July 22, 2024
5 mins read

እስክንድር ነጋ ይብቃው፣ ገለል ይበል

ታጋይ እስክንድር ነጋ፣ ከነአርበኛ ጋሽ ምንተስኖት ጋር ሆኖ፣ የተወሰኑ ነፍጥ የያዙ ወጣቶችን ከጎኖ አድርጎ፣ የሰጠውን መግለጫ፣ የስታሊን ገብረስላሴ ዛራ ሜዲያ ላይ አየሁት፡፡ ተደረገ የተባለው “ምርጫ” የፈጠረውን ክስተት ተከትሎ የተነሳውን ትልቅ ውዝግ በመመልከት ፣ አንዳንዶች ምን አልባት እስክንድር ነጋ ትሁት ሆኖ፣ ነገሮችን ያረጋጋል የሚል እምነት የነበራቸው አይጠፉም፡፡ ሆኖም እንደጠበቁት አልሆነም፡፡
ብቃት ያለው፣ ሃቀኛ የህዝብ መሪ፣
– 1ኛ ከራሱ ፍላጎት በፊት የህዝብን ጥቅም ያስቀድማል፡፡
– 2ኛ ችግሮች እንዳይፈጠሩ አስቀድሞ በማሰብ ጥንቃቄዎችን ያደርጋል፡፡
– 3ኛ ችግሮች ሲፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት፣ ቀዳዳዎችን ለመድፈን ቅድሚያ ሰጥቶ ይሯሯጣል፡፡ ችግሮችን ይፈታል፡፡
– 4ኛ ችግሮችና አለመስማማቶች ሲኖሩ፣ ተፈጥሯዊ ስለሆነ ይኖራልም፣ ሁሉንም አስታራቂና አሰባሳስቢ በመሆነ መልኩ መፍትሄዎችን በማምጣት፣ እመራቸዋለው የሚላቸውን ወገኖች አንድነት አስጠብቆ ይጓዛል፡፡
– 5ኛ ትግሉ ወደፊት እንዳይሄድ፣ እርሱ መሰናክልና ችግር ከሆነ፣ ወይም ከርሱ የበለጠ ትግሉን ወደፊት ሊያስኬዱ የሚችሉ ሰዎች ካሉ፣ ገለል ብሎ ቦታውን ለሌሎች ይሰጣል፡፡
እስክንድር ነጋ የራሱን ድምጽ ለራሱ ሰጥቶ፣ 5 ለ 4 ድምጽ፣ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ አሸነፍኩ ብሎ መግለጫ ሲሰጥ፣ ለተፈጠረው ቀውስና ችግር ደንታም የሰጠው አይመስልም፡፡ መግለጫው እንደወጣ በከፍተኛ ደረጃ ነው ትልቅ ውዝግብ የተነሳው። ይህ ሊያስደነግጠውና ቆም ብሎ እንዲያስብ ሊያደrገው ይገባ ነበር፡፡ በርሱ መመረጥ ዙሪያ ብዙዎች ከተቃወሙ፣ “በፋኖዎች መካከል ንትርክ መኖሩ ማንን ነው የሚያስደስትነው? ማንን ነው የሚጠቅመው ?” ብሎ መጠየቅ ነበረበት፡፡ መሪ ነኝ ሲል፣ የተቃወሙትን ለማነጋገር በመሞከር የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት መሯሯጥ ነበረበት እንጂ ሜዲያ ላይ ቀርቦ፣ የጨረባ ምርጫው ተመርጫለሁ ብሎ አብይ አህመድ እንደሚደነፋው፣ተመርጫለው ብሎ ደረቱን ነፍቶ መውጣት አልነበረበትም፡፡
እስክንድር ወደሰጠው መግለጫ ስንመጣ፣ መግለጫውን የሰጠው ሸዋ ውስጥ ሆኖ ነው፡፡ ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አንድ አመራር፣ ከጋሽ ምንተስኖት በቀር፡፡ ለእስክንድር ነጋ ድምፅ የሰጠው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ መሪ ሻለቃ መከታውን ጨምሮ፣ ሌሎች የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አመራሮችና የክፍለ ጦር አዛዦችን አላየሁም፡፡ ምን አልባት በሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ አመራሮች መካከል ነገሮችን እንደገና ለማጤን የፈለጉ ይመስላል:: ይሄ ጥሩና ተስፋ ሰጪ ምልክት ነው፡፡
ብዙ ጊዜ ጽፊያለሁ፣ እስክንድር ነጋ የመሪነት ብቃት ይለውም፡፡ ገለል ማለትና፣ በሞያው፣ በችሎታው ሊያበረክት የሚችለውን ስራ ቢሰራ ጥሩ ነው፡፡ ትግሉ የህዝብ እንደመሆኑ ግለሰቦችን ማምለክና ማግነን፣ የግለሰቦችን ተክለ ሰውነት መገንባት መቆም አለበት፡፡ የግልሰብ ተከታዮች ሳይሆን የመርህ ሰዎች መሆን አለብን፡፡ ማንም ሰው መሪ ይሁን አይሁን ጥሩ ሲሰራ፣ ጥሩ ህሳብ ሲያመጣ መደገፍ፣ ማባረታት፣ ማመስገን አስፈላጊ ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ አንድ መሪም ሆነ ሰው ስህተቶች ሲሰራ ፣ መውቀስ፣ መተቸት፣ ለማረምና ለማስተካከል መሞከር አስፈላጊ ነው፡፡ ያ ሰው አልታረም ብሎ የበለጠ ጥፋት እየፈጸመ ከሆነ ደግሞ ያንን ሰው መቃወምና መታግል ያስፈልጋል፡፡
ግርማካሳ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop