May 22, 2011
1 min read

የኦሮሚያ የመሬት አስተዳደር ምክትል ኃላፊ ታሰሩ

(ሪፖርተር) የኦሮሚያ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ የክልሉ የመሬት አስተዳደርና የአካባቢ ጥበቃ ቢሮ ምክትል ኃላፊን አቶ መሐመድ ኢብራሂም ሙሳን ባለፈው ሳምንት በቁጥጥር ሥር አዋለ፡፡ የኮሚሽኑ አንድ የሥራ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኃላፊው በቁጥጥር ሥር የዋሉት በከፍተኛ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው፡፡ አቶ መሐመድ ኢብራሂም በቁጥጥር ሥር የዋሉት ባለፈው ሳምንት ዓርብ በሥራ ገበታቸው ላይ እንደነበሩ መሆኑን፣ የታሠሩትም ቡራዩ ከተማ በሚገኘው እስር ቤት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አቶ መሐመድ ቀደም ሲል ለሦስት ዓመታት ያህል የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር፣ ለአንድ ዓመት ያህል ደግሞ ኮሚሽነር ሆነው ሠርተዋል፡፡ በዚህ ዓመት መጀመርያ ደግሞ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ወደ መሬት አስተዳደር ቢሮ በኃላፊነት ተዛውረው ይሠሩ ነበር፡፡

የኦሮሚያ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ከስልሳ በላይ የተለያዩ የክልሉ ኃላፊዎችን ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ማዋሉ ይታወሳል፡፡

በቃለየሱስ በቀለ

Previous Story

Why Nigeria should worry about Ethiopia –Okala

Next Story

It's all over for Hargreaves as Ferguson confirms midfielder's exit

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop