ኢሕአዴግ በምርጫው በደረሰበት መደናገጥ የ5 ለ1 ጠርናፊዎቹን መገምገም ጀመረ

“ፓርቲው ህዝብ ለምርጫ ያልወጣው በጠርናፊዎች ድክመት
ነው የሚል አቋም ላይ ደርሷል” ውስጥ አዋቂ ምንጮች

ባለፈው ሳምንት ሚያዝያ 6 በመላው ሀገሪቱ በተካሄደው የአካባቢና የከተማ ምክር ቤት ምርጫ እጅግ ጥቂት መራጭ በመሳተፉ ኢህአዴግ ተደናግጦ ግምገማ እንደጀመረ ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ምንጮቹ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስረዱት ኢህአዴግ አንድ ለ አምስት ህዝቡን እንዲያደራጁ ያሰማራቸውን ጠርናፊዎች በግምገማ እያተራመሳቸው ነው፡፡ እንደምንጮቹ መረጃ ኢህአዴግ በመላው ሀገሪቱ የጥርነፋ መዋቅር አደራጅቷል፤ መዋቅሩ የግለሰቦችን ዝርዝር መረጃ ለደህንነት አካላት ማስተላለፍ፣ በምርጫ ወቅት ኢህአዴግ እንዲመረጥ ማስገደድ እና ፓርቲውና መንግስት ላይ የሚነሱ ተቃውሞዎችን ለመቆጣጠር ተብሎ የተደራጀ ነው፡፡ ሆኖም ባለፈው ሳምንት በተደረገው ምርጫ አንድ ለአምስት የተጠረነፈው አብዛኛው ህዝብ ለምርጫ አለመውጣቱ ኢህአዴግን አስደንግጦታል፡፡ በዚሁ ምክንያትም ጠርናፊዎቹን “የምርጫ ሰራዊት በአግባቡ አላንቀሳቀሳችሁም” በማለት ጥብቅ ግምገማ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
የፍኖተ ነፃነት የመረጃ ምንጮች እንደሚያስረዱት በተለይ በአዲስ አበባ በሁሉም ወረዳዎች ያሉት የኢህአዴግ ካድሬዎችና የህዋስ አመራሮች አንድ ለ አምስት የጠረነፏቸውን ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለአለቆቻቸው ከቃለመሀላ ጋር አስመዝግበዋል፤ ፓርቲውም ከተጠረነፈው ህዝብ መሀከል ቢያንስ 80 በመቶ እንደሚመርጠው በካድሬዎቹ
ማረጋገጫ ተሰጥቶታል፡፡ ለኢህአዴግ በደረሰው ዝርዝር መሰረት ለምርጫ ያልወጡ ተጠርናፊዎችን ዝርዝር ከፍተኛ በመሆኑ ጠርናፊዎችን መገምገም ጀምሯል፡፡ ጠርናፊዎቹና ሌሎች የኢህአዴግ ካድሬዎችም ቤት ለቤት እየዞሩ የተጠረነፉ ሰዎች ለምን እንዳልመረጡ እንዲጠይቁና እንዲያስጠነቅቁ ኢህአዴግ ትዛዝ አውርዷል፡፡
በተያያዘ ዜና ባለፈው ሳምንት በተደረገው ምርጫ በርካታ መራጮች ድምፅ ያልተሰጠበት ወረቀት ኮሮጆ ውስጥ በመክተታቸው የምርጫ አስፈፃሚዎች እየተመለከቱ ባዶ ወረቀቱ ላይ ለኢህአዴግ ምልክት እየተደረገ እንደተቆጠረና የተለያዩ የተቃውሞ መልዕክቶች የተፃፉባቸው ወረቀቶችም በብዛት መገኘታቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች ተጠናቅረው ለፍኖተ ነፃነት የረደሱ መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  "የህወሓትን ሕዝባዊ ጭፍጨፋና ከፋፋይነት እንኮንናለን፣" - በኮሎኝና አካባቢዋ የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ/ኮሚኒቲ ኮሎኝ/ጀርመን

2 Comments

  1. enie A.A(kifle ketemawin yemalteqisew) wist be mircha asfetsaminet gelelitagna tebilen eyeseran enigegn yenebere sihon, lewereda mikir bet mircha tekahido kaleqe behuala qotera sijemer be-abzagnaw malet yichalal mircha board kasqemetew yemilikit asetat wichi(widiq) yenebere new, lemisale sidboch,yenetsanet tiyaqiewoch,bado wereqetoch,meretinachihu asrabachihun yemil yibeza neber, neger gin enezihin befitsum teqebayinet yelielachewin dimitsochn beqale gubaie teyizo kalteqoteru bemil ye EPRDF cadriewoch ye mircha asfetsamiwochinina yehizb tazabiwochin enanete sergo geboch,enant yihin wereqet talachihum altalachihum ehiadieg(eprdf) endehone yimeretal bemalet bemashemaqeqim chimir wereqetochun endiniqebel bemasferarat,bemashemaqeqi kelay yeteteqesutin dimtsi alba(yeteleyayu yetsihuf meliktochin) dimitsi endalew tedergo endiqoter tedergual, bezihim saybeqa andand yehizb tazabiwoch lay beqetay eniteyayalen yemil zachana masferariya bemasemet new kadiriewochu yehiedut.

  2. why all these up and downs,giving hard time to people?there is no need election process in ETHIOPIA as long as weyane on power. everybody knows that,therefore it doesn’t matter whether the opposition got the vote or not.the election is written on the paper like the other laws.but no body apply it practicaly.so weyanes why you worry?

Comments are closed.

Share