳፋሪ ጉዳይ እያዎቁ ዝም ብለዋል ሲሉ ጋዜጠኞች ይዎነጅሏቸዋል፡፡

የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዛሬ በዚህ አፍሪካዊ ተቋም ዉስጥ ከሙስና ባሻገር የለየለት አንባገነናዊ እና ብልሹ አሰራርም ተንሰራፍቶ ይገኛል፡፡ ይህም ተቋሙን ግልፅ የሆነ የኦዲት ስርዓት እንኳን የሌለዉ እስከመሆን አብቅቶታል፡፡ ኦዲት ቢደረግ እንኳን ለይስሙላ እንጅ ተግባራዊ በሆነ መንገድ ወጭንና ገቢዉን ለመቆጣጠር እና ችግር ሲኖር የእርምት እርምጃ ለመዉሰድ አልነበረም የሚያስብሉ በርካታ ማስረጃዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ በቅርቡ አንድ በዉጭ ሀገር ተቋም በተሰራ ኢዲት አቶ አሰፋ ሽፋ በግልፅ ያለ አግባብ የወሰዱት ገንዘብ እንዳለ በማሳየቱ ገንዘቡን ገቢ እንዲያደርጉ ቢጠየቁም ሰዉየዉ ግና የዉስጥ ግብረ አበሮቻቸዉን መከታ በማድረግ አሻፈፈረኝ ብለዉ የወሰዱትን ገንዘብ ሊመልሱ አላቻሉም፡፡ ቆይቶም ይህ አሳፋሪ ተግባር እንዲሁ ታልፏል፡፡

በወቅቱ የተፈፀሙት የሙስና ወንጀሎችና ሌሎች ተግባራት እንደ አፍሪካ ህብረት ባለ ተቀዋም ዉስጥ ይፈፀማል ተብሎ የማይታ ሰብ እጅግ አሳፋሪ ነበር፡፡ መረጃዉን ለመጀመሪያ ግዜ ይፋ ያወጣችዉ አፍሪካዊ ጋዜጠኛ እንደጠቆመችዉ ለዚህ ሁሉ ስርዓት አልበኝነት ምክንያቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ናቸዉ ያለች ሲሆን፡፡ ሰዉየዉ ኔፓድን እና ተቀዋሙን በቁሙ ቀብረዉታል ትላለች፡፡

5 Comments

  1. I am very sorry for you. You always tell us the drawbacks of our govenment so that we can struggle for our freedom. But you are still abroad. Have not you seen the great strugglers Nelson Mandela or Mahtama Gandhi or just heard about them? They did not motivate their nation while they stayed abroad. They were the part of the struggles. Their aim was not to assume power rather to be the change they wish to see in their country. If you really want to see a change in Ethiopia come here and struggle for it; do not act like a catalyst!!

  2. m/zenawi was a stupid racist (ediet) leader.he was implemented the mission of fasicist italiya.i HATE HATE HATE all tigrians.cause they are anti ethiopia.

Comments are closed.

Share