ምኒልክን ብትወቅሱ ማንነታችሁን ትረሱ (ዶ/ር ኃይለማርያም ላሬቦ)

(ዶ/ር ኃይለማርያም ላሬቦ)

በቅርቡ የአፄ ምኒልክን ስም የማጒደፍ ዘመቻ ያተኰረው ንጉሠ-ነገሥቱ በአሩሲ ውስጥ አኖሌ በተባለ ቦታ ፈጸሙ በተባለ ግፍ ላይ ነው። እንግዴህ “ሞኝና ውሃ እንደወሰዱት ይሄዳል” እንደሚባለው… ቅሌታም ብቻ ነው ልበ-ወለድን እንደእውነት፣ ምናብን እንደድርጊት አድርጎ የሚወስደው። ከዚያም አልፎ ደራሲው የታሪክ ባለሙያ መሆን ይቅርና የዐሥራ-ሁለተኛ ክፍል ትምህርት እንኳን ማጠናቀቅ ያልቻለ ግለስብ ነው። በዚህ በፈጠራ ጽሑፍ ተመሥርቶ ሐውልት የሚያሠራው ግለ-ሰብም ሆነ ባለሥልጣን በግድየሌሽነት የሕዝቡን ገንዘብ ማባከን ብቻ ሳይሆን፣ ሕዝቡን ራሱን ምን ያህል ወደኋላ የቀረ በማሰኘት በዓለምና በታሪክ ፊት እያስገመተ ነው። ርግጠኛ ነኝ የአኖሌ ሕዝብ የሚጠጣ ንጹህ ዉሃ፣ የሚመላለስበት ዘመናዊ መንገድና መጓጓዣ፣ በሽተኛውን የሚያስታምምበት የተደራጀ ሕክምና ቤት፣ ልጆቹን የሚያስተምርበት ማለፍያ ትምህርት-ቤትና፣ ትምህርቱንም ከጨረሰ ወዲያ የሚሰማራበት አስተማማኝ የሥራ ዘርፍ የለውም ይሆናል። የሐውልቱ ገንዘብ በተረት ላይ በተመሠረተ ድርጊት ከሚውል፣ በእነዚህ አገልግሎቶች ላይ ቢጠፋ፣ ሕዝቡን ምንኛ በጠቀመው፤ አሠሪውንስ ምንኛ ባስመሰገነው።


ድርጊቱ እውነት ቢሆንስ ሐውልት ለምን አስፈለገ። ኢጣልያኖች ሰንቱን አሩሲ፣ ስንቱን ኦሮሞ ጨርሰው የለ፤ ለምን ለዚሁ መታሰቢያ አልተሠራም። እውነቱን እንነጋገር ከተባለ፣ በኢትዮጵያ ምድር ለተሠራው ግፍ ሁሉ ሐውልት እንሥራ ከተባለ ደግሞ፣ ከብዛቱ የተነሣ እንኳን ለሰው መኖርያ፣ ለእግሩ ማሳረፍያ የሚሆን መሬት አይገኝም ይሆናል። አሩሲ ራሱ ቋንቋው ኦሮሞኛ ነው ይባል እንጂ፣ ሕዝቡ ግን ከመቶ ሰባው በትውልዱ የከምባታ፣ የሐዲያና የጒራጌ ነው። እንግዴህ በዚህ መሬት በሌላው የተፈጸመው ሳይቈጠር፣ በኦሮሞች እጅ ብቻ ያለቀውን የነዚህን ሕዝብ ቊጥር የያንዳንዱ ቤት ያውቀዋል። እንግዴህ ለነሱም ሐውልት ያስፈልጋቸዋላ። እኔ ራሴ የማወራው የግሌ ታሪክ አለኝ።


በሁለተኛው የኢጣልያን ወረራ ወቅት የኢትዮጵያ ጦር እንደተፈታ፣ በከምባታ ላይ የጐሦች ጦርነት በመባል የታወቀ ከፍተኛ ዘመቻ ተካሂዶ ሕፃንና ዐዋቂ፣ ሴትና ወንድ፣ ወጣትና ሽማግሌ ሳይለይ ብዙ ሕዝብ ዐለቀ። ከብትና ንብረት ተዘረፈ። ብዙዎች ተማርከው የደረሱበት ጠፋ። ይኸ ዐይነት ሰለባና በደል ከደረሰባቸው መካከል ቅርብ ቤተሰቦቼ ነበሩ። እናቴ ጡቷን ተቈርጣ፤ ሆዷን ተዘርጥጣ ሙታለች ተብላ እሜዳ ላይ ተጣለች። እናቷና ጫቅላ እኅቷ ግን ተማርከው ከተወስዱ በኋላ ደብዛቸው ጠፋ። ሌላው ሕፃን ወንድሟ ግን የምርኮና የጥፋት ዕጣ ባይገጥመውም አባለ-ዘሩን ተቈርጦ በሜዳ እንዲሞት ከተጣለ በኋላ በሕይወት ቢቀርም ወራሪዎቹ ጐሦች በያንዳንዱ ቤተ-ሰብና በመላው አገር ያደረሱት ዕልቂትና በደል በሰው አንደበት ተነግሮ አያልቅም ብቻ ሳይሆን የሰቀቀኑ ርዝራዥ እስካሁን ድረስ በያንዳንዱ ቤተ-ሰብና ግለ-ስብ ጆሮ ውስጥ ይጮሃል። ለዚህም ዐይነቶቹ በጐሦች ለተፈጸመ አሰቃቂ ግፍ ሐውልት ያስፈልጋል ማለት ነው።


በሥልጣን ያለው መንግሥት ከሽፍትነት ወደአፄ ምኒልክ ዙፋን ያደረስውን ዘመቻ የጀመረው ስሙን ባወረሰለት በመጀመርያ ወያኔ ትግል ላይ ተመርኲዞ ነው ይባላል። አንዳንድ ታሪክ ጸሓፊዎች ለመጀመርያው ወያኔ መነሾው በኢትዮጵያ መንግሥት የተፈጸመው ያስተዳደር ጒድለት ነው ይላሉ። እኔ ራሴ የሰማሁት ታሪክ ግን ከዚህ በጣም ይለያል። ያስተዳደር ጒድለት ማሳበቢያ ሊሆን ይችላል እንጂ፣ የመነሾው ጥንተ-መሠረቱ ግን የደጋ ትግሬው ሕዝብ ከትውልድ ሲወርድ ሲዋረድ እንደመጣው ትውፊት በዘላኑ ኅብረተ-ሰብ ላይ ያካሄድ የነበረውን የዘረፋ፣ የግድያና የጥቃት ዓመታዊ ዘመቻውን እንዲያቆም በመንግሥት ባለሥልጣኖች ስለተከለከለ ነበር። እንግዴህ ይኸ ዐይነት ዐመታዊ ዘመቻ ምን ያህል ግድያና ዕልቂት በዘላኑ ሕዝብ ላይ ለዘመናት እንዳደረሰ እናውቃለን። ዘመቻው አባትና እናት ገድሎ ብዙዎቹን ልጆች ድኃደግ እንዳደረገ፣ የስንቶቹን እናቶች ጡት እንደቈረጠ፣ ስፍር-ቊጥር የሌላቸውን ወንዶች እንደሰለበ፣ ከብትና ንብረት እንደዘረፈ፣ ሴቶችና ሕፃናት ማርኳቸው እንደወሰደ፤ በኅብረተ-ሰቡ ላይ ምን ያህል ሽብርና ፍርሀት ይፈጥር እንደነበረ፣ ስንቱንስ በጋለሞታነት እንዳስቀረ መገመት አያዳግትም። አፄ ምኒልክ ባንድ ቀን በጥቂት ሰዓት ውስጥ ፈጽመዋል የሚባለው ግፍና ጭካኔ ከዚህ በያመቱ ከሚደጋገመው ድርጊት ጋር ቢወዳደር ኢምንት ነው ማለት ይቻላል። ታዲያ ለዚህስ አረመናዊ ጭፍጨፋ ለምን ሐውልት አያስፈልግም። በዚህ የአሳብ መስመር ከቀጠልን ደግሞ በሥልጣን ያለው መንግሥት አላንዳች ምክንያት በግፍ የጨፈጨፋቸውና ያስጨፈጨፋቸው እልፍ አእላፋት ንጹሓን አሉ። ለነሱስ ለምን በየቀዬአቸው የመታሰቢያ ሐውልት አይሠራላቸውም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኦሮሞ ምሁር ሚኒልክ ሲገለፁ


በአሩሲ አፄ ምኒልክ ምን እንዳደረጉ ማወቅ ከተፈለገ አጥጋቢ ጽሑፍ ስላለን፣ በፈጠራና በስብከት ላይ መመሠረት አያስፈልግም። ጽሑፎቹ የሚያስረዱት አሩሲ ምን ያህል ለአፄ ምኒልክ እጅግ ባለውለታ እንደሆነ ነው። ነገሩም እንደዚህ ነው። አገሩን ባስገበረው በቱላማ ጦር ላይ፣ ጥቂት የአሩሲ ሰው ባንድ ባላባት ተመርቶ፣ ሌሊት ተነሥቶ ጦሩ በሠፈረበት ቦታ አደጋ ቢጥልበትና ከሺ በላይ ሠራዊት ቢፈጅበት፣ ካፄ ምኒልክ ረዳት ጦር ተላከ። ይኸ ረዳት ጦር ሌሊቱን ሲጓዝ፣ ደግሞ እንደገና ተመልሶ አደጋ ሊጥል ከሚሄደው ከአሩሲ ሰው ጋር በድንገት በመንገድ ላይ ተገናኘና በመካከላቸው በተፈጠረው ግጭት ብዙ ሰው ዐለቀ። የኦሮሞ ጦር እንደመሆኑ፣ በኅብረተ-ሰቡ ልማድ ጡት ቈርጦ፣ እጅ ጐምዶ ይሆናል። የጊዜው ልማድ ስለሆነ ምንም አይገርምም፤ ሌላው ቀርቶ በአድዋ ጦርነት እንኳን ተፈጽሟል። ደጋግሜ እንዳልኩት፣ ታሪክ መዳኘት ያለበት ከጊዜው አንፃር ነው።


የሚደነቀውና የንጉሠ-ነገሥቱ አሽማጦች የረሱት ነገር ቢኖር ግን፣ አፄ ምኒልክ እቦታው እንደደረሱ የወሰዱት እርምጃ ነው። በየትም አገር እንደሚደረገውና እንደጊዜው ልማድ መሠረት፣ ጦራቸው የማረከውን የአሩሲን ሰው ሁሉ ባርያ አድርጎ ይዞ ቢቈይባቸው፣ ንጉሡ ከፍተኛ ተቃውሟቸውን አሰሙ። ሠራዊታቸውን በሙሉ ሰብስበው፣ “አሩሲን ከግራኝ ወዲህ የገዛውና ያስገበረው የለም። እኛ ጥንትም የኛ [አገር] ነው ብለን መጣንበት እንጂ ርሱ አልመጣብንም። ባለማወቁ እከላከላለሁ ብሎ ዐለቀ፤ ተጐዳም። ግን ባርያ አድርገን ልንገዛው አይገባንም፤ ወንድማችን ነውና። የማረክኸውን የሰው ምርኮኛ ሁሉን ልቀቅልኝ። በዐዋጅ ከለመንሁህ በኋላ ወስልተህ የአሩሲን ሰው ባርያ አድርገህ የተያዝህ ከተገኘህ እጣላሃለሁ፤ ልቀቅ ብዬሃለሁና ልቀቅ።”በማለት እንዲለቅ በአዋጅ አስገደዱትና ተለቀቀ። ባገሩም ታማኝና ብቁ ነው ብለው የሚያምኑትን አስተዳዳር ሹመው ወደመናገሻቸው ተመለሱ።

ይኸንን የአፄ ምኒልክን ድርጊት ሌሎች የቅኝ ገዢዎች ከወሰዱት እርምጃ አንፃር እስኪ ከጥቂቶቹ ጋር እናስተያይ። ጀርመኖች የታንዛንያ ሕዝብ ባስተዳደራቸው ግፍ አንገፍግፎት ሸፍቶ፣ አንዲት ትንሽ ምሽግ ቢጤ ሰብሮ፣ ጥቂት ሰው ቢገድልባቸው፣ ረዳት ጦር ተልኮ ሁለት መቶ ሺ ሰው በጭካኔ ገደሉ። እንዲሁም የናምቢያ ሕዝብ በጨካኝ አስተዳደራቸው ተማርሮ በዚሁ መልክ ቢነሣባቸው፣ የተላከው ረዳት ጦር አንድም ሰው ሳይቀር እንዲገድል ታዝዞ፣ ከመቶ ሰማንያውን እጅ አረደ። የቀረው ሊያመልጥ የቻለው ወደጐረቤት መንግሥት ሸሽቶ ብቻ ነው። እንዲሁም ፈረንሳዮች የማዳጋስካር ሕዝብ ተበደልሁ ብሎ ቢነሣባቸው፣ ሰማንያ ሺውን አላንዳች ምሕረት ጨፈጨፉ። በጐረቤታችን ኬንያ እንግሊዞች በየቀኑ፣ “ዛሬ ሁለት መቶ ሻንቅላ ገደልን፤

ተጨማሪ ያንብቡ:  ደውሉ ይጮሐል!!

Page 13 of 15

ዛሬ ደግሞ ዐምስት መቶ…” እያሉ ለቅኝ ግዛት ሚኒስትር ወደለንደን የሚልኩትን መግለጫ ያነበበ፣ ስለሰው ሕይወት ነው የሚናገሩት ወይንስ ስለወፍ ብሎ መገረሙ አይቀርም።


የአሩሲ ዐይነቱ የስም ማጥፋት ዘመቻ በአፄ ምኒልክ ላይ ሲደረግ የመጀመርያው አይደለም፤ የመጨረሻም እንደማይሆን ርግጠኛ ነኝ። ዛሬ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት እንደገባ፣ ሊቅ ነጋሦ ጊዳዳ ከፍተኞች የኦሮሞ ባለሥልጣኖችን ሰብስበው፣አፄ ምኒልክ በጦር ኀይል አሸንፈው፣ የኦሮሞን ሕዝብ አላንዳች ርኅራኄ የጨፈጨፉበትና ለነፃነቱ ብዙ መሥዋዕት ከፍሎ በግፍ የተገፈፈበት ወዳሉበት ቦታ ወደጨለንቆ እየደነፉና እያጕራሩ እንደሄዱ ብዙዎቻችን ረስተን ይሆናል። እኔ በተፈጥሮዬ ከፈረንጅ ኋላ ቱስ ቱስ የሚል ሰው አልወድም። ይሁንና ሊቅ ነጋሦን ያገኘሁኋቸው ገና ተማሪ ሳለሁ በኢጣልያን አገር በሮም ከተማ በዚህ መልክ ነው። ሁናቴው ደስ ባይለኝም፣ የታሪክ ሰው መሆናቸውን ስለማውቅ፣ ላናግራቸው ብሻ፣ ፈረንጁ ጓደኛቸው በሥነ-ሥርዐቱ ሲያነጋግረኝ፣ እሳቸው ግን ሊቀርቡኝም ሊያነጋግሩኝም አልፈለጉም። ይልቅስ ያኔ ለሥልጣን እጩ ለነበረው መንግሥት በመመልመል ላይ እንደነበሩ ጓዶቻቸው ሁሉ፣ እሳቸውም ኲምሽሽ ብለው ቁመው ከሩቅ በፍራቻ በስርቆሽ ማየት እንጂ ሰላም እንኳን አላሉም። ድርጊታቸው ከቃል ይበልጥ ይናገራልና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ስለሰውዮው ያለኝ ግምት በጣም ዝቅተኛ ነበር። የጨለንቆው ጉዳይ ሲመጣ፣ ከነጭራሹኑ አዘቀጠው ብቻ ሳይሆን የታሪክ ዕውቀታቸው ምን ያህል አሳዛኝ እንደሆነም ተገለጠልኝ።
የጨለንቆ ውጊያ የተካሄደው ግብፆች ሐረርን ሲለቁ ከሾሙት ከአደሬው አሚር አብዱላሂ ጋር መሆኑን ማንም ያዉቃል። አሚሩ ያነ ቆቱ የተባለውን የሐረርጌን የኦሮሞ ገበሬ በክፉኛ ጨቁኖ የሚገዛ፣ በሐረር ከተማው ሕዝብ ራሱ ብዙ በደል በመፈጸሙ በጣም የተጠላ ብቻ ሳይሆን፣ የኢጣልያን መልእክተኞችን በጭካኔ በመግደሉ፣ አካባቢውን ይዘው የነበሩት የፈረንጆች መንግሥታት አጋጣሚውን ተጠቅመው የአሚሩን ግዛት ሊቀራመቱ በዝግጅት ላይ ነበሩ። አፄ ምኒልክ ሐረርጌ እስከዐራት መቶ ዓመት ድረስ የኢትዮጵያ ግዛት እንደነበረ አገናዝበውት ሲያበቁ፣ አሚር አብዱላሂን በሰላም እንዲገብር ቢጠይቁት፣ ከቱርክ የበለጠ መንግሥት የለም ካለ በኋላ፣ እርስዎ እስላም ከሆኑ እገብርልዎታለሁ ሲል፣ ሽርጥ፣ ጥምጥምና መስገጃ ምንጣፍ ላከላቸው። ቀጥሎም ሠራዊታቸው የገና በዓል እያከበረ ተዘናግቶ ሳለ፣ በድንገት ደርሶ የመድፍ ተኲስ ከፈተባቸው። የአፄ ምኒልክ ሠራዊት ከመ ቅጽበተ ዐይን በሚደንቅ መንገድ ተፈናጥሮ ደርሶ፣ መድፎቹን ማርኮ ቢተኲስ፣ ውጊያው ሳይታሰብ እንደጀመረ ሳይታሰብ በፍጥነት ዐለቀ። ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆነ እንጂ፣ ፍጻሜው ልክ የሮሜው ገናና የጦር መሪ የነበረው ጁልዩስ ቄሣር “መጣሁ፤ አየሁ፤ አሸነፍሁ” እንዳለው ቢጤ ነው። እንግዴህ በአካባቢው የነበሩት አውሮጳውያን እንደጻፉት፣ ሐረር “የተያዘችው አለምንም ደም መፍሰስና ዝርፍያ” ነበር። እንዳይዘረፍም በየቤቱ በራፍ የአፄ ምኒልክ ዘብ ቁሞ ይጠብቅ ነበር። አፄ ምኒልክም እንደደረሱ ሁሉም ሰው እንደባህሉና እንደሃይማኖቱ እንዲስተዳደር ማስጠንቀቂያ ሰጥተው የአሚሩን አጎቶች ሹመው ተመለሱ። ጠፍቶ የነበረው አሚር አብዱላሂ ራሱ ከተደበቀበት ወጥቶ፣ ሐረር የኢትዮጵያ አገር መሆኑን በማሳወቅ፣ “ገብቼ ልገዛ; አገርዎን አያጥፉት” ሲል ላከ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በ1ኪሎ ቁርጥ ሥጋ እና በ12 ድራፍት ብርጭቆ - እውነትና ከሕደት………(ከ ይድነቃቸው ከበደ)


እንግዴህ ሊቅ ነጋሦ ኦሮሞች ነፃነታቸውን ያጡበትና ታላቅ ዕልቂት የደረሰባቸው የሚሉት የጨለንቆ ውጊያ እውነቱ እሳቸው ከሚሉት እጅግ በጣም የራቀ ነው። ይልቅስ አፄ ምኒልክ ኦሮሞችንና ሱማሌዎችን ከጭቈና አላቅቀውአቸው ነፃ አወጥቷቸዋል፤ ሐረርጌም ከአውሮጳ ቅኝ ግዛትነት አምልጣ፣ ከዐራት መቶ ዓመት በኋላ ከናቷ ኢትዮጵያ ጋር ተቀላቀለች። የሚያሳዝነው ግን ሊቅ ነጋሦ ጊዳዳ ተራ የታሪክ ምሁር ብቻ አይደሉም። ምርምራቸውን ያካሄዱት በኢትዮጵያ ባሕር በወለጋ ውስጥ ባለው በሳዮ ኦሮሞ ላይ ከሺ ሰባት መቶ ሠላሳ እስከ ሺ ስምንት መቶ ሰማንያ ስድስት (1730-1880) ዓ.ም. የጊዜ ገደባ ውስጥ ስለነበር ከማንም ይበልጥ ስለኦሮሞ ታሪክና ውህደት እንደሚያዉቁ ይጠበቅባቸዋል። የሐረርንም ጭምር። ታዲያ የሐረር ኦሮሞ ተጨቁኖ የነበረውና ማንነቱን ያጣው፣ በአፄ ምኒልክ ሳይሆን በግብፆች ሥር መሆኑን እንኳንስ እንደሳቸው ያለው ምሁር የታሪክ ጀማሪም ያውቀዋል። የአፄ ምኒልክ አስተዳደር አብነታዊና በሁሉም ዘንድ የተወደደ እንደነበር ሌላው ቀርቶ አውሮጳውያን ባላንጦቻቸው እንደሚመሰክሩ አይተናል።


ከዚህ በላይ ባጭሩም ቢሆን እንደተገለጸው፣ አፄ ምኒልክ ያቋቋሙት ያስተዳደር ሥርዐት በዛሬ ዘመን ሲታይ ወደፈዴሬሽንነት ይጠጋል። መሠረታዊ መመዘኛው ባህልና ታሪክ እንዲሁም የሕዝቡ ምቾትና ልምድ ሲሆን፣ አንዳንዴ ሃይማኖትንም ቋንቋንም ጭምር የሚያስተናግድ ቢሆንም፣ በነኚህ መለዮች ብቻ ተወስኖ እንደመንጋ ከብት ባንድጋ አያጉራቸውም። ጐጃምና በጌምድር የሚዋስኑ አገሮች ናቸው፤ በሃይማኖትና በቋንቋ አንድ ናቸው። ሁኖም የተለየ ታሪክና ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የራሳቸው የሆነ ያስተዳደር ትውፊት ስላላቸው ልዩነታቸውን እንደያዙ ቀጥሏል። እንደዚሁም አብዛኛው የወለጋና የከፋ ሕዝብ በሃይማኖትም ሆነ በቋንቋ ተመሳሳይነት ቢኖራቸውም፣ በታሪክ፣ በባህልና ባስተዳደር የየግላቸው ስለነበሩ ልዩነታቸው እንደተጠበቀ ሁኖ ተዋቅሯል። አወቃቀሩ ማናቸውም ጤናማና እውነተኛ የፈዴሬሺን ሥርዐት ያላቸው አገሮች የተከተሉት ነው ለማለት ይቻላል። ለምሳሌ የአሜሪቃን ፈዴሬሽን የመሠረቱት ዐሥራ ሦስቱ መንግሥታት በቋንቋ፣ በትውልድ፣ በእምነትም አይለዩም። እናት አገራቸውን እንግሊዝን አሸንፈው ነፃ በወጡ ጊዜ በዐሥራ ሦስቶቹ ፈንታ በአንድ መንግሥት ብቻ መዋቀር ሲችሉ፣ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የየግላቸውን አስተዳደር ላይለቁ ብለው በፌዴሬሽን ተቋቋሙ። ሌሎችም በሠለጠኑ አገራት ያሉት በፌዴሬሽን የተዋቀሩት መንግሥታት (ለምሳሌ ያህል እንደጀርመን ያሉት) የተከተሉት መልክ ነው።


አፄ ምኒልክ ዘመናዊነትን ባገር ውስጥ ለማስገባት ያልነኩት የሥልጣኔ መስክ፣ ያላደረጉት ጥረት የለም። በያንዳንዱ መስክ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። ግን ሁሉንም በትዕግሥትና በብልሃት በመያዝ ተወጥተው አስፈላጊ መሠረቶችን በመጣል፣ ኢትዮጵያን በዘመናዊ ሥልጣኔ ተራማጅ ኀይሎች አንዷ እንድትሆን ለማድረግ በቅተዋል። በጣሉት መሠረት ላይ ማነጽና የተሻለች ኢትዮጵያ መገንባት የያንዳንዱ የተከታዩ ትውልድ አላፊነት ነው።


ደጋግሜ እንደተናገርሁት፣ አፄ ምኒልክ በተለያዩ ባላባቶች ሥር ሁኖ እርስ በርሱ ይተላለቅ የነበረውን ሕዝብ፣ ባንድ ሰንደቅ ዓለማ ሥር ሰብስበው አንድ ቤተሰብ አድርገውታል

[pdf-embedder url=”https://zehabesha.info/wp-content/uploads/2020/11/menilek-ii-great.pdf”]

21 Comments

  1. Thanks Dr for your courage to speak the truth about Menilik and the atrocities committed by OROMO invaders on other Ethiopians 400 years ago, dr you are brave man unlike AMHARA HISTORIANS who lack courage to write and speak the truth while thousands of AMHARAS being killed due to the fabricated history and propaganda propagated against AMHARAS and MENILIK

    regarding the stupid and opportunist Dr NEGASO you are right he is a history doctor however he used his knowledge of History to blame AMHARAS and Menilik this stupid doctor has the audacity to accuse MENILIK soldiers to abuse his dad 140 years ago while he was supervising the killings of thousands of AMHARAS at BEDENO, ARBABAGOGU

    Dr NEGASO knows OROMOS committed GENOCIDE on the people of ENARAYA, who used to live in his homeland or the present day of WOLLEGA he also knows Oromos are not indigenous people of ethiopia and the land they call OROMIYA

    cutting female BREAST and pennis and other human organs is typical culture of OROMOS, AMHARA people never cut a human organ in their history rather OLF OROMOS still practice cutting and slaughtering and even skinning humans and that is what they did in ARBA GOGU, BEDENO,

    WHAT IS sad is that DR NEGASO knows that there is no any historical evidence to prove the cutting of FEMALE BREAST by MENILIK except the ORAL history created by OLFites and this stupid HISTORY DOCTOR, NEGASO wants us to believe the oral history being told by OLFites as a true history kkkkk DR NEGASO would be the only historian in the world who considers ORALA HISTORY as a true history kkkk what a stupid person what a waste of Education

    DR HAILEMARIAM LAREBO YOU HAVE TO PREPARE YOURSELF THE COMING AVALANCHE OF CRITICS and INSULTS and even a DEATH TRHEAT from OLFites who wants to KILL ANYONE WHO TOLD THEM THE TRUTH that is why coward AMHARA HISTORIANS choose to keep silent but YOU ARE A HERO TO SPEAK UP THE TURTH even though YOU WILL BE THE TARGET OF OLF OROMOS to the final days of YOUR LIFE, these people would hunt and attack anyone who tell them the truth and even they threaten to kill people who writes about the crimes they committed that is why the scared AMAHRA elites and the criminals OLF who supervised and ordered the killings of thousands of AMAHRAS walk freely and even regarded us as OROMO HEROS

  2. I have just finished reading the above commentary and take off my hat to Dr. Hailemariam Larebo who is cowering those who are at the helm of power and instigating violence between two big tribe in Ethiopia, i.e., Oromo and Amhara and spreading hatred among the people.
    God bless you.

  3. dr.h/m larebo you know yourself? you know exactly your individual history of love? i think you are a person who are born with out dream in the world. because your aim is to eat,drink,sleep&think as a donkey or opposite of human being.you don’t shame yourself when you speak stupid word.that is not a history of you and your wife on bedroom.it is ahistory a biggest and best of best nations in the world.if you think before speaking,it will be best.shout again and again.but,you are nothing,you can’t change a reality. WE ARE A PROUD OF OUR HISTORY!!!!!!!!!!

  4. Kededebu woyane dros mn yitetebekal.yemigermew hzbu dedeboch yemilutn ende ewnet mewsedu new.dedeb yemisebkewn mekebel dedebnet new.tawkalachih woyane yegna andnet,hbrt hule yaschenkewal.lezihm new egnan lemaleyayet enklf yataw.please,we have to understand the evil mission of TPLF(woyane),before we going to blame any one.I am Oromo,but i never have acceped what the stupid says.minilk was the best leader of the millinium,not only 4 ethiopia but also 4 africa and the world,as history witnessed it.

  5. Thank you Dr. Hailemariam Larebo for your brilliant incisive analysis. You are a true son of Ethiopia and an intellectual with impeccable integrity. I thank you for your educative writing.

  6. Wow very interesting article. Our people need such kind of evidence particularly on this moment. Those people of the son of scorpion are polluting our people. For me it is very shame even to insult Emiye Minilik. You know why people call him like that? please ask your elders who are not poisoned by Woyane/Shabia/OLF/OPDO lies and tricks. One of very astonishing thing is that how on earth educated person believes false articles from our enemy, Tesfabis G/ebab? Leave that one, Minilik is the first king who demonstrated federalism in Africa. He was a very wise and dedicated leader, he is the one who ignite modernity in our beloved land. He is the pioneer who won the then colonialists and demonstrated for those suppressed one about freedom. He is our hero as he brought us together after long year separation due to zemene mesafint era like the one we see now. Please Minilik II is a blessed person, we don’t have mouth to speak about him. He is a man of the millennium.

    Our brothers and sisters, please don’t be fool by the stupid politicians. We are from the same blood and DNA. How can you identify the true Oromo, Amhara, Gurage, Sidama, Kembata, Tigre…Language is not a tool to make ethnic screening. Tepewuzenal just like playing card, we need to focus more on our unity and struggle against our enemies. Let’s think according to our beloved fathers and mothers, for me their action and thinking are better that the so called Drs and Professors. Because they truly demonstrated love, unity, respect, sharing, forgiveness, peace…Let our almighty shower us with love and respect. Let’s pray for those who work day and night to create bloodshed and atrocities on our innocent and God fearing peoples.

  7. If you say what happened to the Oromo at Anole is a fiction (and never happened), what makes your story an authentic one? Are you not making it up to justify your denial of the atrocities perpetrated against the Oromo? Are you not cooking sweet lies to please your Amhara masters so that they can take you to their restaurants on weekends? I assume you are educated enough to be proud of and make a good living. Not withstanding with that however, you went so low to fill your belly. You don’t have self respect and that is the worst of all sicknesses. You are brained washed enough that your education cannot heal. Woy, temro lemewared!! hililinan meshet!

    • የተደረገው ጦርነት በሀረር አሚር አይደም ካልክ በምልስረጃ አቅርብ እንጅ ሌላ ንግግር መፍትሄ የለውም

  8. Wow,you are super egoist,self actualised & humanistic person strong enough to tell the truth.I am proud of you,doctor.

  9. Why people write this kind of fiction as History? The writer never mentioned any reference or where he got all these informations.
    I read on zehabesha an article of Dr Negaso about the History of Addis Ababa supported by references and books of historians who live back then.
    But this article is not supported by any reference, Why the Zehabesha post fictions of individuals not supported by history references as a History?

  10. 10q Dr. we need people like u fair nd matured! woyana is using many ways to create ethinic difference to maintain it’s power! Fabricating stories to atack it’s rival amhara tribe, while they oppress the other tribes!

  11. Thanks Dr Larebo for the courage you have shown to speak up the truth unlike coward AMHARA elites

    Dr LArebo you might know by now how OLFites managed to suppress the truth by unleashing attacks, throwing insults and even making death threats, these SICK OLFites have the usual tactics to discredit the truth either they will call you Debtera or AMHARA slave this way they successfully silenced AMHARA Schoolars and even other scholars like you came from other Ethnics

    Preaching love as you did will infuriate OLFites and even made them go crazy as it will spoil their plan to exterminate AMHARA people

    What you just said is let’s not go back and talk about the things happened in the past as it will make our future grim and dangerous and you pointed out the truth about Menilik expansion and you challenged them the significance of the ANOLE statue they fall in love with

    OLFites know well how All States created, All states in the world created by force and expansion involved death and destruction however not only OLFites but also the History Dr Negaso does not want to acknowledge as acknowledging this will create peace between Amharas and Oromos

    For OLFites and sick people like Dr Negaso it is only Menilik who use force to create a nation that is how they teach their blind followers to incite hate towards Amharas and Menilik

    Finally I would like to ask this to OLFites and TPLF What can we Learn from The ANOLE statue in the 21 century??????????????? They claim they built the statue to learn from History kkkkkk this Hate mongers did not even know this is the 21 century, one can not standup and expand to another territory and create his own state things are different now, there are organizations like UN kkkkkk we all know the motive of erecting the ANOLE statue

    Btw as the doctor states if we started to erecting statues we have to erect statues for the Amharas and other Ethiopians killed by Oromo invaders 400 years ago especially for the people of DAMOT ENARYA etc who were victims of Oromo GENOCIDe to stop the future Genocide being planned by OLFites against Amharas

    Dr LArebo you need to be ready and thicken you skin for the all kinds of attacks and name callings from Hateful OLFites who does not want to hear the truth about their history and people who preach about peace, unity, and peaceful coexistance

  12. Dr Larebo your article is not supported by references and substantial evidences. This kind of history writing is not allowed in history proffesional writing. Can you tell us from where you got all the article you wrote?

  13. Self centered fool wanna be Dr. Haile who was fired multiple times from the university. You seems you are working for TPLF, we are done with dead Amhara built empire. They are dead and will never come back. Our mencha will be against the current one. Therefore, we forget you and look in gadaa.com for your answeres. You all will die in Washington, dreaming of one warlords kings to bring you back to power, Education never change people mind.

  14. Well done Dr.Hailemariam. We all know what happens in other worlds and what people did to control or eliminate the ‘other’ it did not happen in Ethiopia. Had it been the case they would have been successful. We all know that there was a power struggel for supermacy and sometimes that required war and killing. And as we all know every ethnic group including Oromo did that period so what? Can we settel and build a democratic society or should we go back and retaliate? Only the people behind such a mad idea of a statue knows what they are preparing. Be wise and know the history. We know that the last 20 years or so history is rewritten in Ethiopia and it is done in a nasty way but that does not justify anything because what happened is still a fact and still remains in the minds and hearts of people that share it. Beyond that it requires a bright mind to see things…I think this is one fruit of the TPLF education system…

  15. Dear readers,

    It is important to be cautious as TPLF itself either on its own or through some other individuals deliberately authors and disseminates extremely charged and controversial information to keep us divided.

    This is not the time to write such a biased, divisive and one-sided propaganda. This is a critical time for the peoples of Ethiopia to compromise their differences and stand in unison against the TPLF brutal regime. It is very worrying that some writers knowingly or unknowingly appear to be in their 19th centuries still and promote hatred and mistrust. Such things benefit only the ruling junta and not the peoples of Ethiopia. We must be cautious as to whose interest such writers are really serving – TPLF or Ethiopian people. Why do they want to take us back to controversies again and again when we try to come together and focus on TPLF?

  16. Let historians by profession alone debate on all controversial parts of our history. The self styled historians(pseudo_politicians and pseudo_historians) let them sit back and hear the verdict of the professionals if they truly want the truth to come out. Now everybody thinks as if he is expert in everything following the example of the deceased ex_pm.

  17. We expect a lot from a people who claim to be educated to write more precise articles. That is what the country lacks. In a country where the population is as diverse as it gets, and the people not experianced enough to responsibly enjoy the social media, the elites of the country can do a lot for the betterment of the country. But what we observe is people being emotional and not being based on facts. No one wants to even admit that what the other person is taking might have a grain of truth in it. Then it comes down to name calling. In politics you don’t always get what you wanted. You compromise. We must start to listen to each other and bridge the gap. We need a person with a good vision for our country. Until we start to see people who stand for facts and respect others opinion(even if we don’t accept it) we are going no where.

  18. Emye Menelik was Ethiopia’s only leader who is all couragious, generous, progresive and selfless together who installed the deep rooted unity among us even unshaken by the curren hate propganda targeting ethnicities.

Comments are closed.

Share