ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲንቅናቄ፣ ዘረኛው ወያኔ በኦሮሚያ ሕዝብና ወጣቶች ላይ እያካሄደው ያለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ፣ እስርና አፈናን በጥብቅ ይቃወማል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን ያስገነዝባል።

የአሮሚያ ወጣቶች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም የድሀ ገበሬዎች መፈናቀልን መቃወማቸው ፍትሀዊ ነው። የወያኔ “ማስተር ፕላኖች” የወያኔ የዘረፋ እቅዶች መሆናቸው በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው። ነዋሪዎቹን ያላማከረ፣ ግንባር ቀደም ባለጉዳዮችን ባለቤት ያላደረገ፣ የሕዝብ ይሁንታ ያላገኘ ማስተር ፕላን ተፈፃሚ ማድረግ አይቻልም።

ወያኔ ኦሮሚያን ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያ በምስለኔዎቹ አማካይነት እየገዛ የኢትዮጵያን ውድ ልጆች በራሳቸው ጉዳይ ባይተዋር አድርጓቸዋል። ኦህዴድ በወያኔ ቅጥረኛነት የኦሮሚያ ወጣቶችን በማስጨፍጨፍ ላይ ያለ እኩይ የአድርባዮች ስብስብ ነው።  ወጣቶች የተቃወሙት ይህንን ነው።እነዚህ ወጣቶች በአካባቢያቸው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባቸዋል። ድምፃቸው ሊሰማ ይገባል። የሌላው አካባቢም ወጣት የኦሮሚያ ገበሬ መፈናቀል ያገባዋል። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በሚደረግ ጉዳይ ሁሉ ያገባናል። በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወያኔ የራሱን እቅድ እንዲጭንብን አንፈልግም።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ አድርጎ እንዲወስድ ጥሪ ያደርጋል።  በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል የተጀመረው መፈናቀል ዛሬ አዲስ አበባ አጎራባች ከተሞች ደርሷል። በአምቦ ይህንን የተቃወሙ ወጣቶች በግፍ ተጨፍጭፈዋል፤ በሌሎች ቦታዎችም ላይ ግድያውና እስሩ በርትቷል። ወጣቱ  የጥይት እራት ሆኖ እስኪያልቅ መጠበቅ አንችልም፤ ሁሉም ትግሉን ይቀላቀል።

የወያኔ የጥቃት ሰለባ የሆኑት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይን ያነሱ ወጣቶች ብቻ  አይደሉም። በአንድ ወይም በሌላ መንገድ የወያኔን አምባገንነት የተቃወሙ በሙሉ የጥቃቱ ሰላባዎች ናቸው። ለሰልፍ ቅስቀሳ አደረጋችሁ በሚል የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ሰልፉ ተደርጎ  ካለቀ በኋላም አልተፈቱም።  ይህ ሰቆቃ ማብቃት አለበት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አደገኛ የበግ ለምድ ለባሽ ቀበሮዎችን የማይፀየፍ ትውልድ

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

3 Comments

  1. ደግሞ ግንቦት ሰባቶች ከየት ነው ብቅ ያሉት ? አይ የነርሱ ነገር …

  2. I always wonder whether the policy and direction of Ginbot 7 on various issues such as the Grand Ethiopian Renaissance Dam, its close ties with Eritrea and now in supporting fully the oromo youth struggle as part of the whole ethiopian people movement for democracy and freedom. For me this organization’s leadership is totally incompetent and lacks common sense and rational judgment towards the interest of Ethiopia and its people. Firstly, by objecting totally the construction of the GERD Ginbot7 have shown its unqualified support to Ethiopia’s number one enemies Egypt and their Arab allies. Secondly, the organization still believes by associating itself with Isayas and Shabia one day it will liberate Ethiopia from the current TPLF regime. This is a pathetic dream. The only people who would bring real change for the interest of ethiopia and its people are ethiopians themselves. From today’s Ginbot 7 statement we also realize the inability of this organization to lead a national movement. This is because the oromo youth movement is not a national struggle to establish democracy, representative government and freedom in Ethiopia. Their so called ‘movement and struggle’ led by individuals such as Jawar mohammod main aim is to make ‘ Oromia for Oromos’ and to prevent other ethiopians from participating in the over all economic and social activities of the ‘Oromia’ region. This is not a struggle for the unity of Ethiopia. And no ethiopian wish to participate in this kind of separatist and isolation movement. However, your organization is calling the Ethiopian people to support fully this Jawar Mohamod’s instigated violence the so called ‘Oromo youth movement’. This is unacceptable policy and shows your organization inability to lead. Ethiopians want to change the current regime through a ‘unified Ethiopian’ struggle and National movement not a with a narrow tribalist and ethnically based separatist violence.

  3. All Ethiopian must raise up together againest the dictatorial regime of woyane(TPLF)together.now the time is coming to end the rule of this minority junta who massacared
    1) 200 innocent children and women and young men in 1997 when rigged election and claimed they killed them when they robbed bank.
    2)400 Annuak civilian in Gambella(Genocide)
    3.) Sidama Loqee Massacre including women and children
    4)uprooted Amhara farmers from different parts of the rigon(killil) its obvious Killis leaders do not have authority to do that with out command of TPLF
    5 killed .Ambo children, women and university students and claimed also the same reason with 1997, killed when they robbed the bank.

Comments are closed.

Share