ያቶ ኤርምያስ ለገሰና የመሰሎቹ ቅጥፈት፣ እውን አማራ ዘረኛ ነው?

#image_title

ጭራቅ አሕመድ የገደለውን ግርማ የሺጥላን አማራ ገደለው ለማስባል፣ አቶ ኤርምያስ ለገሰና መሰሎቹ ግለሰቡ የተገደለው አባቱ ወይም አያቱ ኦሮሞ ናችው እየተባለ ስለሚታማ ነው እያሉ አማራን ዘረኛ ለማስባል ከፍተኛ ዘመቻ ከፍተዋል፡፡  ስለዚህም፣ እውን አማራ ዘረኛ ነው ብሎ መጠየቅ የግድ ነው፡፡

በመሠረቱ አንድን ብሔር እንዲህ ነው እንዲያ ነው ብሎ በጥቅሉ መፈረጅ ትልቅ ስህተት ነው፡፡  ብሔርን በጅምላ መውቀስ ወይም መከሰስ ከተቻለ ግን፣ ከጦቢያ ብሔሮች ውስጥ በዘረኝነት ለመወቀስ ወይም ለመከሰስ የመጨረሻው የሚሆነው አማራ ነው፡፡

ትግሬ በመጀመርያ የሚመለከተውና የሚጠይቀው ትግሬ መሆንን ነው፡፡  ለምሳሌ ያህል አማራ ነው የሚባለው ጌታቸው ረዳ ለወያኔ ያደረገው ማናቸውም ትግሬ ነው የሚባል ሰው ለወያኔ ካደረገው የበለጠ ቢሆንም፣ ጌታቸውን በተመለከት ግን ትግሬወች በመጀመርያ የሚመለከቱት ትግሬ አለመሆኑን ነው፡፡  በወያኔ ላይ የሚደርስን ማናቸውንም ጉዳት የሚያሳብቡት ደግሞ በጌታቸው አማራ መሆን ነው፡፡  በተመሳሳይ መንገድ ኦሮሞም በመጀመርያ የሚመለከተውና የሚጠይቀው ኦሮሞ መሆንን ነው፡፡

በሌላ በኩል ግን ያማራ ሕዝብ ያንድን ሰው አማራነት መጠየቅ የሚጀምረው ፀራማራ ንግግሮችን ሲናገር ወይም ደግሞ ፀራማራ ድርጊቶችን ሲፈጽም ሲመለከተው ብቻ ነው፡፡  ግርማ የሺጥላ ለኦነጋውያን አድሮ አማራን ባይጨፈጭፍና ባያስጨፍጨፍ ኖሮ አሮሞ ይሆን ወይ የሚለውን ጥያቄ የሚጠይቅ አማራ ባለነበረ ነበር፡፡

ጭራቅ አሕመድ ስልጣን ሲይዝ ትግሬ አልደገፈውም፣ የተመለከተው ኦሮሞ መሆኑን ነውና፡፡  ኦሮሞም አልደገፈውም የተመለከተው አማራ ናት ከምትባል ሴት ጋር መጋባቱንና እናቱ አማራ ናቸው መባሉን ነውና፡፡  አማራ ግን ጭራቅ አሕመድ ኦሮሞ ነው የሚባለውን ሙሉ በሙሉ አምኖ ተቀብሎ ሙሉ በሙሉ ደግፎት ነበር፣ የተመለከተው ኦሮሞነቱን ሳይሆን ኢትዮጵያን እወዳለሁ ማለቱን ብቻ ነበርና፡፡  የአማራ ሕዝብ የጭራቅ አሕመድን ኦሮሞነት መመልከት የጀመረው የኦነግን ዓላማ የሚያራምድ አማራ ጨፍጫፊና አስጨፍጫፊ ጭራቅ መሆኑ መረዳት ሲጀምር ብቻ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የወጣት ተስፋዬ ተካልኝ የ23 ወራት ‘አጥንት የሚሰብር፤ ዘር የሚያመክን’ የግፍ እስርና ግርፋት ሲዖል

አቶ ኤርምያስ ለገሰንም የኦሮሞና የትግሬ ጽንፈኞች ሲያብጠለጥሉት፣ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ሲደግፉት የነበሩት አማሮች ነበሩ፣ ትኩረታችው በማንነቱ ላይ ሳይሆን በምግባሩ ላይ ነበርና፡፡  እነዚህ አማሮች ያቶ ኤርምያስ ለገሰን ኦሮሞነት መጠርጠር የጀመሩት “አማራ፣ አማራ አትበሉኝ” ማለት ከጀመረ በኋላ ነው፡፡

በነገራቸን ላይ ባሁኑ ጊዜ ኦሮሞ ነው ከሚባለው ውስጥ ከዘጠና በመቶው በላይ ኦሮሞ ያለሆነ፣ በሞጋሳና በጉዲፈቻ ማንነቱን እንዲያጣ የተደረገ ስለሆነ፣ ያቶ ኤርምያስ ለገስ አያት ዋቅጅራ ስለተባሉ ብቻ አቶ ኤርምያስ ኦሮሞ ነው ማለት አይደለም፣ ያቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያት ቂጢሳ ስለተባሉ ብቻ አቶ አንዳርጋቸው ኦሮሞ ነው ማለት እንዳለሆነ፡፡

 

በጦቢያ ምድር ላይ ከጣና እስከ ጫሞ፣ በኦሮምኛ ቃል ያለ ተሰይሞ

ከመስፋፋት በፊት ሁሉም አስቀድሞ፣ አይደለም ኦሮሞ ወይም የኦሮሞ፡፡

በስሙ ኦሮሞ ከሆነው ሕዝብ ላይ፣ ዘጠና በመቶ ወይም ከዚያ በላይ

በደሙ ያይደለ ብሔሩን የረሳ፣ ወይ ጉዲፈቻ ነው አለያም ሞጋሳ፡፡

 

አሮሞን በዚህ እይታ ስንመለከተው ምናልባትም በጦቢያ ውስጥ ከሚገኙት ሕዳጣን ብሔረሰቦች የመጨረሻው አናሳ ነው፡፡  ኬኛነቱን ሙጥኝ ብሎ ማንንም የማላስኖርበት፣ የኔ የራሴ፣ የግሌ ክልል ይኑረኝ ካለ ደግሞ ነገሌ ቦረናም እጅግ ሲበዛበት ነው፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

3 Comments

  1. አይ ኤርምያስ አሁንስ እኛንም አዋረድከን ያንተው ሰዎች ጥምብ እርኩስህን ሲያወጡት አይሆንም ብለን ላንተ እንዳልቆሰልን እንዳልተዋደቅን ሁሉ ዛሬ ላይ እንጀራህን በሰው ደም ላይ አደረከው? አይ ክፉ አመል በል ወንድሜ አትወጣውም ነብስህ እንደባዘነች ትኖራለች ቀደም ሲል ግምቦት 7 ጋር ተናንቀህ አይሆንም ዜጋ ነው ብለን በዜግነትህ ብቻ ካንተ ዘንድ ቆምን ኦሮሞዎችም ሲያዋክቡህ እንደዛው ዛሬ የያዘህ አልለቅ ብሎህ የግርማ የሽጥላን ግድያ ኦሮሞና አማራ ብለህ ለየኸው? እንግዲህ ማንኛውንም ነገር በኦሮሞና በአማራ ከለየኸው ልጅህን ስትቆጣውም አንተ አማራ ብለህ ስደበው። ያሰብከውን አታገኝም እንደባከንክ ተለጥጠህ መጨረሻህ ይሆናል ሃሳብ አልቆብሃል የስድብ ዲያሪ አዘጋጅ።

  2. ፕሮፍ መቼም ካንተ አናውቅም ብርሃኑ ጁላ የከምባታና ሃድያ ሰው ነው በሞጋሳ ኦሮሞ የሆነው በመጨረሻው ሉባ ነው ነጋሶ ጊዳዳም እንዲሁ የበቀለ ገርባ ስሙ ይናገራል አሁን እሱና ጅዋር በምናቸው ነው ሌጮንና ዳውድ ኢብሳን የሚመስሉት? ህዝቅኤል ጋቢሳ ቅልቅል የሌለው ትግሬ ነው መልኩም ይናገራል የወለጋ ኦሮሞ እንዳለ ጎጃሜ ሲሆን ዮሃን ክራምፕ ነው አጥምቆ ሁሉንም ኦሮሞ ብሎ የጠራቸው። የአሩሲው ከምባታና ሃድያ ነው ኦሮሞ ቁጥሩ ቢበዛ በታሪክ አዋቂዎች ቢበዛ 5% ነው ይላሉ። አርፈው መኖራቸውን ሰው አልጠላውም ብቻ የሰው የሆነ ሁሉ ተሰርቶ ካለቀ በኋላ የኛ ነው የሚሉት ክፉ በሽታ አላቸው አሁን አሁንማ ከባህላቸው እንደ አንዱ አድርገውታል። ሊቀ ሊቃውንት ሕዝቅኤል ጋቢሳ ክርስቶስ ኦሮሞ ነው ብሏል አንዱ እንዲሁ አዳምና ሄዋን ኦሮሞ ናቸው ብሏል አሁን አሁንማ አክሱም አካ ሱማ ከሚለው ቃል የመጣ ነው የኦሮሞ ነው ብለዋል። ግራ የገባ ነገር እኛስ እንችለዋለን ወደ ኬንያም የኛ ነው ማለት ጀምረዋል። አሁን ብዙ የኛ ስደተኞች ሱዳን ውስጥ አሉ ስላስጠጋችሁን እግዜር ይስጣችሁ ይባላል እንጂ ብድግ ብሎ የኛ ነው ይባላል? አሁን ኤርምያስ ምኑ ነው ኦሮሞ የሚመስለው ፈረንጅ ከጋና እሱና ቀጀላ መርዳሳን ሰው እንዲያበጣብጡ ይዟቸው መጥቶ ነው እንጅ። ኧረ ልብ ይስጣችሁ። አይ ዮሃን ክራምፕ የስራህን ይስጥህ።

  3. ኤርምያስ በራሱ መቆም የማይችል የእስስት ባህርይ ያለውችቭ ልጥፍ ነው:: መዋረድ ሲያንሰው ነው:: አብይ ሲነፋፋ ሲያይ ወደ ኦሮሙማ ማዘንበሉ ነው :: ባህርይ አይደል??
    አብይ እንኳን ኤርምያስን ሊያስጠጋ ለራሱም በለኮሰው እሳት እየተለበለበ የሚሄድ ልሙጥ መሀይም:: የቀጠሩት ጌቶቹ ልክ እንደ ላይቤሪያው መሪ ሳሙኤል ዶ ይበሉታል::

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share