April 21, 2014
8 mins read

ስለፍትህ ሲባል ስርዓቱ ይፍረስ! ፫ (ተመስገን ደሳለኝ)

ተመስገን ደሳለኝ)

ልዕለ ኃያሏ ሀገረ-አሜሪካን ዛሬ ለተጎናፀፈችው የሕግ የበላይነት የተከበረበት ሥርዓት መሰረት
የጣሉት እነ ቶማስ ጃፈርሰን በነፃነት አዋጃቸው ላይ ‹‹ሁሉም ሰዎች በእኩልነት የተፈጠሩ ናቸው›› በማለት
ሲደነግጉ፤ እንግሊዛዊው ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል ደግሞ “Animal Farm” በሚለው መፅሐፉ፣ ጉልበታም
‹‹ገዥ›› አድርጎ በሳላቸው ገፀ-ባሕሪያት አማካኝነት ‹‹…አንዳንድ እንስሳት (ሰዎች) ግን የበለጠ እኩል ናቸው››
ይለናል፡፡ በርግጥ ሁለቱም አይነት አስተዳደሮች መሬት ወርደው ዓለማችንን ዲሞክራት እና አምባ-ገነን
በማለት በሁለት ጎራ የከፈሉ የመሆናቸው ጉዳይ አከራካሪ አይደለም፡፡ ራሷ አሜሪካንን ጨምሮ አብዛኛው
የአውሮፓ አገራት ከሞላ ጎደል በዜጎች እኩልነት ላይ የተመሰረተ ማሕበረሰብ መገንባት ከቻሉት ውስጥ
ሲመደቡ፤ ብዙሃኑ የአፍሪካ እና የእስያ መንግስታት ደግሞ ‹‹አንዳንድ ሰዎች ይበልጥ እኩል ናቸው›› በሚል
መንፈስ የተቃኘ አገዛዝ አንብረው፣ የትኛውንም ተግዳሮት በጠብ-መንጃ ዓይን መመልከትን ፈቅደዋል፡፡ ከእነዚህኞቹ መካከል የእኛይቷ
ኢትዮጵያ ዋነኛዋ ናት፡፡
ባለፉት ሁለት አስርታት በጠቅላይነት የጨዋታ ሕግ እየተመራ፣ ከሰሜን-ደቡብ የተንሰራፋ መዋቅር መዘርጋቱ የተሳካለት ኢህአዴግ፤
የፖለቲካ ሳይንስን በአብዮታዊነት ለውጦ፣ ሀገሪቱን ለጥቂቶች የፌሽታ፣ ለብዙሃኑ የዋይታ መድረክ ሲያደረጋት አንዳች ኮሽታ
ያለመሰማቱ መነሾም ይኸው ነው፡፡ ለሕግ ከማይገዙ ፖለቲከኞች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው አንስቶ፣ በአንድ ጀንበር ሰማይ-ጠቀስ ህንፃን
እንደጓሮ አትክልት የሚያፀድቁ ‹‹አባ-መላዎች›› መበርከታቸው አስማታዊ-ጥበብ ያልሆነብንም ለዚሁ ነው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ
ትምህርታቸውን እንኳ ያላጠናቀቁ አፍላ-ወጣቶች ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ባላቸው መኪኖች መምነሽነሻቸውም ሆነ፣ ለአቅመ
አዳም ሳይደርሱ ግዙፍ የአስመጪና ላኪ ድርጅት ባለቤት ሆነው ማየታችን ይህንኑ ያስረግጥልናል፡፡
አብዮታዊ ግንባሩ ከፊተኞቹ ንጉሳዊም ሆነ ወታደራዊው አስተዳደር የሚለይበት ክፉ ገፅታዎች አሉት፡፡ ለአብነትም ከአጀንዳችን ጋር
በሚዛመደው የፍትሕ ሥርዓት ማነፃፀር ይቻላል፡፡ በአፄው ዘመን በአንፃራዊነት የሰፈነው የሕግ የበላይነት በሂደት ተንኮታኩቶ
ቢወድቅም፤ ደርግ በጎዳና ላይ የፈፀመው ዘግናኙ የቀይ ሽብር ጭፍጨፋ ምዕራፍ ከተዘጋ በኋላ ባሉት የሥልጣን ዘመናቱ፣ በእውቀት
የበቁ እና ከአድሏዊነት የራቁ ሊባሉ የሚችሉ ዳኞች እና ዐቃቢያነ-ሕግ በመሾም፣ ዛሬ ካለው የተሻለ ተቋማዊ የፍትሕ ስርዓት ለመገንባት
መሞከሩን የጊዜው መዛግብት ያወሳሉ፡፡ ከዚህ ባሻገር በሕግ ባለሞያዎች እንደመልካም ነገር የሚጠቀሰው ‹‹ጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ›› ተብሎ
አንድ ሰው ተመርጦ የሚሾምበት አሰራር ነበር፡፡ ምክንያቱም በዚህ ቦታ የሚመደብ ግለሰብ የሀገሪቱን መሪዎችን ጭምር መክሰስ
የሚችልበት ተቋማዊ ሥልጣን ያለው ከመሆኑም በላይ ‹‹አደገኛ ናቸው›› የተባሉ የህትመት ውጤቶችንም ሲያምንበት ሳይሰራጩ ቀድሞ
እስከማገድ የሚያደርስ ሥልጣን ነበረውና፡፡ ይህ አይነቱ አሰራር በምዕራባዊያን ሀገራት የተለመደ ሲሆን፤ የቀጥታ ሥርዓታዊ
ተጠያቂነትንም ስለሚያስከትል በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሕግ ለማስከበር ጠቃሚ መሆኑ በዘርፉ ምሁራንም ዘንድ የታመነበት ነው፡፡
በደርግ ዘመን (ለርዕሰ-ብሔሩ ታማኝ የመሆን ግዴታውን ሳንዘነጋ) ለክስ የሚያበቃ ማስረጃ ካገኘ፣ በየትኛውም የሥልጣን እርከን ላይ
ያለ ሹመኛን በሙሉ ፍርድ ቤት ከመገተር የማያስመልስ ሥልጣን እንደነበረው ይነገራል፡፡
ይሁንና ይህ ሁናቴ የግርንቢጥ ተመንዝሮ የፍትህ ስርዓቱን ከማፀየፍም ተሻግሮ፣ በሕግ ፊት እኩል ያልሆኑ ወይም በኦርዌላዊያን
ቋንቋ ይበልጥ እኩል የሆኑ ‹‹ዜጐች› ተበራክተው የታዩት በዘመነ-ኢህአዴግ ነው ብል ብዙም ስሁት ድምዳሜ አይሆንም፡፡ ከዓመታት
የጥምዝምዞሽ ጉዞ በኋላም የተቀደሰችዋ የፍትሕ ምኩራብ ረክሳ፣ የዜጎች መብት ተደፍጥጦ፣ ‹‹ሕገ-አራዊት›› ገንግኖ፣ ጠብ-መንጃ
መንገሱ ሊስተባበል የማይችል ሀቅ ሆኗአል፡፡
በርግጥ ከሁሉም አስከፊውና አሳሳቢው ጉዳይ የፍትሕ ሥርዓቱ ለዝግመታዊ ሞት መዳረጉ ነው፡፡ ይህንን እውነታ ፕሮፍ መስፍን
ወልደማርያም ‹‹አገቱኒ›› በተሰኘው መጽሐፋቸው የነገሩን ግላዊ ገጠመኝ በሚገባ ከማስረዳቱም ባሻገር፤ ይህን ዘመን ካለፈው ዘመን
እንድናነፃፅረው ዕድል ይሰጠናልና ልጥቀሰው፡-
“ሁለት በጣም የተለያዩ አሰራሮች አጋጥመውኛል፤ መጀመሪያ በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ተይዤ ነበር፤ በአንድ መጻሕፍት ቤት ቆሜ
ስመለከት አንድ ሰው መጣና መታወቂያውን ከአሳየኝ በኋላ መጥሪያ ወረቀት አሳየኝ፤ እንሂድ ብሎ ይዞኝ ሄደና በወንጀል ምርመራ
አንድ ክፍል ውስጥ አስገባኝ፤ ሁለተኛው በወያኔ ዘመን በ1992ና በ1998 የተያዝኩበት ነው፤ ሁለቱንም ጊዜ ከአስር እስከ አስራ አምስት
የሚሆኑ የታጠቁ ወታደሮች ነበሩ፤ በ1992 የተያዝኩት አንድ የመጻሕፍት መደብር ውስጥ ቆሜ ነበር፤ ከአስር እስከ አስራ አምስት
የሚሆኑ የታጠቁ ወታደሮች በአካባቢው ተበታትነው ለጦርነት የተዘጋጁ ሆነው ሲጠብቁ ሶስት ያህሉ በመጻሕፍት ቤቱ ገብተው
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

Previous Story

[የፋሲካ ወግ] ቴሌፎኑ ‘ለግዜው’ ጥሪ አይቀበልም – ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

Next Story

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለመምህራን የተላለፈ ጥሪ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop