ገንቢ ፀፀትንና ልባዊ ይቅርታ መጠየቅን እየሸሸን ፈፅሞ የትም አንደርስም!

June 29, 2024
ጠገናው ጎሹ

በዚህ ሂሳዊ አስተያየቴ ከሰሞኑ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በኢትዮጵያ የአሚሪካ አምባሳደር ጋር ስለ አደረጉት ውይይት በፎቶ ግራፍ ተደግፎ የቀረበ ዜናን መነሻ ያደረገ ነው። ይህንን እንደ ምሳሌ/እንደ ማሳያ ተጠቀምኩበት እንጅ በዚህ ረገድ ያለብን ፈተና ዘርፈ ብዙና ሥር የሰደደ (wide and chronic)  የመሆኑን መሪር እውነትነት ዘንግቸው አይደለም።

በመሠረቱ  እጅግ አስከፊ በሆነ ፖለቲካ ወለድ መከራና ውርደት ወስጥ የሚጓጉጠው  (የመከራ ዶፍ ሰለባ የሆነው) ህዝብ  የሚያሳስበውና የሚቆጨው ማነኛውም ኢትዮጵያዊ በግልብም ሆነ በቡድን በየትማኛውም ጊዜና ቦታ አወንታዊ አስተዋፅኦ የማድረጉ አስፈላጊነት የሚያጠያይቀን አይመስለኝም።    ይህ ማለት  አስፈላጊና ገንቢ የሆነ ሂሳዊ  አስተያየት  (ትችት)  አያስፈልግም  ወይም ይህንን ማድረግ አላስፈላጊ ተጠራጣሪነትን እንደ ማራመድ ተደርጎ መወሰድ አለበት ማለት አይደለም።።

ከዚህ አንፃር ነው የሁለቱ  ግለሰቦች ከአሚሪካ ከፍተኛ ዲፕሎማት ጋር የመነጋገራቸውን ዜና በመልካም ዜናነት መቀበል ትክክል ቢሆንም ጥያቄ ማንሳትም ተገቢ የሚሆነው። ያለምንም ጥያቄና ሂሳዊ አስተያየት ወይም ያለምንም እንከን አልባነት ማለፍ ግን ትክክል አይሆንም። ፈፅሞ አይጠቅምም።

እንደ መግቢያ ይህንን ካልኩ ወደ ጥያቄ አዘል አስተያየቴ ልለፍ።

1) መቸም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወለድ መከራና ውርደት ያሳስበኛል ከሚል አካል/ወገን ጋር ስንነጋገር የአማራ ፋኖ እና የሌሎች የትግል ባለድርሻዎችና ተጋሪዎች  ጉዳይ መነሳቱ አይቀርምና በዚህ ረገድ ተገቢው ጥንቃቄና ፖለቲካዊ ጥበብ ሊኖረን ይገባል።ምክን ቱም  ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አደረጃጀቱና ፍኖተ ካርታው ወደ ዴሞክራሲያዊ  የአንድነት ብስራት አዋጅና የተግባር ውሎ ተሸጋግሮ ለዚህ የድል ግስጋሴው ያግዝ ዘንድ ማንዴት/ይፋዊ ሃላፊነት ካልተሰጠን በስተቀር በግል ወይም በቡድን  ደጋፊነት ከምናደርገው አስተዋፅኦ አልፈን መሄድ ያለብን አይመስለኝም። የአነዚህ ሁለት ወገኖች (የገዱና የይልቃል) የጥረት ይዘትና አቀራረብ ከዚህ አንፃር ስለ መሆኑ ወይም ስላለመሆኑ እርግጠኞች ነን ይሆን?

2) ሀ/ በተለይ ደግሞ እንደ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አይነት ከወጣትነት እስከ ባለ ግራጫ ፀጉር የእድሜ ርዝማኔ የህወሃት ኢህአዴግ እጅግ እኩይ ዓላማ  አስፈፃሚ እና ራሱን ብልፅግና ብሎ የሰየመው እጅግ ሴረኛና ጨካኝ የኦህዴድ-ኢህአዴግ ጉልቾች አንዱ በመሆን “እኛ ለሥልጣን ሳይሆን ለአገር ስንል ነው” የሚል እና የፖለቲካ ሥልጣን ከመያዝ እውነታና ወሳኝነት አንፃር ሲታይ እጅግ የወረደ ዲስኩር የደሰኮረ እና በአብይ አህመድ በቅጡ እንኳ ሳይነገረው ከወንበር ወንበር እያቀያየረ መናገር የሚችል አሻንጉሊት አድርጎ ሲገለገልበት የነበረ ሰው ሌላው ቢቀር ከምር የሆነና ገንቢነት ያለው ፀፀትና ይቅርታን ለመግለፅ የሞራል አቅም የተሳነው ምን አይነት ትርጉም ያለው ግብአትነት እንዳለው መጠየቅ በደምሳሳው ማግለል የሚሆነው እንዴት ነው? ለ/ ከምንም በፊት ከምር የሆነ ፀፀትንና ይቅርታን በግልፅ እና መሪር አስተማሪነት ባለው የፖለቲካና የሞራል ሰብእና ለመግለፅ ወኔው ከሌለን ለግዙፉና ለመሪሩ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎ አስተዋፅኦ የምናደርገው እንዴት ነው?  ሐ/ በፊትም የህወሃት እኩያን የፖለቲካ ኢሊቶችን እና በኋላም የኦህዴድ/ብልፅግና ተረኞችን እኩይ ዓላማና አጀንዳ እጅ እያወጡ በማፅደቅ እንደ ደመ ነፍስ እንስሳት ከርሳቸውን ከመሙላት ያለፈ ሚና የሌላቸው የፓርላማ አባላት (ካድሬዎች) ስብሰባ ላይ  ዘመናት ያስቆጠረውን የህዝብ መከራና ውርደት የሚያንፀባርቅ ዲስኩር ማስማትን በአወንታዊነት ማየት ተገቢ ቢሆንም እውነተኛ በሆነ ፀፀት እና ገንቢ በሆነ (ከምር አስተማሪ በሆነ ይቅርታ) ካልታጀበ በእጅጉ ጎደሎ የሆነ የፖለቲካ ሰብእና አይሆንም እንዴ? መ/ እንዲህ አይነት የፖለቲካና የሞራል ግልፅነትና ልዕልና የሚጎላቸው ወገኖች  አያድርገውና የሥርዓት ለውጥ ትግሉ ቢከሽፍና እኩያን ገዥ ቡድኖች የካድሬነት የመመለሻ በር ቢያዘጋጁ  ሰንካላና ወራዳ የሰበብ ድሪቶ እየደረቱ የመጀመሪያ ተሰላፊዎች ሊሆኑ እንደማይችሉ ምን ያህል እርግጠኞች ነን? ሠ/ የፖለቲካ ባህላችንና ታሪካችንም የዚህ አይነት አሳፋሪና መሪር ተሞክሮ ደሃ ነው እንዴ?  ረ/ ለመሆኑ እንደ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የመሰለ የእኩያን የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ፈጣሪና አስፋፊ ሥርዓትን በፍፁም ካድሬነት ከልጅነት እስከ ግራጫ ፀጉር እድሜ   አገልግሎ   በቃኝ ብሎ የተሰናበተን  ፖለቲከኛ የታሰበበት፣ የተደራጀና የተቀነባበረ፣ አካፈን አካፋ ብሎ ለመጥራት የማይገደው፣ ምን መደረግ አለበት የሚለውን ጥያቄ ቀጥተኛና ግልፅ በሆነ አቀራረብ ለመመለስ የሚችል ፣ እና እውነትም ከልብ በመፀፀት  ለነፃነትና ለፍትህ ትግሉ ጉልህ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው  የሚያሰኝ ያላሳለሰ ጥረት ሲያደርግ አላየንም/አልሰማንምና እንዲህ አይነቱን ፖለቲከኛ ምነው ብቅና ጥልቁ? ብሎ መጠየቅ ፖለቲካዊ ነውር  ነው እንዴ?

3)  ለብዙ ዓመታት በካድሬነትና በባለ ሥልጣንነት ተዘፍቀው የኖሩበትን ሥርዓት በሆነ ምክንያት ለቀው ሲወጡ ምንም ስህተት እንዳልሠሩ ያለምንም  ፀፀትና ይቅርታ ስለ ነበሩበት እኩይ የፖለቲካ ሥርዓት እንደ አዲስ ሲነግሩንና ሲተነትኑልን እኔስ/እኛስ ? ለማለት ፈፅሞ ወኔ የሌላቸው አቶ ገዱ አንዳርጋቸውንና አንዳርጋቸው ፅጌን የመሰሉ ወገኖችን በግልፅና በቀጥታ ፖለቲካዊው አመጣጣችሁና አኳኋናችሁ በእጅጉ ጎደሎ ነውና ህሊናችሁን ከምር መርምሩ ማለት  ካልቻልን ስለ የትኛው እውነተኛና ዘላቂ የነፃነትና የፍትህ  ሥርዓት ነው የምናወራው? ይህንን ከምር ወስደውና መርምረው በትክክለኛው ፍኖተ ነፃነትና ፍትህ ላይ ለመገኘት ፈቃደኞችና ዝግጁዎች የማይሆኑ ወገኖችን (ግለሰቦችን) ማባበል ግዙፍና መሪር ዋጋ የተከፈለበትንና እየተከፈለበት ያለውን መሠረታዊ የሥርዓት ለውጥ ትግል ይጎዳል እንጅ ፈፅሞ አይጠቅምም ብሎ መከራከር ትክክል ካልሆነ ሌላ ምን?

4) አንዳንድ ሁኔታዎችን (አጋጣሚዎችን) እየጠበቁና እያመቻቹ አደረግን ወይም እያደረግን ነው ለማለት ከሚያስችሉ ዜናዎችና ምስሎች (ፎቶ ግራፎች ወይም ተንቀሳቃሽ ምስሎች) ጋር ብቅና ጥልቅ ማለት ከጠቀሚታው ይልቅ አሳሳችነቱ (አዘናጊነቱ)  ያመዝናልና  ከዚህ አይነት ጋግርታም (chronically poor) የፖለቲካ ባህል ለመውጣት በግልፅና በቀጥታ መነገጋገር ይኖርብናል።

5) በዚህ ረገድ ህልውና፣ ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነት፣ ሰላምና የጋራ እድገት የሚሰፍንባትና የሚረጋገጥባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በአንፃራዊነት እጅግ አበረታችና ተስፋ ሰጭ ተጋድሎ በማካሄድ ላይ ከሚገኙት ከአማራ ፉኖዎች እና ከሌሎች የዴሞክራሲ አርበኞች ብዙ ይጠበቃል። ጋግርታሙ የፖለቲካ ባህል ማለትም የወንበር ሽሚያ፣ የአድርባይነት ደዌ፣ የጎጠኝነት አባዜ፣ በግል ኩርፊያ የአንድነት ስንጥቅን ከመድፈን ይልቅ የማስፋት፣ የግልብና የግል ስሜት ሰለባ የመሆን፣ መከራና ውርደት መቀበልን እንደ ፅድቅ መንገድ አድርጎ የማመንን (ራስን የማታለልን) ፣ የሥርዓት ለውጥ ሳይሆን የጉልቻ ለውጥ ባለ ድርሻ የመሆን  ወራዳነትን፣ በራስ ውድቀት ትግሉ ቢቀለበስ ” ፈጣሪ ባይለው ነው” የሚለውን ጨምሮ ሰንካላ የሰበብ ድሪቶ የመደረትን፣ ወዘተ  አስቀያሚ ፈተና የጊዜን ወርቃማነት እና ሌሎች የትግል ግብአቶችን ግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የፖለቲካና የወታደራዊ አንድነት ሃይልን (አደረጃጀትን) እውን በማድረግ ካላለፍነው እዚያና እዚህ የምናያቸው የብቅና ጥልቅ የፖለቲካ ጨዋታዎች ጠልፈው እንደማይጥሉን ዋስትና የለንም።

እናም ልብ ያለው ልብ ይበል!

4 Comments

  1. ገዱ አንዳርጋቸው እንዲህ ደፍሮ አልፎ ተርፎ እንዲህ ፊት ለፊት መፍትሄ እፈልጋለሁ ብሎ ይመጣል ብሎ መገመት የማይታሰብ ነበር ግና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ነው ይቻላል ለአብይ እስካደሩ። አረጋዊ በርሄ፣ቀጀላ መርዳሳ፣ሌንጮ ለታ/ባቲ፣ብርሀኑ ነጋ፣አገኘሁ ተሻገር፣ዳውድ ኢብሳ፣ጁዋር መሀመድ —- በወንጀል ፍሬ ተንደላቅቀው የሚኖሩ በመሆኑ ሊገርመን አይገባም። አቡን እንዳይወጣና እንዳይገባ በተከለከለበት የአብይ ምስራቅ አፍሪካ ገዱ መንፈስ ሁኖ ነው የወጣው ወይስ ተልእኮ አንግቦ? የብአዴን የስራ ስኬት ጅላጅል መሆንና ተዋርዶ መባረርን አስቀድሞ መቀበል ነው። ንጉሱ ጥላሁን ዛሬ ላይ በባህል ሚኒስቴር የዘበኞች አለቃ ነው ይባላል ነገ ዝመት ይባላል ቀሪውን የምናየው ነው።

  2. ወንድም ጠገናው፦
    ቸኩለን እዳናሳስትና እንዳናደናቅፍ መጠንቀቁ ደግ ነው። የሚያወራው ብዙ ቢሆንም፣ ሁሉንም ወሳኝ ባለቤት መኖሩን ማስታወስ ይገባል። ምሁራን ከ1966 ዓ.ም. ጀምሮ ግራ ቀኙን ባግባቡ ሳያዩ መቻኮላቸው ያመጣውን ውጤት ባለፉት 50 ዓመታት አይተናል። ትዕግስት ጠቃሚ ነው።

  3. The significance of Masinga, the US ambassador to Ethiopia, posing for a photo with Gedu and Yilkal cannot be overstated. It sends a powerful message: Abiy acknowledges his inability to manage Ethiopia effectively, and changes are needed.

    In parliament, only Gedu and Christian have openly criticized the boy king. Christian ended up in jail, while Gedu outmaneuvered the shenanigans Abiy’s tactics and escaped Ethiopia.

    Picture this; Over the past six years, while one Shimelis has remained in office in the Oromia region, the Amhara region has seen seven head administrations change. This suggests the boy king is manipulating the political landscape in the Amhara region.

    While Gedu needs to clarify the situation, stop hiding, and expose Abiy’s conspiracy, Fano and its supporters should leverage Gedu and similar figures to gain support from Western diplomatic networks and challenge Abiy and his cronies.

  4. May I Just once again emphasize my point of view not to have unnecessarily conversation but to be clear?
    By the way, I thank all of you for your comments/opinions which are constructively relevant to the tragic situation in our country caused by the very stupid and brutal ruling elites of ethno-centric political gambling.
    Let me say the following about the very essence of my piece :
    1) I sincerely and strongly believe that the political personality of dismembering oneself from a very horrible political system of ethno- centrism that has committed unimaginable crime on innocent citizens for about 30+ years and posturing as a genuine politician who joins the struggle for freedom and justice without a real sense of confession ( regret) and apology is nothing but a terrible self-deception as well as deception of others. I other words, If one is not at least morally courageous enough to sincerely regret and say deeply sorry for having a bloody political background, it is both politically and morally wrong.How one claim that he or she is a person of freedom and justice if he or she has no deep and serious respect for the very essence or value of admitting horrible behavior and action against peoples’ interest??? Absolutely disturbing!

    2) I argue that these guys such as Gedu Andargachew and Andargachew Tsige and others were among the terrible politicians who are not and cannot be immune from unequivocally though criticism for being parts of the most bloody politics of ethno/centrism . So, is it too much or unfair to ask them to officially and truthfully confess and apologize for what they did when they turn their backs on their old masters (bosses) and join the struggle for freedom and justice???
    3) It must be underscored that for diplomacy to holds a real meaning and be one of the means to get things changed for the better!, it must be conducted by the right person with credible or impactful political and moral standard !!! It is no simply a a matter of whoever does involve as long as he or she has acquaintance/ familiarity with others who are parts of that diplomatic affairs .
    4) I never said and will never say that people like Gedu and Andargachew must be rejected from any endeavor in the process of the struggle . What I strongly believe and say is that if we really want to bring about a real and irreversible democratic system, the very quality of those who play exemplary role must be considered seriously. It must not be whoever interested is welcome. And one of the most desirable and impactful factors in this regard is a well shaped and unshakable political and moral personalities.
    5) The political culture of not calling a spade a spade or not telling things as they are on effective and timely fashion because of the unsubstantiated fear that things will get worse is a very clumsy political argument. Why and how asking those old guards of EPRDF and so called Prosperity party who distanced/dismembered themselves to express real sense of regret and sincere apology and then be parts of the struggle for the birth of democratic country is too much or unfair???
    Thank you once again guys!

Leave a Reply

Your email address will not be published.

191614
Previous Story

ለ4ኛ ጊዜ የቀረበው አደገኛው ረቂቅ አዋጅ፤ የአዲስ አበባን ኅልውና አደጋ ላይ ወድቋል! ከጠለምት የወጡ መረጃዎች! | “ባህርዳርን መቀማታችን ነው…ሰራዊቱ አልታዛዝ ብሏል” | በሁለት ቀናት ውስጥ 30 አርሶአደሮች ተገደሉ፥ የአቶ አረጋ ከበደ ወንድም በፋኖዎች ተያዘ፥ | “እኛም ይበቃናል ለአብይ መሞት አንፈልግም” ሻለቃ |

191640
Next Story

ድንበር አቅራቢያ የተካሄደው ከባድ ውጊያ፣ የአየር መንገዱ ውል ሊፈርስ ነው፣ የመቀሌው አስፈሪ ሪፖርት፣ የእነ ደሳለኝ ጫኔ ፍጥጫ

Go toTop