May 9, 2023
5 mins read

ካልተስማሙ የምናዉቀዉ ቀደም ሲል በነበረዉ አቋም ላይ መሆናቸዉን ነዉ

abiy geday

ከሰሞኑ በኢአሀዴግ እና በኦነግ የጦር ተፋላሚዎች ጋር በታንዘኒያ አገር በምትገኝ አገር ለቀናት ተካሂዶ ያለምንም ስምምነት መቋጨቱን እና ይህም ለቀጣይ ጊዜ በይደር መያዙን ይሰማል ፡፡

ሰማን ለማለት ከልምድ መቀበል ስለሚያስቸግር እና ግልፅነት ያለዉ ይፋዉ የመረጃ ልዉዉጥ በአገራችን ባለመለመዱ ነዉ ፡፡

ይሁንና ከአራት ዓመት በፊት ኤርትራ ከነበረዉ ኦነግ ዉስጥ የገጠሩ ክንፍ ከነሙሉ ትትጥቁ  መግባቱ እና ይህም አድማሱን በማስፋት ከምዕራብ ኢትዮጵያ አስከ መኃል አገር መዛመቱን ይነገራል ፡፡

በተጨባጭ እየደረሰ ባለዉ ሠባዊ እና ቁሳዊ ጥቃት እና ዉድመት የተነሳ ንግግር አስፈላጊ መሆኑ እና የሁሉም ሠባዊ ፍጡር ፍላጎት ቢሆንም ስምምነቱ ስለመካሄዱም ሆነ ስለዉጤቱ መተማመን የሚያስችል ስለመሆኑ ተከድኖ ይብሰል ፡፡

ለመሆኑ በሰላማዊ መንገድ መብታቸዉን ፣ ህልዉናቸዉን እና አገራቸዉን ለመከላከል ከፍተኛ ዋጋ የለፈሉትን ኢትዮጵያዉያንን በመዘንጋት እና በተለያየ መንገድ በመጉዳት በመጠመድ ከዚህ በተቃራኒ አስቀድሞ ከነሙሉ ትጥቅ ወደ አገር ቤት የገባን ኃይል  በስምምነት ተቀብሎ ዛሬ ኢህአዴግ ለመስማማት ቢራመድ ሰዶ ማሳደድ እና እንዲሁም የፖለቲካ ስልጣን ጉዳይ ካልሆነ የአገር እና የህዝብ ጉዳይ መሆኑ ሌላዉ ተጠባቂ እና ተጠያቂ ወቅታዊ ጉዳይ ነዉ ፡፡

ለዓመታት እንደ ጂረት የሚወርደዉ የዜጎች ዕንባ እና ደም ሲፈስ ፣ ህዝብ ሲፈናቀል ፤ ዜጋ ሲበደል ፣ ፍትህ ሲጓደል አንድም ስለ ህዝብ እና አገር ለመናገር ሀነ ለመዘከር ፍላጎት የሚያሳይ አካል ባለመኖሩ

ዛሬ ላይ ከብሄራዊ ደህንነት እና የህዝብ አንድነት ስም ድርድር ማለት በአሁኑ ጊዜ ለብሄራዊ አንድነት  ቀናኢ ከሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የዓማራ  ህዝብ እና የዓማራ ብሄራዊ ነፃነት ትግል (አብነት) ኃይሎች ላይ በአገራዊ አንድነት እና ሉዓላዊነት ላይ መታማት  ከተለያዩ ኃይሎች ጋር ለሰላም እና ለአገራዊ አንድነት ስለመሆኑ አጠያያቂ መሆኑ ከግምት በላይ ዕዉነት መሆኑን የሚጠራጠር ቢኖር በዕዉነት የማይኖር ነዉ ፡፡

በብዕር እና በተግባር የሚሞግቱ ጉምቱ ኢትዮጵያዉያን በሚገፉበት ምድር ሳይረራቁ የሚታረቁ  ስምምነት ላይ መድረስ አለመድረሳቸዉ ይቆይ እና በቀደመዉ ስምምነታቸዉ ላይ ምን ተካቷል የሚለዉን መጠርጠር ሳይሻል አይቀርም ፡፡

በታንዛኒያዉ የኢህአዴግ እና የኦነግ ወታደራዊ  ክንፍ  ጋር ታንዛንያ ላይ የተካሄደዉ ንግግር የቀደመዉን የአስመራ ስምምነት ለማደስ እና በአገሪቷ ላይ ለደረሰዉ የሠላሳ ዓመታት ሠባዊ እና ቁሳዊ ጥፋት ተጠያቂዉ ማን ይሁን የሚለዉን አሁንም ቢብራራ እና ህዝብ እንዲያዉቀዉ ቢሆን በጎ ነገር ነበር ፡፡

እናም ሆድ ሲያዉቅ ዶሮ ማታ  እንዲሉ አለመስማማት የሚለዉን ይቅር እና የተስማሙበትን ሁለቱ “ተስማመተዉ ያልተስማሙበትን ነገር “ ስለ አገር እና ህዝብ ቢናገሩ ፤ቢኖሩ ሁሉም ደስ ይሰኛል ፡፡

 

አንድነት ኃይል ነዉ !

 

Allen

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop