April 15, 2014
7 mins read

ድምጻዊ ጎሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ) ከተሾመ አሰግድ ለወሰደው ዘፈን ይቅርታ ይጠይቅ ይሆን? ወይስ ማን አለብኝነት ያልፈዋል?


ይታየው ከሚኒያፖሊስ

ከዓመት በፊት በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 38  ነዋሪነቱ ሚኒሶታ የሆነው ስመ ጥሩው ድምጻዊ ተሾመ አሠግድ “በጠራራ ጸሐይ ተዘረፍኩ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፍረደኝ” ሲል ለዘ-ሐበሻ ጋዜጣ በሰጠው መግለጫ ላይ አስታውቆ ነበር። ካለፈቃዱ ጎሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ) የተባለው ድምጻዊ የተሾመን “የኔ አካል” ወስዶ መሥራቱን አምርሮ መቃወሙንም አንብበን ነበር። “አንድ ዘፋኝ የአንዱን ወስዶ ለሕዝብ ሲያቀርብ ባለቤቱን ማስፈቀድ ይኖርበታል” ያለው ተሾመ “ጎሲ ከ20 ዓመት በፊት የተጫወትኩትን፦ “የኔ አካል የኔው ነሽ፤ ምን አወርስሻለሁ፤ አንጀቴና ልቤን ያው ትቼልሻለሁ”” ዘፈኔን ካለፈቃድ በክሊፕ ጭምር ማውጣቱ ክፉኛ በድሎኛል” ካለ በኋላ “ድምጻዊው ጎሳዬ ቀለሙ የኔን ብቻ ሳይሆን ዘፈኑን የደረሱልኝን ገጣሚው ይልማ ገብረአብን እና የዜማ ደራሲውን አበበ መለሰን ሁሉ ተዳፍሯል። ይህንን ዘፈን በፈረንጆች በ1987 ዓ.ም አካባቢ ከነራሄል ዮሐንስ ጋር በጋራ ባወጣሁት አልበም ውስጥ ሳካትተው ግጥሙን እና ዜማውን የሰጡኝ እነርሱ ናቸው። በሙዚቃ ክሊፑ ላይ የነዚህ ስም አልተጠቀሰም። ይልቁንም የሌላ ሰው ስም በመጻፍ የኛን ሥራ የራሱ በማስመሰል አቅርቦ ሥራዬን ዘርፏል” ሲል ቅሬታውን አሰምቶ እንደነበር አንበበናል።

“ወደ ሕግ ጋር መሄዴ የማይቀር ነው። ጉዳዩን ፍርድ ቤት አድርሼ እሞግተዋለሁ” ያለው ድምጻዊ ተሾመ አሰግድ “የኔ አካል” የተሰኘውን ሥራዬን ካለፈቃዴ ተነጥቂያለሁና ከዚያ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፍረደኝ፤ በጠራራ ጸሐይ ነው የተዘረፍኩት።” በማለት የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰረቁ ዘፈኖች ሲወጡ ከኦርጂናሉ ዘፋኝ በይሁንታ መገኘቱን እና አለመገኘቱን ማረጋገጥ ይኖርበታል ሲል ጥሪውን አቅርቦ ነበር። “ድምጻዊ ጎሳዬ ቀለሞ (ጃኪ ጎሲ) የተሾመ አሰግድን ዘፈን መሥራቱን አምኖ በቪድዮ ክሊፑ ላይ ምስጋና አቅርቧል” በሚል የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ለተሾመ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።

ተሾመም “ይሄ ገሎ ማዳን ነው። ነጮጭ ሲናገሩ መጀመሪያ አቁስለውና ከዛ ለቁስሉ ማበሻ ጨርቅ ስጠው ይላሉ። ጎሳዬም ያደረገው ያ ነው። ዘፈኑን ካለፈቃዴ ወስዶ፤ ክሊፑም ከመልዕክቱ ጋር የማይገናኝ አድርጎ ሰርቶ በመጨረሻ ተሾመ አሰግድን አመሰግናለሁ ብሎ ቢጽፍ ምን ዋጋ አለው? ከገደለኝ በኋላ ማርኩህ ቢለኝ ምን ዋጋ አለው?” በማለት አምርሮ ሲናገር መስማታችን ይታወሳል።

በኢትዮጵያ ስመ-ጥር ከሆኑ ድምጻዊያን መካከል የሆነውና ብዙዎች “ኢትዮጵያዊው ስቲቭ ዎንደር” የሚሉት ተሾመ አሰግድ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በመስከረም ወር 1945 ተወልዶ በተወለደ በ5 ወሬ ዓይነ ስውር መሆኑን በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 2 ላይ በሰጠው ቃለ ምልልስ መናገሩ ይታወሳል። የመጨረሻ ካሴቱን ካወጣ 17 ዓመት ያለፈው ይህ ድምጻዊ እስካሁን ስንት ካሴቶችን ሰርተሃል በሚል ጥያቄ አቅርበንለት “ጥቂት ካሴቶችን አውጥቻለው:: ትዝታና ባቲ በሚባለው የሙዚቃ ቅኝት በፊሊፕስ አሳታሚነት በ1960ዎቹ አንድ ሸክላ አውጥቼ ነበር:: ከዛ በተረፈ ያልተሳካለት አንድ ካሴት ሰርቼ ነበር:: ከዛ ወዲህ ግን ጅቡቲ ለ5 አመታት ከቆየው በሗላ ከሮሀ ባንድ ጋር በመሆን ‘የኩባያ ወተት”ን ሰራሁኝ:: ይበልጥ ከሕዝብ ጋር ያስተዋወቀኝም ይሄ ሥራ ነው:: በሌላ በኩል ከነራሄል ዮሐንስ; አሰፉ ደባልቄ እና ኬኔዲ መንገሻ ጋር አንድ ካሴት; እንዲሁም ከማርታ አሻጋሪ; በዛወርቅ አስፋው እና ኤልያስ ተባባል ጋር በመሆን አንድ ኮሌክሽን ሰርቼ ነበር:: በራሴ በኩል 2ኛውን ሙሉ ካሴቴን “ደርባባዬ’ን አውጥቼ ነበር:: ብዙም በሕዝብ ዘንድ አልገባም:: ግን አልፎ አልፎ ሰዎች ያውቁታል::” ሲል መልሷል። 

ተሾመ ጎሳዬ ሰረቀኝ ባለው ዘፈን ዙሪያ ይህን ቢናገርም ጆሲ ሾ ላይ የቀረበው ጃኪ ጎሲ በማን አለብኝነት እንደውም ተሾመ ስለዚህ ዘፈን አያገባውም ሲል መናገሩ ይታወሳል። ጎሳዬ ቀለሙ ይህን ያለው ለደራሲው እንደገና ስለከፈልኩት ተሾመ ይህ ዘፈን የኔ ነው ብሎ መከራከር አይችልም ሲል በቲቪ መድረክ መናገሩ ይታወሳል። ይህን ያለው ሃገር ቤት ሆኖ ነበር። ዛሬ ተሾመ አሰግድ በሚኖርበት ሰሜን አሜሪካ ጎሳዬ ቀለሙ መጥቷል። ተሾመ ፈቃድ ይፈልጋል። ሆኖም ግን ጃኪ በማን አለብኝነት “ድምጻዊው የለፋበትን ሥራ አያገባውም” ሲል ተናግሯል። ጃኪ እነ ምነው ሸዋ ላይ እንዳሳየው በግትርነቱ ይቀጥል ይሆን ወይስ ተሾመ እንዳለው ወደ ሕግ በመሄድ ጃኪን በስርቆት ይከሰው ይሆን? አብረን የምናየው ይሆናል።

5 Comments

  1. The writer exaggerates the topic and he made Jacky the only person who use someone’s song and it is obvious the writer is jelous of Jacky’s success

  2. The writer of the article is overblowing the case. It looks the writer is insider of Teshome Aseged. If so, why don’t you try to mediate the case between the two?…Though I disagree with any copyright violation, please stop the smear campaign….we all know Jacky can do better than this. He’s a bright young man. Selam awerdu……

  3. Dear writer, you are very jealous or negative minded person. Either way is symptom of mental problem. If I were you I would check with psychiatrist before the illness reaches to worst. What a shame to discourage a young person in negative way. Egzer Yimarih!

  4. It seems like the editor of this website has personal problem with Jakcy. Dear Henock, why is it your website posting accusation on this rising star singer? Please refrain from this kind of silly action, you can do better than this, and your when it comes the figght aginst woyane. Whatever problem you or your clicks have with jacky try to resolve it. If not, move bro. Jealeousy is not healthy

  5. The hyphenated Azmari should ,at least, have to show respect for Teshome by admitting his deliberate fault than being adamantly deny Teshom’s right to claim.

Comments are closed.

ETH Nor
Previous Story

በኖርዌ ያሉ ኢትዮዽያውያን የወያኔን የስለላ መረብ በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

Next Story

ሰማያዊ ፓርቲ ሕዝቡ በሚያዝያ 19ኙ ሰልፍ በመውጣት የወቅቱን አሳሳቢ ጉዳይ እንዲናገር ጥሪ አቀረበ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop