May 3, 2023
7 mins read

የህዝብ መንቃት እና መደራጀት  ለብሄራዊ አንድነት እና ደህንነት አብነት ነዉ

344693413 147241198163670 3681649681900627043 n 1 1 1

የኢትዮጵያ ህዝብ በቅንት እና በአርቆ አሳቢነት ከብሄራዊ ጥቅም እና ስም አኳያ አስቀድሞ የሚያስተባብረዉ ፣ የሚያስተሳስረዉ ፣የሚያደራጀዉ እና የሚመራዉ ኃይል ከፊት ባለመኖሩ ከዚህ ይልቅ በተቃራኒ ከጀርባ በማድፈጥ በመከራ ጊዜ የሚደበቁ ፤በፍስኃ ዘመን አገር እና ህዝብ በችግር  ወላፈን ሲፈተኑ የደረሱትን የክፉ ቀን ደራሾችን ሲያናንቁ እና ሲሳለቁ ማየት ዛሬም እንደጥንቱ ማየት የተለመደ ሆኗል ፡፡

በተለይም የዓለም ጥቁር ህዝቦች በዘረኞች እና በቅኝ ግዛት ናፋቂዎች በባርነት እና በቅኝ ግዛት ቀንበር ጫና በነበሩበት ዘመን ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት መዳፍ ለማስግባት ከሚተጉት የ9ኛዉ ክ/ዘመን ተስፋፊዎች መካከል ኢጣሊያ ለሰሜን እና ምስራቅ አፍሪካ የቅኝ ግዛት ቅርምት ሲታደላት በድጋሚ በተደረገ የ40 ዓመት ዝግጂት የቅኝ ግዛት ጦርነት እና ወረራ ዕግሬ አዉጭኝ ያሉት የዘመኑ ሹማምነት በአገኙት ቀዳዳ ወደ ድሎት እና ስደት አገር ሲኮበልሉ ከህዝብ እና አገር ጋር በፊዉታራሪነት የተዋደቁት ዕዉነተኛ ቁርጥ ቀን የህዝብ ልጆች ነበሩ ፡፡

ይሁንና ከ፭ ዓመት የነፃነት ተጋድሎ በኋላ የድል ብስራት በተነገረበት ማግስት የድል አጥቢያ ጀግና መሳይ እና የኢትዮጵያዉያንን ነፃነት እና የብሄራዊ ልዑላዊ ክብር የሽ ዘመናት ታፍሮ እና ተከብሮ መኖር የማይዋጥላቸዉ የዉጭ እና የዉሥጥ ከኃዲዎች በጨነቀ ጊዜ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከህዝብ ፊት በመሆን አገሪቷን ፣ ህዝቧን እና የዘመኑን ሹማምንት ለአገራቸዉ እንዲበቁ ያደረጉትን የዚያ ዘመን የነፃነት ፋና ወጊዎች በተለያየ ሁኔታ በደል  እና መገለል ደርሶባቸዋል ፡፡

ይህም ኢትዮጵያ ለሞቱላት  የምታቃጥል ረመጥ ዕሳት ፤ ለገደሏት በረከት ሆና እንትቀጥል እና በራስ መተማመን እንዳይኖር ከፍተኛ ሴራ ተሰርቷል፡፡

ይህም ረብ የለሽ በሆነ እና የበሬ ግንባር በማይሆን የባድመ መሬት በተደረገ የዕናት እና ልጂ ( ኢትዮጵያ እና ልጂ ( ኢትዮጵያ እና ኤርትራ)  የአንድ ህዝብ ጦርነት በትንሹ ፸ ሽ ኢትዮጵያዉያን ደም መፍሰስ እና ህይወት መጥፋት ምክነያት ሆኖ ለስልጣን ናፋቂዎች ዕድሜ ማራዘሚያ በማድረግ የዚህ ህዝብ መስዋዕት ደመ ከልብ ሆኗል ፡፡

ይህ ሳይበቃ በብሄራዊ አንድነት እና ሉዓላዊነት ስሜት በዚሁ በሴራ በታጀለ ጦርነት ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉት እና ከሞት ለተረፉት  የቁርጥ ቀን ልጆች በተለይም የዓማራ ህዝብ ተወላጆች ሹመት እና ሽልማት ሲገባ ክህደት እና ዉርደት ተፈፅሟል ፡፡

ይህ ለ ፫ ጊዜ በሁለት ሽ አስራ ሶስት ዓ.ም. ኢትዮጵያን ለማፍረስ እና የዓማራን ህዝብ ለመዉረር በህዎኃት የተደረገዉ የወረራ ሴራ መሰረት ከወረራ ባሻገር የህልዉና ጉዳይ ወደ መሆን በመድረሱ የዓማራ ህዝብ እና ቁርጠኛ የህዝብ  ልጆች ባደረጉት ከፍተኛ የሞት ሽረት ትግል ተደርጓል ፡፡

በዚህም ከፍተኛ የድል ዉጤት አገርን እና ትዉልድ ከጥፋት እና ሞት የማዳን ተግባር ተከናዉኖ የብዙዎች ህይወት ዕልፈት እና አካል ጉዳት ፣ የንብረት እና ሀብት ጥፋት ተስተናግዷል፡፡

ሆኖም ለአገር እና ለህዝብ ዋጋ መክፈል ወንጀል የሚሆንበት የሰሜን ምዕራብ እና መኃል ኢትዮጵያ ህዝቦች አመድ አፋሽ ሆኖ በሰላም ስም ጦርነት ተከፍቶበታል፡፡

ይህ ሁሉ በኢትዮጵያዉያን ፣ዓማራ ላይ የሚደረግ የጠላት ሴራ  ኢትዮጵያን ለጥፋት እና ህዝቡነ  ለባርነት ቀንበር ለመዳረግ ተደጋጋሚ የክህደት ተፈፅሟል፡፡

ለዚህም ኢትዮጵያን ሆነ  ኢትዮጵያዉያን ከጥፋት እና ከተደጋጋሚ ጥቃት ለመታደግ የሚያስችል ህዝባዊ እና ብሄራዊ ልባዊ አደረጃጀት እና ሁነኛ አመራር ባለመኖሩ ነዉ ፡፡

ዛሬም ቢሆን የዓማራ ህዝብ ህልዉና የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት እና የዜጎች ደህንነት  ዋስትና ሊሆን የሚችለዉ የዓማራ ህዝብ  የህልዉና እና ነፃነት ትግል የኃይል ሚዛን በዕዉን መኖር እና መረጋገጥ አለበት ፡፡

ለዚህም የኢትዮጵ የቀደመ የዘመናት ታሪክ እና ታላቅነት ለማስጠበቅ  እና ለማስቀጠል የዓማራ ህዝብ በመደረጃት ለራሱ እና ለኢትዮጵያ ህልዉና መደራጀት እና ለነፃነቱ ዘብ መቆም  አለበት ፡፡

በዚህ ረገድ የዓማራ ብሄራዊ ነፃነት ትግል ” አብነት ” መቋቋም እና መኖር በዚህም ወቅቱን የዋጀ የኃይል አሰላለፍ አስካልተፈጠረ ድረስ ላለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት የነበረዉ መከራ እና የኢትዮጵያዉያን  ሉዓላዊነት ጉዳይ ወደ ተበባሰ ደረጃ የሚያመራ መሆኑን መገንዘብ ያሻል፡፡

ኢትዮጵያ ያለ ኢትዮጵያዉያን ባዶ እና ንብ አልባ ቀፎ እንደሆነ ስለሚቆጠር ኢትዮጵያዉያንን ማሳደድ የመጨረሻዉ የክ/ዘመናችን መከካድ ከመሆን ዉጭ ሌላ ሊሆን አይችልም ፡፡

 

Allen .A

Unity is power and Power is everything!

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

Go toTop