October 1, 2023
2 mins read

በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በመንግስታዊ እገታ ሥር የሚገኙት እነ ክርስቲያን ታደለና ዮሐንስ ቦያለውን ጨምሮ ሌሎች የማንነት፣ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ከነገ ጀምሮ የርሃብ አድማ እንደሚያደርጉ ገለጹ፤

christian and Yohanes 1 2

christian and Yohanes 1 2እኛ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታግተን የምንገኝ የማንነት፣ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ከነገ ሰኞ መስከረም 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሚከተሉት ነጥቦች ምክንያት የርሃብ አድማ አድርገናል፡፡

  1. በአማራ ሕዝብ ላይ የተከፈተውን የዘር ፍጅት፣ ጅምላ ጭፍጨፋ እና ማንነት ተኮር ጥቃት በመቃወም፤
  2. በአማራዊ ማንነታችን ምክንያት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ታግተን የሚደርስብን የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የሕክምና እጥረት፣ የምግብ እጥረት በመቃወም፤
  3. በወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ከፍርድ ቤት እውቅና ውጭ ታግተን ለፍርድ ባለመቅረባችን፤ ለከፍተኛ የበሽታ ወረርሽኝ እንዲሁም ለከፋ የአየር ንብረት ሙቀት መጋለጣችንን በመቃወም፤
  4. በታገትንበት ካምፕ ውስጥ የሥርዓቱ ገዳይ ቡድን የሚያደርስብን የግድያ ዛቻ፣ አማራ ተኮር ስድብ፣ ማስፈራሪያና ማንቋሸሽ በመቃወም፤

በመሆኑም በእነዚህ ከላይ በጠቀስናቸውና ሌሎች ምክንያቶች የርሃብ አድማ እና መሰል እርምጃዎችን ተፈጥሯዊ መብታችንን ተጠቅመን የምንጀምር መሆኑን እየገለጽን የፍትሕ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አገራዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ተቋማት በመንግሥት ላይ ተጽዕኖ በማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡

ግልባጭ፦

ለኢሰመኮ

ለእንባ ጠባቂ ተቋም

ለመገናኛ ብዙኃን ተቋማት

ለአውሮፓ ሕብረት

ለተባበሩት መንግሥታት

384098239 6606068196138037 1527491897707228100 n

 አቤት ፍርሃት: አዲሱ የኢትዮፕያ ኪም ጆንግ ኡን

382600714 724079356426984 2208775650585417728 n 1

Leave a Reply

Your email address will not be published.

5688966979 1 1
Previous Story

ከአማራ ፋኖ፣ ከኢትዮጵያ ፋኖ፣ ይድረስ ለሎንዶን ፋኖ!!! ሚሊዮን ዘአማኑኤል (ኢት-ኢኮኖሚ)

186197
Next Story

ከባድ አደጋ ላይ ነን ግጭቱ ወደ መኮንኖች ተሸጋግሯል” አበባው አፈረጠው – “ኦሮሞዎቹ ይታጠቁ፣ ሌሎች ትጥቁን ያውርዱ” አብይ አህመድ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop