የመብት ረገጣውንና የከፋፋዮችን ሤራ በጋራ እናስወግድ! (ሸንጎ)

ግንቦት 19 2006 (ሜይ 27 2014)

 

ሁሉ ከገዥው ቡድን የሚሰጠው ምላሽ የሚያነሳውን ጥያቄ በመመርመር፣የደረሰበትን ብሶት በማዳመጥ ሰላማዊ መፍትሄ ከመሻት ይልቅ ድብደባ፣ እሥራት፣ ስቃይና ግድያ እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ይህ ለሃያሦስት ዓመታት ሳያባራ የቀጠለው የግፍ ተግባር እነሆ በቅርቡ በአምቦ፤ በነቀምት፤ በጊምቢና በሌሎቹም የሀገራችን ክፍሎች ውስጥበዘግናኝ መልኩ ተደግሟል። ጨካኙ የህወሓት፨ኢህአዴግ አገዛዛ በሥርዓቱ ፖሊሲ ላይ ተቃውሟቸውን ለማሰማት ሰላማዊ ሰልፍያካሄዱ ተማሪዎችን፣ ከአሁን በፊት በጎንደር፣ በአዋሳ፣ በአዲስ አበባና በሌሎች ቦታዎች እንዳደረገው፣ ዛሬም በጥይት ደብድቦ ብዙዎችንገድሏል፤ ሌሎችንም አቁስሏል።

 
ደግመን ደጋግመን እንደገለጽነው፤ ይህ ሰብዓዊ ርህራሄ የጎደለው ተግባር በኢትዮጵያውያን ሁሉ መወገዝ አለበት። በሀገራችን ምድርውስጥ በፍጹም እንዳይደገምም ሁሉም ተባብሮ ሊነሳና አምቢ፤ በቃ ሊል ይገባዋል። ይህን ዓይነት አስከፊ ወንጀል የፈጸሙ ሁሉለፍርድ መቅረብ ይኖርባቸዋል።

 
አገዛዙና በግድያው የተሳተፉት ሁሉ ሊገነዘቡት የሚገባው ነገር ቢኖር የዚህ ዓይነት ጭፍጨፋና መንግሥታዊ ሽብርተኝነት የሕዝብንብሶት አባብሶ፣ ሰሜቱን እንዲሸፍት እንደሚያደርገው እንጂ አፍኖ ማጥፋት በፍጹም እንደማይቻል ነው። የሕዝብን ተቃውሞበጉልበት ማጥፋት የሚቻል ቢሆን ኖሩ ለ፪፫ ዓመታት የተካሄደው ማለቂያ የሌለው ግፍ ሕዝቡን ሰጥለጥ እንዲል ባደረገው ነበር።
በሀገራችን ውስጥ ያለውን እውነታ በትክክል መረዳት ለሚፈልግ ሰው የገዥው ቡድን የግፍ ተግባር እየከፋ በሄደ ቁጥር የሕዝቡምእምቢኝ ባይነት እየጠነከረና እየተስፋፋ መሆኑን በቀላሉ ማየት ይችላል።
ህወሓት፨ኢህአዴግ በሥልጣን ላይ ለመቆየት የመብት ረገጣ ብቻ ሳይሆን ሕዝባችንንም እርስበርሱ በጥርጣሬና በጠላትነት እንዲተያይ አንዲሁም የአንዱ ቋንቋ ተናጋሪ የሌላው ቋንቋ ተናጋሪ፤ የአንዱ ሃይማኖት ዕምነት ተከታይ የሌላው ሃይማኖት ዕምነት ተከታይ ጠላትእንደሆነ አድርጎ የሚያራመደው የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የሀገራችን ችግር መንስዔ መሆኑን በገልጽ መረዳት ይቻላል።
አገዛዙ ሲያራምደው የቆየው የሃያ ሦስት ዓመት ከፋፋይ ፖሊሲው በአሁኑ ወቅት አስከፊ ገጽታው በተለያየ መልክ በመገለጥ ላይ ነው። ዜጎች በፍቅርና በሰላም ተከባብረው ተረዳድተውና አንድ ሆነው መኖር ሲገባቸው እርስበርስ እንዲጋጩ እየተደረገ ነው። አንዱኢትዮጵያዊ ሌላውን ከአካባቢው ለቅቆ እንዲሄድ የማስጨነቅ፣ የማሰፈራራት የማስገደድ ተግባሮች ከቀን ወደቀን እጅግ አሳሳቢ በሆነመልኩ እየተካሄደ ይገኛል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዛሬስ - ትንሽዬዪቱ አብረህት ስታለቅስ ሕወሃታውያኑ ልባቸው ራርቶ ይሆን? -  በየነ ከበደ

 
የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ይህ ተግባር የሚፈጸመው በአብዛኛው ባለሥልጣኖችና ካድሬዎቻቸው አማካኝነት ነው። ለምሳሌከጉራፈርዳና ከሌሎችም የቤነሻንጉል አካባቢ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲባረሩ የተደረገው፡ በአካባቢው ከፍተኛ ባለሥልጣኖች ትዕዛዝ ነው። ከጥቂት ዓመታት በፊት ከወለጋ ንብረታቸውን ተነጥቀው በጉልበት ተፈናቅለው የተባረሩት በሺዎች የሚቆጠሩወገኖቻችንም ግፍ የተፈጸመባቸው በአገዛዙ ባለሟሎች አጋፋሪነት ነበር። ይህ የአንዱን ቋንቋ ተናጋሪ ኢትዮጵያዊ የሌላው ጠላት እንዲሆን፤ የአንዱን ኅብረተሰብ ክፍል ጥቅም ለማስጠበቅ ሌላውን ማግለል እንደሚገባው በሚያደርግ ከፋፋይና አርቆ አሳቢነትየጎደለው አመለካከት በፈጠረው አጥፊ ሁኔታ ተጠቅመው የአገዛዙ ባላሟሎች ብቻ ሳይሆኑ ጠባብ ብሄረተኞችም በሕዝባችን ውስጥ አለመተማመን፣ ጥርጣሬና መርዘኛ ክፍፍል ለመንዛት መሞከራቸው አልቀረም። በቅርቡ በአንዳንድ ቦታዎች የተከሰቱት ሁኔታዎች የሚያመለክቱትም ይህንኑ ነው።

 
ዓይኑን ጨፍኖ በክህደት ውስጥ የሚገኘውና የከፋፋይነትን መርዝ የዘራው የህወሓት፨ኢህአዴግ አገዛዝ ግን በሀገሪቱ ውስጥ ሰላምእንደሰፈነ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ነገር ተንበሽብሾ ሕዝቡም የደስታ ኑሮ እየኖረ እንደሆነ ሊነግረን ይሞክራል። ሃቁ ግን የተገላቢጦሽ በመሆኑ በሀሰት ፕሮፖጋንዳ ራስን ለማታለል ካልሆነ በስተቀር ሕዝብን መሽንገል እንደማይቻል ግልጽ መሆን አለበት።
ሕዝባችን መሠረታዊ በሰላም የመኖር መብቱን ከተገፈፈ ቆይቷል። የህልውና ዋስትናውን አጥቷል። በሰላም ገብቶ የመውጣት፣ ውሎየማደር መብትና ዋስትና ሊያገኝ አልቻለም። ይህ አደገኛ ሁኔታ በዚሁ ከቀጠለ ሀገራችንንም ሆነ ሕዝባችንን እጅግ ዘግናኝ ሁኔታይጠብቃቸዋልና ዛሬውኑ እንዲቆም የምንችለውን ሁሉ ማድረግ አለብን። ከዚህ ዓይነቱ የርስበርስ ጥላቻና ግጭት የሚጠቀም ማንም እንደማይኖር መረዳት ያስፈልጋል።

 
በኢትዮጵያችን ውስጥ በሁሉም ላይ አስከፊ የመብት ረገጣ እየተካሄደና የሕዝባችንም ስቃይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ነው። በመሆኑም የሀገራችንን ችግር ለመፍታት የትግል ትኩረታችን ከፋፋዩንና ጨቋኑን የህወሓት፨ኢህአዴግ የግፍ አገዛዝ በጋራ አስወግደን በምትኩ አንድነቷ በተጠበቀ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉንም ዜጋ በእኩልነት የምታስተናግድ ዴሞክራሲያዊና ህገ፡መንግሥታዊሥርዓት የሚያከብር ሕዝባዊ ሥርዓት መመሥረት ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የከፋፋዩችን ሴራ

ተጨማሪ ያንብቡ:  እረ ለመሆኑ ከአንድነት ወዲያ ለኦሮሞ ማን ሊመጣ ነው? 

 

 

 

 

 

 

 

 

2 Comments

  1. aye shengo….keyebotaw yetebarerew Amara new lemalet deferet atachehu,durus yetegere menega adelachehu shengo bemulu.

Comments are closed.

Share