May 19, 2023
4 mins read

እምቢ ለዘረኝነት! – ገለታው ዘለቀ

ግናው የዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የእህት ልጅ!
/
የዛሬ አስር አመት ገደማ ነው። ደቡብ ኮርያ እንደነበርኩ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ወደ ደቡብ ኮርያ ይመጣል። ይህ ሰው በወቅቱ የተወሰን ሰዎች ሳንሰማ ኮርያ ውስጥ ከሚኖሩ ከአንዳንድ ኢትዮጵያውያንን ጋር ስብሰባ ለማድረግ ወስኖ ስብሰባው በታሰበው ሰዓትና ቦታ ይጀመራል። ከፍ ሲል እንዳልኳችሁ ይህንን ስብሰባ እኔ አልሰማሁም። ለግል ጉዳይ ስብሰባው ከሚካሄድበት አካባቢ እሄዳለሁ። በዚያ አንድ ኢትዮጵያዊ ወንድሜን አገኘሁ።
ይህ ወንድም ወደ ኮርያ ከመጣ ገና ጥቂት ጊዜው ነውና በደንብ አንተዋወቅም።
የሆነ ሆኖ ሰላም ከተባባልን በኋላ
 ” ዛሬ ስብሰባ እንዳለ ታውቃለህ?” ይለኛል
እኔ አላውቅም። የምን ስብሰባ? ብየ ጠየኩት
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የሆነ ሆቴል ተከራይቶ ኢትዮጵያውያንን ሊያነጋግር ነው። ስለዚህ እንሂድና ለህዝባችን ድምጽ እንሁን….. ለሃገራችን ድምጽ እንሁን…… የዚህ አገር ሚዲያዎችም ስለሚኖሩ ጉዳዩ ትኩረት ያገኛል። ለታሰሩ ወገኖች ድምጽ እንሁን…. እንሂድ ….. እንሂድ……እንሂድ…… አለኝ።
እኔም እንዲህ አይነት አክቲቪስት ሳገኝ ደስ አለኝና ሁለታችንም ተነስተን እየበረርን ከስብሰባው ቦታ ደረስን። ቀስ ብለን ከስብሰባው አዳራሽ ተቀመጥንና ስብሰባው ሲጀምር ድምጽ ማሰማት ጀመርን።
ለውጥ እንሻለን….. ለውጥ…ለውጥ …… እያልን ጮህን። የነበቀለ ገርባንና የነ እስክንድርን ስም እየጠራን ይፈቱ…… ይፈቱ…… ኢትዮጵያውያን ነጻ ይሁኑ….. የሚል ድምጽ አስተጋባን። የጸጥታ ሰዎች ከስብሰባው አስወጥተው እሲኪያሰናብቱን ጮህን።
ወደ ውጪ በፖሊሶች አማካኝነት ከወጣን በኋላ። የሆቴሉን ጊቢ ለቀን እንድንወጣ ተነገረን። በዚሁ መሰረት ጉዞ ወደ ሰፈራችን ጀመርን……
እዚህ ቪዲዮ ላይ ከእኔ ጎን ቆሞ ከፍ ባለ ድምጽ ወያኔ ዘረኛ ነው……. ዘረኛ ነው….. ዘረኛ ነው….. እያለ የሚጨኸው ትንታግ ወጣት ጋር ተያይዘን ጉዞ ቀጠልን። ከስብሰባ ስንወጣ አንድ አብሮን የነበረ ሰው አብሮን ነበርና ይህንን ትንታግ ወጣት እያየ
“ቤተሰብ ምን ይል ይሆን? አጎትህን…. ”  እያለ ያወራል።
ፈጠን ብዬ ይህንን ወደ ስብሰባ እንድሄድና ተቃውሞ እንዳሰማ የቀሰቀሰኝን ከጎኔ ሆኖ ወያኔ ዘረኛ….. እያለ ይጮህ የነበረውን ወጣት አየሁት
ምንህ ነው ዶክተር ቴድሮስ? አልኩት
አጎቴ ነው። የእናቴ ታላቅ ወንድም ነው……. ።
የውነትህን ነው?
“አዎ ትናንትናም በግል ሊያገኘኝ ልኮብኝ እምቢ ብዬው ነው። አገር እያፈረሰ ለእኔ አጎት ቢሆን ምን ይሰራልኛል ብለህ ነው? የእሱ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርነት ለእኔ ምኔም አይደለም” አለኝ። ወጣቱ ትንታጉ የቴድሮስ አድሃኖም የእህት ልጅ…………….ታሪኩ….ታሪክ ሰራ።
          እምቢ ዘረኝነት ማለት አለብን ጎበዝ። የብሄር ፖለቲካ በቃ! ኢትዮጵያውያን ልክ እንደዚህ ወጣት ዘርና ብሄር ሳይገድበን ለፍትህ ከተነሳን በርግጥ ሀገራዊ ህብረታችንን እንጠብቃለን!
# Ethiopia
ገለታው ዘለቀ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop