May 19, 2023
4 mins read

እምቢ ለዘረኝነት! – ገለታው ዘለቀ

182695
#image_title
ግናው የዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የእህት ልጅ!
/
የዛሬ አስር አመት ገደማ ነው። ደቡብ ኮርያ እንደነበርኩ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ወደ ደቡብ ኮርያ ይመጣል። ይህ ሰው በወቅቱ የተወሰን ሰዎች ሳንሰማ ኮርያ ውስጥ ከሚኖሩ ከአንዳንድ ኢትዮጵያውያንን ጋር ስብሰባ ለማድረግ ወስኖ ስብሰባው በታሰበው ሰዓትና ቦታ ይጀመራል። ከፍ ሲል እንዳልኳችሁ ይህንን ስብሰባ እኔ አልሰማሁም። ለግል ጉዳይ ስብሰባው ከሚካሄድበት አካባቢ እሄዳለሁ። በዚያ አንድ ኢትዮጵያዊ ወንድሜን አገኘሁ።
ይህ ወንድም ወደ ኮርያ ከመጣ ገና ጥቂት ጊዜው ነውና በደንብ አንተዋወቅም።
የሆነ ሆኖ ሰላም ከተባባልን በኋላ
 ” ዛሬ ስብሰባ እንዳለ ታውቃለህ?” ይለኛል
እኔ አላውቅም። የምን ስብሰባ? ብየ ጠየኩት
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የሆነ ሆቴል ተከራይቶ ኢትዮጵያውያንን ሊያነጋግር ነው። ስለዚህ እንሂድና ለህዝባችን ድምጽ እንሁን….. ለሃገራችን ድምጽ እንሁን…… የዚህ አገር ሚዲያዎችም ስለሚኖሩ ጉዳዩ ትኩረት ያገኛል። ለታሰሩ ወገኖች ድምጽ እንሁን…. እንሂድ ….. እንሂድ……እንሂድ…… አለኝ።
እኔም እንዲህ አይነት አክቲቪስት ሳገኝ ደስ አለኝና ሁለታችንም ተነስተን እየበረርን ከስብሰባው ቦታ ደረስን። ቀስ ብለን ከስብሰባው አዳራሽ ተቀመጥንና ስብሰባው ሲጀምር ድምጽ ማሰማት ጀመርን።
ለውጥ እንሻለን….. ለውጥ…ለውጥ …… እያልን ጮህን። የነበቀለ ገርባንና የነ እስክንድርን ስም እየጠራን ይፈቱ…… ይፈቱ…… ኢትዮጵያውያን ነጻ ይሁኑ….. የሚል ድምጽ አስተጋባን። የጸጥታ ሰዎች ከስብሰባው አስወጥተው እሲኪያሰናብቱን ጮህን።
ወደ ውጪ በፖሊሶች አማካኝነት ከወጣን በኋላ። የሆቴሉን ጊቢ ለቀን እንድንወጣ ተነገረን። በዚሁ መሰረት ጉዞ ወደ ሰፈራችን ጀመርን……
እዚህ ቪዲዮ ላይ ከእኔ ጎን ቆሞ ከፍ ባለ ድምጽ ወያኔ ዘረኛ ነው……. ዘረኛ ነው….. ዘረኛ ነው….. እያለ የሚጨኸው ትንታግ ወጣት ጋር ተያይዘን ጉዞ ቀጠልን። ከስብሰባ ስንወጣ አንድ አብሮን የነበረ ሰው አብሮን ነበርና ይህንን ትንታግ ወጣት እያየ
“ቤተሰብ ምን ይል ይሆን? አጎትህን…. ”  እያለ ያወራል።
ፈጠን ብዬ ይህንን ወደ ስብሰባ እንድሄድና ተቃውሞ እንዳሰማ የቀሰቀሰኝን ከጎኔ ሆኖ ወያኔ ዘረኛ….. እያለ ይጮህ የነበረውን ወጣት አየሁት
ምንህ ነው ዶክተር ቴድሮስ? አልኩት
አጎቴ ነው። የእናቴ ታላቅ ወንድም ነው……. ።
የውነትህን ነው?
“አዎ ትናንትናም በግል ሊያገኘኝ ልኮብኝ እምቢ ብዬው ነው። አገር እያፈረሰ ለእኔ አጎት ቢሆን ምን ይሰራልኛል ብለህ ነው? የእሱ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርነት ለእኔ ምኔም አይደለም” አለኝ። ወጣቱ ትንታጉ የቴድሮስ አድሃኖም የእህት ልጅ…………….ታሪኩ….ታሪክ ሰራ።
          እምቢ ዘረኝነት ማለት አለብን ጎበዝ። የብሄር ፖለቲካ በቃ! ኢትዮጵያውያን ልክ እንደዚህ ወጣት ዘርና ብሄር ሳይገድበን ለፍትህ ከተነሳን በርግጥ ሀገራዊ ህብረታችንን እንጠብቃለን!
# Ethiopia
ገለታው ዘለቀ

3 Comments

  1. Yes, Ethiopiawinet is a winning proposition. To get there we can fight back in any form. This days collaborating Amarawinet, Guragenet, Wolaitanet,…. should help as a tactic to get to Ethiopiawinet. If the rulers understand the new tactical opposition would bring them down soon then they need to change course and embrace Ethiopiawinet in good faith.

  2. አባ ዊርቱ የሚባሉ አንድ ጩሉሌ አደናጋሪ ነበሩ የት ጠፉ? ከዚያ አብይንና ኦሮሙማን ያጠናክራሉ ከዚህ የአንድነት ሃይሉን ያደናግራሉ ጎበዝ ነበሩ አቀራረብ ይችሉበታል ከኮሮና በኋላ ድምጻቸው ጠፋ።

  3. ገለታው ጥሩ ነገር አቅርበህልናል አሁን ማን ይሙት አንድ ትግሬ ከተቃውሞ አልፎ አጎቱን ይቃወማል ብሎ ማን ያምናል? እነ ስታሊን፤ቴዎድሮስ ጸጋዬ እንዲህ መከራቸውን የሚያዩት ለክሊክ ሰብስክራይብ ብለው አይደል ስሙኒ ለመሰብሰብ። በዚህ ትግሬ ኢትዮጵያዊ እግር ቢሆኑ ሰው አይገድሉም? ይሄ የተባለው ትግሬ ያደረገው እውነት ከሆነ ገድሉ ከዘርአይ ደረሰ ከአሉላ አባነጋ፤ ከክቡር ገ/መድህን አርአያ ከአክሱሙ ጌታችው ረዳ ጋር አብሮ ሊዘከር ይገባል። እዚህ ላይ ጌታቸው ረዳ የሚለው ስም ከራያው ጌታቸው ረዳ ጋር ሊያምታታ አይገባም የራያው ጌታቸው ረዳ ስሙንም ዜግነቱንም ሃይማኖቱንም ለሆዱ ሲል የለወጠ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Fano
Previous Story

ሙሴ፣ ሱስ፣ የዓባይ፣ ሽምግልና፣ እርቅ፣ ስልቻ ቀልቀሎ በሚሉ ማታላያዎች አማራን ማጭበርበሩ ይበቃል!

182702
Next Story

”ሰው መሆን ብቻ!”አስተርአየ ብርሃን | ”ከዋሸህ አትማል፤አንዱ ስህተት ይበቃሃል..”ተስፋሁን ከበደ | ጦቢያ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop