May 1, 2014
12 mins read

በቅሎን አባትህ ማን ነው? ቢሉት “አጎቴ ፈረስ ነው አለ” አሉ፤ ምንነትና ማንነት፡ የዘመኑ አንገብጋቢ ጥያቄ

ከፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም
ሚያዝያ 2006

ምጽዓት የቀረበ ይመስላል፤ ብዙ ሰዎች ሳይጠየቁ በቁሎው የተጠየቀውን ጥያቄ ራሳቸውን ጠይቀው አጎቴ ፈረስ ነው የሚለውን መልስ እየመለሱ ናቸው፤ ስለምንነታቸውና ስለማንነታቸው በውስጣቸው አንድ አስጨናቂ ነገር እንዳለባቸው ግልጽ ነው፤ የጎዶሎነት ስሜት ስለሚሰማቸው የድረሱልኝ ጥሪ በጩኸት እያሰሙ ነው፤ ግንባር ቀዳሚ መለከት ነፊም አለ፤ እውነት ግን አይደፈጠጥም፤ እየዘለለ ያፈጥባቸዋል፤ አጎቴ ፈረስ ነው ባሉ ቁጥር፣ አባትህስ እያለ ያፈጥባቸዋል! በፈረስ አጎትነት የአህያን አባትነት መደምሰስ አይቻልም፤ ነገር አፍጥጦ ከመጣ አፍጥጦ ከመግጠም የተሻለ መልስ አይገኝለትም፤ ተቅለስልሰው ሊያልፉት ሲሞክሩ በኅሊና ውስጥ ተቀርቅሮ ይደበቃል፤ ለራስም ለማኅበረሰብም ክፉና ዘላቂ በሽታ ይሆናል፤ ኢትዮጵያዊነት ማንነቱን የሚክድ ኢትዮጵያዊ ሲያቃዠው ያድራል እንጂ ፍቆ አያጠፋውም፤ አንድ ጊዜ በጀኒቫ በአንድ የአበሻ ምግብ ቤት ስበላ አንድ ዱሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዬ የነበረ የኤርትራ ተወላጅ ሲገባ ተያየን፤ እየሳቅሁ ደሞ እዚህ ምን ልታደርግ መጣህ ስለው፣ ከዚህ ማምለጥ እኮ አይቻልም፤ አለኝ፤ እንዴት ብሎ!

ምንነት ከማንነት የተለየ ነው፤ ምንነት ከማንነት ይቀድማል፤ ምንድን ነህ? የሚለው ጥያቄ ከተመለሰ በኋላ ነው ማን ነህ? መልስ የሚያስፈልገው፤ የምንነትን ጥያቄ የማያውቁ የማንነትን ጥያቄ ፍልስፍና አዋቂዎች መስለው የተውሶ ሀረጎችን ጣል ጣል እያደረጉ ተደናግረው ለማደናገር ይሞክራሉ፤ ከንቱ ድካም ነው፤ ማንነት ከምን ተነሥቶ ነው ራሱን ችሎ የሚቆመው? ራስን ሳያውቁ ሌላውን ለማወቅ መሞከር፣ ራስን ሳያሳምኑ ሌላውን ለማሳመን መሞከር፣ ያልሆኑትን ለመሆን ከመሞከር የሚቀልለው ራስን መሆን ነው፡፡

በቁሎው አባትህ ማን ነው ተብሎ ሲጠየቅ የነፍሱ ቁስል ተነክቶበታል (ለነገሩ በቁሎ ነፍስ የለውም)፤ ለዚህ ነው እያወቀ ጥያቄውን የሳተው! አሁን ሌላ ጥያቄ ሊያስፈልግ ነው፤ በቁሎው የካደው አባቱን ብቻ ነው? በአባቱ በኩል አጎቱ አህያ ነው፤ በእናቱ በኩል አጎቱ ፈረስ ነው፤በቅሎ አንግዲሀ አጎቴ ፈረስ ነው ሲል የካደው አባቱን ብቻ አይደለም።

በቁሎ አጎቴ ፈረስ ነው አለ የተባለውን ሳስብ የአባቴ ሸክሊት የምትባለዋ በቁሎ ትዝ አለችኝ፤ ማይጨው ዘምታለች! እሷ ትዝ ስትለኝ የማላውቃቸውን ወላጆችዋንም አሰብሁ፤ አንድ ወንድ አህያና አንዲት ባዝራ (ሴት ፈረስ)፤ ለመሆኑ አጎቴ ፈረስ ነው ያለው አህያ አገሩ የት ይሆን? ለመሆኑስ አጎቴ ፈረስ ነው ሲል ምን ማለቱ ነው? የሸክሊትን ዘር በአጭሩ ብናየው እንደሚከተለው ይሆናል፤–

አንደኛበቁሎው በአባቱ በኩል አንድ ወንድና አንዲት ሴት አያት አህዮች አሉት፤
ሁለተኛበቁሎውበእናቱበኩልአንድወንድናአንዲትሴትፈረስአያቶችአሉት
ሦስተኛ አባቱ፣ አህያው፣
አራተኛ እናቱ ፈረስዋ (ባዝራዋ)፣
አምስተኛ አህያ አጎትና አህያ አክስት፣
ስድስተኛ ፈረስ አጎትና ፈረስ አክስት፣

ከአንድ በቁሎ ተነሥተን ወደአንድ አህያና ወደአንድ ፈረስ ተሸጋግረን ስንት አህያና ስንት ፈረስ አዛመድን!

ስለኢትዮጵያ ሕዝብ ጎንደሬው የሲዳሞ ሰው፣ መሀንዲሱ፣ የሕግ ባለሙያው ደመቀ መታፈሪያ ያደገበትንና ያየውን በልብ-ወለድም በታሪክም እያቀነባበረ ከአርባ ዓመታት በፊት ጀምሮ ደጋግሞ ጽፎበታል፤ ብዙዎቻችን አልተማርንበትም፤ አላሰብንበትም፤ አልተወያየንበትም።

በማእከላዊ እስር ቤት፣ ከዚያም በቃሊቲ ከአንድ የወላይታ ወጣት ጋር (በአለበት ይቅናውና) ወዳጅነት ጀምረን ነበር፤ ስለወላይታ ለመማር ፈልጌ ገና ጥያቄዎችን መጠየቅ ስጀምር ወላይታ ውስጥ ብዙ ጎሣዎች መኖራቸውን ነገረኝ፤ ብዙ ነገር ለመማር ተዘጋጅቼ ሳለሁ መቼም ሁሌም በባርነት ውስጥ ስላለን እንደፈቀድን ለመሆንና እንደፈቀድን ለማድረግ አይፈቀድልንምና ለያዩን (ይለያያቸውና)፤ ያሰብሁትን ሳልፈጽም ቀረሁ፤ ቢሆንም ወላይታ ብዙ ከሌሎች የኢትዮጵያ ጎሣዎች ጋር ዝምድና ያላቸው ጎሣዎች መኖራቸውን ለመገንዘብ ችያለሁ፤ የደመቀ መታፈሪያን ሀሳብ በትንሽዋ ወላይታ ውስጥ ለማየትና ሀሳቡን ለማረጋገጥ አስችሎኛል፤ መማር ለፈለገ ቃሊቲም ትምህርት ቤት ነው።

ከብዙ ዓመታት በፊት አንድ የተምቤን ሰው ከጻፈው እንደተገነዘብሁት፣ በአንድ ዘመቻ ጊዜ ከሸዋ ከዘመተ ሰው መወለዱን በዳዊት መጽሐፍ ላይ ተጽፎለት ያገኝና የቅኔ ትምህርቱን ሲጨርስ አባቱን ፍለጋ ወደሸዋ ይመጣል፤ ቡልጋ ይደርሳል፤ እየጠየቀ የአባቱን ዘመዶች ያገኛል፤ የአባቱ ልጅ (ወንድሙ) አዲስ አበባ መሆኑ ይነገረውና አዲስ አበባ ይመጣል፤ በእንግሊዝ አገር ተምሮ የተመለሰውን ወንድሙን ያገኛል፤ ሥራ ያስገባዋል፤ የፈረንጁን ትምህርት ይማራል፤ ራሱን ችሎ ይኖራል፤ ወንድሙን ከነልጁ ደርግ ይገድለዋል፤ የተምቤኑ ተወላጅ ለሸዋው ወንድሙ ለቅሶ ይቀመጣል።

ከአንድ ሳምንት በፊት አንዲት ሴት አራት ልጆች ይዛ በአጠገቤ ስታልፍ ሳቅ ብላ አንገትዋን ሰበር አድርጋ ሰላምታ አሳየችኝ፤ አወቅኋት፤ ከአምስት ስድስት ዓመታት በፊት በዚያው በእኔ ሰፈር አካባቢ ትለምን የነበረች የመቀሌ ሴት ናት፤ በዚያን ጊዜ አርግዛ ሳያት የመጣሽው ከነባልሽ ነው ወይ ብዬ ስጠይቃት ወንድ ልጅዋ አባቱ እንዳልመጣ ነገረኝ፤ እርግዝናዋ ድንገተኛ አደጋ መሆኑን ነገረችኝ፤ በጣም ትልቅ ሆና ስለነበረ ወደሀኪም ቤት እንድትሄድ ገንዘብ ሰጠኋት፤ ከወለደች በኋላም አንድ ጓደኛዬ መሣፈሪያ ሰጣትና ወደመቀሌ ተመለሰች፤ አሁን እንደገና መጣች፤ ስጠይቃት ሁሉም ነገር ተባብሷል፤ የማዳበሪያ እያሉ ያስጨንቁናል፤ አለች፤ በይ አሁን ደግሞ ተጠንቀቂ ብዬ ተሳስቀን ተለያየን፤ ችግርም ያዛምዳል።

እንደመደምደሚያ አድርጌ ቢትወደድ አስፍሐን ላንሣ፤ ቢትወደድ አስፍሐ ለኢጣልያ ያደሩ ባንዳ ነበሩ፤ በመጨረሻም በጎንደር ላይ ኢጣልያ ድል ሲሆን ከጌታቸው ጋር ነበሩ፤ ኢጣልያኑ ጌታቸው ወደአገሩ ሲሸሽ ቢትወደድ አስፍሐን ይዞ ለመሄድ ፈልጎ ነበር፤ ቢትወደድ አስፍሐ ግን ለሁለተኛ ጊዜ አልከዳም ብለው በአገራቸው ቀሩ፤ የዱሮዎቹ ሰዎች ያላቸው ሰብአዊነትና አብሮ የመኖር ጥበብ ቢትወደድ አስፍሐን ከራስ አበበ አረጋይ ጋር አገናኛቸው፤ ታላቁ ባንዳ የትግራይ ገዢ ለነበሩት ለታላቁ አርበኛ ረዳት ሆኑ፤ ራስ አበበ ስለቢትወደድ አስፍሐ ያላቸውን አስተያየት ለማወቅ ዕድሉ አልገጠመኝም፤ ቢትወደድ አስፍሐ ስለራስ አበበ ያላቸውን አስተያየት ግን በመጠኑም ቢሆን ለማወቅ ችዬአለሁ፤ ቢትወደድ አስፍሐ ራስ አበበን በጣም ያከብሩአቸዋል፤ በጣም ያደንቁአቸዋል፤ የቢትወደድ አስፍሐ አማርኛና የኢትዮጵያ ታሪክ እውቀት ሳይተላለፍልን በመቅረቱ በጣም አዝናለሁ፤ ስለኤርትራ ‹ናጽነት› ድምጽ እንዲሰጥ ወያኔ በሚገፋፋበት ጊዜ ቢትወደድ አስፍሐ በሙሉ መንፈሳዊ ወኔ የወያኔንና የሻቢያን ጫና ተቋቁመው ኢትዮጵያዊነታቸውን አልክድም ብለው በኩራት ቆሙ፤ ባንዳው አርበኛ ሆኑ! ንስሐ ያጸዳል! ንስሐ ነጻነትን ያጎናጽፋል፤ የደበቁት ኃጢአት ግን በቀን ያቃዣል!

ባንዳና የባንዳ ልጅ ሁሉ የአርበኛ ስም ሲጠራ ያቃዠዋል! አጎቴ ፈረስ ነው! ይላል።

6 Comments

  1. Prof. As usual thank you. You are the only one person for 80 million Ethiopian.as you know the time is really dark, and when you think the future of Ethiopia it is so bad, but when I read your articles it gives me hope.

  2. when you finalise all this you get three poing
    1. yetenbenue tigre got help from his shawa brother to get job
    2. Mekel girls are all beggers and the prof. and his freinds from shawa helped her.
    3. Tigrians are banda
    We got it prof. you talk about one ethiopia but same time you are telling us one is better than the other.

  3. Mesfen Woldemariam (ex-professor)
    Hulgizie betigrai hizb be atsiew gizie yetchewetekew mina albeqa bloh ahunm tigrew banda endehone banda yebanda lij endehone geltsehal ye ahya tewuldenum tentenehal . Lemehonu professor Mesfen kehuletu kegeltskach yeywuld op ch ketgnaw wegen neh? Banda zer yelewm. Ke Amsra bandawoch neberu ke Tigraym banda nebetu keyetgnawm bhereseb banda neber. Lemagn hono yefeter woim habtam hono yemiwoled sew yelem. Neger gin adlawi ena zeregna. Balabatawi yehailesselassie mengst kufugna betedegagami tornetna yetefetro derq slateqaw tiqit sewoch lemnewal tesdewal

  4. Professor it is a good timing you wrote this interesting article in the current political atmosphere where people priority seem to focus on local and ethnic issues rather than striving for national change to bring democracy and freedom in ethiopia. The trend towards in pushing forward to narrow tribal and ethnic identity in ethiopia for the last twenty years under the current regime seem to boil over for the last few weeks in which resulted too many people deaths and injuries around the country. it’s very disappointing to see these kind of incidents in a country like ethiopia in which various ethnic groups is being lived together in piece for centuries. The focus more on ethnic and tribal identity rather than national one in the long term would endanger our unity, togetherness and may lead to a series strife among ethiopians like that of Rwanda. The only solution for this problem is to think big and live in harmony for a better ethiopia.

  5. Dedeb anten belo professor dekoro amara. Oromon lemesadeb new ahiya yemtlew lante amara new getah tegrew oromow debubu….sewoch aydelum begid beamara ethiobiawinet letddfettachew tefelgaleh betawkew ethiopiawinetm yekefa zeregnnet new!!!! Tebab selesew lij mawrat sigebah beethiopiawinet yeteshfene yeamaran yebelaynet merz lematetat tefelgaleh ahunma hulum temare ayseram!!!!!

Comments are closed.

Breking News
Previous Story

ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በተማሪዎች ተቃውሞ እየተናጠ ነው

Next Story

ሰሚ ጆሮ ያጣ የሕዝብ እሮሮና ጩኸት እስከመቼ? (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ ሌና)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop