January 25, 2023
25 mins read

 የጠላቶቻችን ሤራ ማክሸፍ የምንችለው፣ ሰው መሆናችንን ተገንዝበን ፣ በአንድነት “ እኛ ሰው ነን ። “ በማለት ሥንቆም ብቻ ነው

We Are All People of Ethiopia

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

We Are All People of Ethiopiaየመንግስተ ሰማይ መግቢያ ቁልፍ ተሰጥቶኛል የሚሉ አንድአንድ ፣ የፕሮቴስታንት ሰባኪያን የዓለማዊ ጥቅም ማጋበሻ ሥራ ላይ መጣዳቸው ግልፅ እየሆነ መጥቷል ። ለድሎትና ለምቾት ሲሉ ብቻ  ህቡ በሆነ አገር አፍራሽ  ሤራ ውሥጥ ተጥደው እየተንተከተኩ ነው ። የተቀናጀ  ሤጣናዊ የመከፋፈል  ድርጊት ፤ አገርን ለማፍረስ የተወጠነ ሤራ በቸርቻቸው  ውስጥ ይማሰላል ። “ እመብርሃን አውጪኝ ! “ ማለት ይኽን ጊዜ ነው ።    በየዋሁ እና ወንጌልን አንብቦ በማይረዳው ህዝብ ጢባጢቤ በመጫወት አደንዝዞ የነጭ ባርያ ማድረግ የፕሮቴስንታቱ “ሚሺን እና ጎል “  መሆኑንን የተረዳ ሁሉ ከሐዋርያት ተግባር በእጅጉ ከራቁት ፓስተሮች አርባ ሺ ኪሎሜትር ይርቃል ።

በኢትዮጵያም     ሠርቶ ከመበልፀግ ይልቅ ከሰማይ መና ይወርድልሃል ጠብቅ እያሉ ህዝብ ያለሥራ  አንጋጦ መና ከሰማይ ሲወርድ ለመቅለብ እንዲዘጋጅ ብቻ የሚሰብኩ ጋሃነም የመጨረሻ ቤታቸው የሆነ አያሌ ሰባኪያን አሉ ።

ነገ ሚሊዮን ብሮች በአካውንትህ ይገባል  ! መጪው ጊዜ ያንተ ብልፅግና ነው ! ሰበርኩት ! ወጋሁት በጅዶ ሤጣንን አንከባለልኩት ! “ሊባረባራጨራፎራካራዳራኦራ ! “ በልሣን መናገር ይሉሃል ። ድርቅ ያለ ፈጣጣ ግራ የተጋባ   አስተምህሮ ማአት ዕብድ ሰባኪያን በአገሪቱ  ከተማና ገጠሩን ሲያውኩ እያስተዋልን ነው  ።

ምድረ ሰባኪ ፣ ሐዋርያ ና ፖስተር ተብዬ እንዲደላቀቅ  85 % የኢትዮጵያ ህዝብ በችጋር እንዲገረፍ “ የጌታ ፈቃድ ሆኗል  ። “ ይልሃል ። ይኼ ቱልቱላ !  ፈጣሪ ሰውን እያበላለጠ እንደማይወድ የማናቅ ይመስለዋል ። “ ሐሰትን ይናገር ዘንድ ጌታ ሰው አይደለም ። “

የዛሬን የኢትዮጵያዊውን ሰው  ችግር የፈጠረው የዓለም የሥግብግብ ሥርዓት ነው ። ሰው ሥግብግብ በመሆኑ ነው ኒኩሌር ቦንብ ጭምር በመስራት እርስ በእርሱ በአይነ ቁራኛ እየተያየ የሚኖረው  ። በፈጣሪ ህግ ፣ ደንብና መመሪያ ሰው ቢኖር ኖሮ እኮ ! ድህነት በዓለም ባልኖረ ነበር ። ምድረ ሥግብግብ ኃያል በሆኑት አገራት ፣  በአውሮፖና በአሜሪካ እየኖረ አፍሪካን በመዝረፍ ህዝቧን ያሥርባል ፣ ያሳርዛል እንጂ ፈጣሪ ማንም ሰው እንዲራብና እንዲታረዝ አይፈቅድም ።

የነጮቹ የባዶ ሥብከት አስተምሮም ከአዛኝ ቅቤ አንጓች የዘለለ አይደለም።  በበኩሌ የማሞኘት ፣ አይናችሁን ጨፍኑ እና እንስረቅ ባይነት ላይ የተመሠረተ ነው ። በየሚዲያ ስብከቶቻቸው ይኽው ድራማ ነው የሚሥተዋለው ።

በአገራችንም  አገርን ለማፍረስ ወይም ” ኢትዮጵያ ” የተባለውን የአፍሪካዊያን ኩራት የሆነውን ሥም ለማጥፋት አሊያም ተሸናፊ በማድረግ የጥቁርን ህዝብ አንገት ለመስበር  ሌት ተቀን በገጠርና በከተማ የሚያላዝኑ ሰዎችና የተለያዩ ግለሰቦች የሚዘውሮቸው ማደንቆሪያ ቸርቿች ተፈጥረዋል ። ።

እነዚህ ህዝብን ከሥራ ይልቅ ጩኸት የሚያሥተምሩ ። ፈጣሪን አሳንሰው በማየት ፤ በጩኸት እና በኡኡታ !ብዛት ፣ ይሰማናል ብለው የሚያሥቡ ፣ በትያትረኝነት ደግሞ ፤ ለምፃሙን ፈወስን ፤  እውርን አበራን ፤ ሙታንን አስነሳን ፤ በማለት አሥቂኝ ድራማ በየመድረካቸው የሚያሳዩ  ደረቆች ሆነው እናገኛቸዋለን ።

ይኽንን ስንመለከት ፣ “ እንዴት   ሰው የፈጣሪ ፍጥረት ሆኖ ሣለ  ፣ የፈጣሪውን ሁሉን አዋቂነት ፣ ተመልካችነት ፣ ቻይነት ፣ አድራጊና ፈጣሪነት ዘንግቶ ፣ የፈጣሪን ሚና እጫወታለሁ ?  አንዳችም አይሳነኝም ይላል  ? “

ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ እና የነበረ ነው ። ቤተክርስቲያንም የተመሠረተችው በክርስቶስ ላይ ነው ። የሁላችንም ነፍስ የምትገኘው በመዳፉ ውስጥ ነው ። እኛ ፍጡር ነን ። የእግዚአብሔር ሸክላ ነን ። ፃድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። እኛ ገና በእምነት ና በሥራችን ተመዝነን  ነው ፣ በእርሱ  ለመፅደቅ የምንችለው ።  ትልቁ ወደ ፅድቅ አድራሽ መንገድ ደሞ ወንድማችንን እንደራሳችን መውደድ ነው ። ግን ይኽንን ማድረግ ብዙዎቻችን አልቻልንም ። በተለይም ወጣቱ በለከት አልባው “የፕሮቴስታንቶች መዝሙር ተብዬ ጭፈራ በመማረክ ፍላሎቱን መቆጣጠር አቅቶት   ፤ ገና ወተት እየተጋተ ሣለ ፣ አጥንት ቆርጥሜያለሁ ። ቆሜም መሄድ ጀምሬያለሁ ይለናል ።

ወጣቶች የፓስተሮችን ሴራ እንደ ራዕይ በመቁጠር  ፣ “ራዕያቸው  ሁሉ የፈጣሪ ነው ። “ ብለው በማመን  ለኢየሱስ ክርስቶስ  ወንጌል እውነት ጥብቅና እንደመቆም   ለሐሰተኛ ራእያቸው በማድላት    ለፓስተሮቻቸው ይሟገታሉ ። በበኩሌ ብዙዎቹ ፓስተሮች ሲዖል እንጂ መንግስተ ሰማይ ይገባሉ ብዬ አላስብም ።ህዝብን በድህነት እንዲኖር እያደረጉ ፣ እነሱ እጅግ ከተንቀባረሩ እንዴት አድርገው መንግሥተ ሰማይን ይወርሳሉ?  እንዴት  ፣ አጭበርባሪዎች ፣ ሠራቂዎች ፣ በሐሰት ማዮች ፣ ወንድሞቻቸውን እንደራሳቸው የማይወዱ ። ወዘተ ። ለመንግሥተ ሰማይ ይበቃሉ ?

ክርስቲያኖች ሁሉ በመፀሐፍ ቅዱስ እንደሚመሩ እያወቁ ፣  ፈጣሪያችንን  አቅመ ቢስ አድርገው ፣  እነሱ ሁሉን ቻይ እንደሆኑ በድራማዊ ድርጊት በማሳየት ይህንን ከዕውቀት ያ ተገናኘ  ህዝብ እያሳቱ  “ መንግሥተ ሰማይ የእኔ ናት ማለት ። “  የዋህነት ነው ።

ፈጣሪያችን መድኃኒዓለም በእኛ በሸክለዎቹ ሰዎች የሚመረመር ከቶም  አይደለም ። ለእኛ በጎ ስላደረገልን ሌሎች በጎዳና ላይ ለተሰጡ እልፎች ፣ “ የቡሆ ዕቃቸው “ ባዶ ለሆነ ሚሊዮኖች ፣ በፈጠራት ምድር በሆዳም ፖለቲካኞች ሤራ እየታረዱ ፣ እየተፈጨፉ ላሉት ፍጡሮቹ አይገደውም ብለን ካሰብን ግብዞች ነን ። ከእኛ ከተሟላልን ይልቅ ፈጣሪ ለእነዚህ ዛሬ ለሚያለቅሱ ፣ ለሚያዝኑ፣ለሚራቡ ና ለሚጠሙ ወዘተ  በእጅጉ ያዝናል ።

ዓለም ለሥጋ ያደላች ናት ። የደላው ፣ የተመቸው ፣ የተትረፈረፈው የበለፀገው አገር   ሰው  ፣ ምቾቱና ድሎቱ ሰይጎድል እንዲቀጥል ስለሚያደርገው ስለተጨማሪ ትርፍ እንጂ ፣  ለሚራቡ ፣ ስለታረዙና መጠለያ አልባ ለሆኑ የአፍሪካ ሰዎች ደንታ የለውም ።

የኀጉሪቱ ቱጃሮች ጭምር ለዚህ ለምንዱባን ህዝብ ፈፅሞ ደንታ የላቸውም ። ከመሠርቅ ። ከመዝረፍ የደሃ አገራትን ሀብትና ንብረት አሜሪካና አውሮፓ ውሥጥ ከማካበት  የዘለለ ራዕይ የላቸውም ።

አብዛኛው አፍሪካ በማአድን የበለፀገች ብትሆንም ሀብቷ የድህነቷ ምክንያት ሆኗል ። ብልጡ ፈረንጅ ዜጎቿን ዕውቀት ዓልባ እንዲሆኑ በማድረግ ፣ በድህነት ለሚኖረው ለአንዱ  ሣ ፣ ምግብ ፣ ልብስና የሚተራረድበት መሣሪያ ያቀርባል ። አገሬው  ምድሪቱን  ያለዕውቀት እና ጥበብ  ምንም ሊጠቀምባት ያለመቻሉን እያወቀ ፣ ” ይሄ የአንተ ጎሣ ግዛት  ነው  ፤ ያ የእርሱ ግዛት አይደለም ፣ ለምን ይወስድብሃል ? ” በማለት የአንድ አገር ዜጋ ፣ ፈጣሪ በፈጠራት ምድር ፣ “ ያለገንዘቡ “ በከንቱ እንዲገዳደል   በማድረግ ብዝበዛውን እያደላደለ ነው ። ይኽ አይነቱን ኢ ሰብዓዊነት ሳስተውል  ” ሰው  እንዴት  የአምሳያውን መራብ ፣ መጓሣቆል ፣ በድህነት መቆራመድ ፤ ወዘተ    አይሰቅቀውም ? ” ብዬ እጠይቅና መልሼ ” የአፍሪካን ህዝብ የነጩ ዓለም ከቶ ከሰው ይቆጥረዋልን ? ” በማለት በጥያቄ ጥያቄውን እመልሳለሁ ። …

በነጩ ዓለም ውስጥ ያሉ ጥቂት የኢኮኖሚ የፖለቲካ  የበላይነት ያላቸው ሰዎች ፣ በገዢዎቻቸው በኩል የአፍሪካን ወተት እያለቡ ከመጠጣት ውጪ አህጉሪቱን የማልማት ፤ ህዝቦቿን ከድንቁርና እና ከችጋር የማላቀቅ ቅንጣት ሃሳብ እንደሌላቸው ቢታወቅም ፣ የአፍሪካ ምሁራን ዛሬ የነቁ በመሆኑ ፣  ከገዢዎች የአውቅልሃለሁ ሥብከት ህዝቡን ለማላቀቅና አህጉሪቱን እንደ አውሮፓ ለማበልፀግ  ፣ ፍትህ ፣ ዴሞክራሲ ፣ የዜጎች ሰው የመሆን ነፃነት በአፍሪካ ይንገሥ ዘንድ ሠላማዊ ትግሉ እንዲፋፋም ጥረት እያደረጉ ነው ።  በበኩሌ በኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ ምጡቅ አእምሮ ያላቸው ፖለቲከኞች ፣ ኢኮኖሚስቶች ፣ የማህበራዊ ዘርፍ ባለሙያዎች ፣ ኢጂነሮች ፣ ዶክተሮች ፣ የእርሻ ባለሙያዎች ፣ ወዘተ በብዛት እንዳሉ  አሳምሬ አውቃለሁ ። ይኑሩ እንጂ ሰው መሆናቸውን ብቻ ሥለሚያምኑ ፣ የዘር እና የቋንቋ ሥርዓቱን ሥለሚጠየፉ ፤ የቋንቋ አጥሩም  ሥለማያስጠጋቸው አገርን ለመጥቀም ቢፈልጉም እጅግ አዳጋች የሆነ ፈተና ተጋርጦባቸዋል ። …

” በአፍሪካ ሰው መሆኑን የተገነዘበ ዜጋ በበዛ ቁጥር ፣ በማንኛውም ሰከንድ፣ ኃላፊነቱን ፤ ሟችነቱን ሥለሚያውቅ ፣ ባለው አጭር እድሜ  ከመላው አፍሪካ ዜጋ ጋር ውህደት ፈጥሮ  ፣ ኑሮውን ለማጣፈጥ እዛም እዚህም እየሰራ እስከጊዜው ለመኖር   እንጂ ፤ ልክ ዘላዓለም ዓለም ፣ ነዋሪ እንደሆነ ራሱን በመቁጠር ፣ የሌላውን ህይወት ለመቀማት ጠብመንጃ በማንሳት ፣  ዘመኑንን በመገዳደል አይጨርስም ። እናም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የአፍሪካ አገራት ውሥጥ ሰው መሆኑንን የተገነዘበ መንግሥታዊ ሥርዓት መቋቋም ይኖርበታል ። ” በማለትም ምክራቸውን ይለግሳሉ ።

ዛሬ ምዕመኖቿ ፣ እግዛብሔርን ፈሪና አክባሪ በሆኑ  በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ  ታላቅ ሸፍጥ የተሠራውም ሰውን ከማያስቀድም እና እኔ ቋንቋ ነኝ ። ከሚል አጥራዊ ሥርዓት የተነሳ ነው ።

በዙ ጊዜ እንደፃፍኩት ፤ ኢትዮጵያ በተጨባጭ ያለችው በመከላከያና በፊደራል ፖሊሥ ውሥጥ ብቻ ነው ።  በትርክት ደረጃ በየቴሌቪዢኑ መኖሯ ይታወቃል።  በተረፈ ቋንቋና ጎሣ ነው ፤ በየክልሉ የሚዘመረው ።

አዳም ና ሄዋን የሰው ዘር መገኛ መሆናቸውን በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያምኑ  ዜጎች  ሁሉ ከልባቸው ቢያምኑም በዓለም የሌለው የእኛ የመለሥ ዜናዊ ሥርዓት “ ሰው ቋንቋ ነው።   “ ብሎ “ አንተ ሰው አይደለህም ፤ እንትን ነህ ።እንትን ነህ  ። “ በማለት ሰውነቱን እንዲረሳ በጠብመንጃ አሥገድዶታል ። አንዳንዱንም በእርዳታ ሥንዴ ።

እንሆ ዛሬ    በሰው   መካከል መከፋፈልን የፈጠረው የመለሥ ዜናዊ ቋንቋ ተኮር ሥርዓት ነው ።  ፈጣሪያችን በማይገደው ቋንቋ ፣ ነገድ ና ዘር ተደረጅተው “ የኦሮሞ ቤተክህነት “ በማለት ከመድኃኒታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አስተምህሮ ያፈነገጠ የዲያቢሎስ ሃሳብን ለማራመድ እና ቤተ ክርስቲያኗን “ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ፣ የአንድ ለአምሥት መገለጫ “ በማድረግ  ምዕመናንን በቋንቋ እንዲከፋፈሉ  ለማድረግ ፣ ህገ ቤተክርስቲያንን ጥሰው ፣ በራሳቸው ላይ የጵጵስና ቆብ የደፉት በዚህ ሰው መሆንን በካደ የቋንቋ ሥርዓት የተነሳ ነው  ።

ብዙዎች እንዳሉት  ” እነዚህ የእግዛብሔርን ሥልጣን በጉልበት የቀሙ ናቸው ። ”     እናም   ከእግዜር ጋር የተጣላ ከአማኙ  ህዝብ ጋር የተጣላ መሆኑ የታወቀ ነውና ፣ ማንም አማኝ እነሱ ባሉበት ሥፍራ ሁሉ አይገኝም ። መሥቀላቸውንም አይሳለምም ። ምክንያቱም በአንድ እግዚአብሔር ላይ እና በፍጥረቱ ሰው ላይ መከፋፈልን ፈጥረዋልና !

በነዚህ የኃይማኖት አባቶች ክህደት የተነሳ፣ የፈጣሪ ቅጣት በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በራፍ ላይ ነው ። ከቅጣቱ በፊት ግን ፣ ለሁላችንም ከሐጢያት  ፣ ከዕብሪት ና ከግብዝነት  የመመለሻ ፣ የንሥሐ ጊዜ ሰጥቶናል ። በዚህ ርህራሄው የምናሾፍ ካለን ፍፃሜያችን ጥርስ ማፏጨት ይሆናል ።

” በፈጠርኳቸው በየዋሃን ሰዎች ፣ ሥሜን በሐሰት እያነሳችሁ ፣ ሐዋርያት ነን …እያላችሁ ። ለራሳችሁ ሥም በመስጠት   አትቀልዱ ። ይላል ። ” የሠራዊት ጌታ ፣ ሁሉን ቻዩ እግዛብሔር ።

በበኩሌ ከገዢዎች ቁጣ ፣ ይልቅ የፈጣሪዬን የመድሃኒዓለምን ቁጣ በእጅጉ እፈራለሁ ። … ለሐጢያን የመጣ ለፃድቃንም ይተርፋልና !

ለማሳረጊያ ከመፅሐፍ ቅዱስ መመርያ የሚሆነን እንካችሁ በማለት ፅሑፊን እቋጫለሁ ።

ሉቃስ 9

¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯

¹ አሥራ ሁለቱንም ሐዋርያት በአንድነት ወደ እርሱ ጠርቶ በአጋንንት ሁሉ ላይ ደዌንም ይፈውሱ ዘንድ ኃይልና ሥልጣን ሰጣቸው፤

² የእግዚአብሔርንም መንግሥት እንዲሰብኩና ድውዮችን እንዲፈውሱ ላካቸው፥

³ እንዲህም አላቸው፦ በትርም ቢሆን፥ ከረጢትም ቢሆን፥ እንጀራም ቢሆን፥ ብርም ቢሆን ለመንገድ ምንም አትያዙ፥ ሁለት እጀ ጠባብም አይሁንላችሁ።

⁴ በማናቸውም በምትገቡበት ቤት በዚያ ተቀመጡ ከዚያም ውጡ።

⁵ ማናቸውም የማይቀበሉአችሁ ቢሆኑ፥ ከዚያ ከተማ ወጥታችሁ ምስክር እንዲሆንባቸው ከእግራችሁ ትቢያ አራግፉ።

⁶ ወጥተውም ወንጌልን እየሰበኩና በስፍራው ሁሉ እየፈወሱ በየመንደሩ ያልፉ ነበር።

 

 

ዕብራውያን 3

¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯

( ምዕመናንም ይህንን እንመልከት ። )

 

¹ ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤

² ሙሴ ደግሞ በቤቱ ሁሉ የታመነ እንደሆነ፥ እርሱ ለሾመው የታመነ ነበረ።

³ ቤትን የሚያዘጋጀው ከቤቱ ይልቅ የሚበልጥ ክብር እንዳለው መጠን፥ እንዲሁ እርሱ ከሙሴ ይልቅ የሚበልጥ ክብር የተገባው ሆኖ ተቆጥሮአልና።

⁴ እያንዳንዱ ቤት በአንድ ሰው ተዘጋጅቶአልና፥ ሁሉን ያዘጋጀ ግን እግዚአብሔር ነው።

⁵ ሙሴስ በኋላ ስለሚነገረው ነገር ምስክር ሊሆን በቤቱ ሁሉ እንደ ሎሌ የታመነ ነበረ፥ ክርስቶስ ግን እንደ ልጅ በቤቱ ላይ የታመነ ነው፤

⁶ እኛም የምንደፍርበትን የምንመካበትንም ተስፋ እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ ቤቱ ነን።

⁷ ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚል፦

⁸-⁹ ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት፥ አባቶቻችሁ እኔን የፈተኑበት የመረመሩበትም አርባ ዓመትም ሥራዬን ያዩበት በምድረ በዳ በፈተና ቀን በማስመረር እንደ ሆነ፥ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።

¹⁰ ስለዚህ ያን ትውልድ ተቆጥቼ፦ ዘወትር በልባቸው ይስታሉ መንገዴን ግን አላወቁም አልሁ፤

¹¹ እንዲሁ፦ ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቍጣዬ ማልሁ።

¹² ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤

¹³ ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፥ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፥ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ፤

¹⁴ የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና፤

¹⁵ እየተባለ፦ ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።

¹⁶ ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ? በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን?

¹⁷ አርባ አመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ፥ ኃጢአትን ያደረጉት እነርሱ አይደሉምን?

¹⁸ ካልታዘዙትም በቀር ወደ እረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ?

¹⁹ ባለማመናቸውም ጠንቅ ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

179101
Previous Story

የፌደራል ስርዓት መርሆዎች በ ገለታው ዘለቀ

ዲያቢሎስ አብይ አህመድ
Next Story

የጠቅላይ ሓሳዩን ጓደኞች እንተዋወቅ!! – ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop