በሰው ና በዜጋ ላይ የተመሠረተ የመንግሥት ሥርዓት ፤ ዛሬ ና አሁን  እጅግ እንደሚያሥፈልገን የተገነዘብን ይመሥለኛል ።

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ

ወያኔ ፤ ( ትህነግ ፣ ህውሃት ፤… ወዘተ ። ይባል ። የሰው ሥብሥብ ነው ። ሆኖም በዘር ላይ የተመሠረተ ጠባብ የፖለቲካ ቡድን እንደሆነም ይታወቃል ። ) ከኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት ጋር ታረቀ ። ” ትጥቄን እፈታለሁ ። የጦር መሣሪያም አሥረክባለሁ ። አዲስ ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም ና ነፃ ምርጫ በትግራይ እንዲካሄድ እንቅፋት አልሆንም ። ሠላምን በትግራይ ክልል ለማንገሥ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር  ተባብሬ እሰራለሁ  ። ” አለ ። ወዘተ ።   ብሎ በደቡብ አፍሪካ በፕሪቶሪያ ከተማ የሠላም ሥምምነት ሰነድ ፈረመ ። ሲባል ፣ ” እፎይ ! ቀየደቂቃው ፣ በከንቱ የሚሞተውን ወገናችንን መታደግ በራሱ የሚያሥመሠግን ተግባር ነው ።  ምንም የማያውቀው ምሥኪን ህዝብ ፀሎቱን ፈጣሪ ሰማው ። ” ነው ያልነው ። አብዛኛው ሠላም ወዳድ ህዝብና  ብዙዎቹ  ምሁራን ። በቀና ልቦና ይኽንን ነው ያሉት ። ( በበኩሌ ጦርነት መቆሙን ብቻ ሣይሆን ፍፁም ከአገራችን ቢጠፋ ደሥተኛ ነኝ ።  ” ሰው የሚገድልና የሚያሰቃይ ሤጣን ብቻ ነው ። ” ብዬ የማምን ሰው ነኝ ። ሤጣን ደግሞ በልዩ፣ልዩ መንገድ የሰውን አእምሮ ተቆጣጥሮ እንደ ሰው ፣ ሰው ሆኖ በሰዎች ህሊና ውሥጥ በያዳንዱ ሰው ይሁንታ የሚኖር ነው ። መጥፎ ና እኩይ ድርጊት ከየትም አይመጣም ። ሴጣን ከተጠናወተው ለበጎና ለሠናይ ምግባር ካልተገዛ አእምሮ እንጂ ! )

… ይኽንን ድንገታዊ የእርቅ ዜና ሥሰማ ግን ( ልብ በሉ ፤ ወያኔ ግብዓተ መሬቷ ሊፈፀም አንድ ሐሙሥ ሲቀረው የተደረገ የሠላም ሥምምነት ነው ። )     ” ከእንግዲህ  በሬ ወለደ ቢሉኝ አምናለሁ ። ” ነው ያልኩት ። ” The Impossible  is possible  . How the dead man Woking ? ” …  ። …

” ኩበት ሰምጦ ዲንጋይ ዋኘ ። አህያ  በቅጥር ጊቢ  ውሥጥ ተወስና  የውሻን ተግባር ፈፀመች ።  የቤት ፣የሠፈር  ጠባቂነት ላይ የተሰማራው  ውሻ ሣር ሊግጥ ና ሊያናፋ ፣ ወደ  ዳ ወጣ  ። ወተት ጠቆረ ። ኑግም ነጣ ። ” ቢሉኝ ከእንግዲህ በኋላ  አምናለሁ ። ነበር ያልኩት  ።  ነገሩ ሁሉ ፣ ” ድመት መንኩሳ ፣ ዓመሏን አትረሳ  ! ”   እንደሚሆን ግን አላጣሁትም ነበር ። ዛሬም እየሆነ ያለው ይኸው ነው ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በህገመንግስቱም ቢሆን ወልቃይት ጠገዴና ራያ የአማራ እንጅ የትግራይ ሊሆኑ አይችሉም!!!

ዛሬ እየሆነ እያሥተዋልን ያለነው እውነት ግን ፣ዓይናችንን ለሠላም ብለን ሥንጨፍን  ፣ ከበፊቱ በተጠናከረ መልኩ  ዘመናዊ ቢላዋ እና ልዩ፣ልዪ ኃይልን የመሣል ተግባር ነው ። ኃይል በማደራጀት ና  በሥልጠና በማብቃት  ፤ ምናልባትም በጠላቶቻችን የታገዘ  ወታደራዊ ሥልጠና በማግኘት ለዳግማዊው  መብረቃዊ ጥቃት ወያኔ እየተዘጋጀች ሊሆን ይችላል ።  ይሁን እንጂ ይኽንን እኩይ የጥፋት ዕቅድ እንዳናውቅባቸው የሠላም ሥምምነት የጊዜ ማራዘሚያ ድራማ ትህነግ ከግብረ አበሮቹ ጋር እየተወነ  እንደሆነ የሚያጠራጥሩ ድርጊቶች አልፎ፣አልፎ ሲከወን እየታዘብን ነው ።

ለመሆኑ ፣ ” የኤርትራ ጦር ከራሱ ደንበር ይልቀቅ ፤ ካለቀቀ ሥምምነቱን አንተገብርም ። ” ማለት ምን ማለት ነው ? ” ህውሃት የትግራይ ክልል ምክር ቤትን ጠርታ መሠብሰቦ ምን መልዕክት ና ለማሥተላለፍ ፈልጋ ነው ? ‘ የሞትነውም እኛ ያለነው ና በጠብ መንጃ እየስፈራራን ህዝብን የምንመራው እኛ ነን  ። ” ማለቷ  ይሆንን ?  መከላከያን ያለ ደጀን ለማሥቀረት እና ተረት ለማድረግ ነው  እንዴ …” የኤርትራ ጦር ከድንበሩ  ይልቀቅ  ። ” እየተባለ በዘወርዋሬ የሚጮኸው ። የኢትዮጵያን መከላከያ አለአጋር ለማሥቀረት ተፈልጎ እንደሆነ የማይገባው ማነው ?

ወዳጄ ሆይ ! ሠላም !ሠላም ! የሚለውን  የማዘናጊያ ዘፈን አብረህ በማንጎራጎር አትዘናጋ  ። ወደድክም ጠላህም የተቀሩት ጥቂት እባቦች ጭንቅላታቸው ተቀጥቅጦ እሥካልሞቱ ጊዜ ደረስ የአማራና የአፋር  ልቂት እና የኢትዮጵያ መድማት  ቀጣይ እንደሆነም ተገንዘብ ። ለሚቀጥሉት አራት ወራት ወያኔ እፎይታን ካገኘች ለታአምር የሚበቃ ዘግናኝ ድርጊት መፈፀሞ አይቀርም ። ይልቁንስ ከኤርትራ ጦር ጋር እንደ አገር ተባብሮ የተቀናጀ የጦር ልምምድ ማድረግ የሚያዋጣ እና ጥሩው አማራጭ  መሆኑንን ተገንዘብ ። ወያኔ “በዓምበሉ “ አማካኝነት አሣልፎ የሰጠውን አገር ዛሬ በጠላትነት የሚመለከተው ከምዕራባውያን ጥቅም አንፃር መሆኑንም አትዘንጋ ። የዛሬው የወያኔ ዓምበልም የህውሓትን ማሊያ ለብሶ ለአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም እንደሚጫወት እወቅ ። የሚሊዮኑ ደሃ የትግራይ ወጣት ከንቱ ሞት ለእርሱ የሆሊውድ ፊልም ነው ። ( የሚያሳዝነው በዚህ እጅግ ዘመናዊ ዓለም እኛ እንደ ዲንጋይ ዘመን ህዝቧች በጭፍን እና በመንገኝነት ፤ በጉልበት መሪ የሆኑትን አላዋቂ ጥቂት ግለሰቦች መከተላችን ነው ። )

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጀዋር መሐመድ የኢትዮጵያ አቤሴሎም መሆኑን ገሃድ እያውጣ ነው - ዋቅወያ ነመራ

ወያኔዎች ለአሜሪካ  መንግሥት ባለሥልጣናት ፣ በሰጡት የወርቅ ገፀ በረከት በዘመናዊ መሣሪያ ብቻ ሣይሆን በዘመናዊ መንገድ  የትግራይን ልዩ ጦር እየሰለጠኑ እንደሚገኙ አጠራጣሪ ምልክቶች ከታዩ ይኽ እጅግ አደገኛውና ደግማዊ አደዋን ከሳች ሴራ እንደሚሆን ከወዲሁ ይወቁት   ። … ( የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጥቅም እንጂ ሌላ የሚገዛቸውም ሆነ የሚገዙለት ምድራዊኃይል እንደሌለ እናውቃለን ። በሱማሌያ የተዋረዱትም ነዳጇን አይተው ነው ። በዩክሬንም ይኽ የጥቅም ታሪክ ነው ከዘሌኒሥኪ ጋር እንዲወግኑ ያደረጋቸው ።   ሥጋ ባለበት በዛ ፣ አሞራ እንደሚሰባሰብ እወቅ ። )

ከትህነግ የጭራቅ መንገድ  ለመላቀቅም የኢትዮጵያ ህዝብ ያለው ምርጫ አንድና አንድ ነው ። አሁን እና ዛሬ እያባለን ያለውን የዘረኞች የከፋፍለህ ግዛ የፖለቲካ መንገዳችንን ወደ ሰውና ዜጋ ዘመናዊ የፖለቲካ ሥርዓት መቀየር ። ይኽንን ሥታደርግ ብቻ ነው ወያኔንን በአፍጢሙ የምትከሰክሰው  ። ይህንን ሥርዓት ካነበርን ፣ በአንድ ቀን የትግራይ ኗሪ ህዝብ ህውሃትን ታሪክ ያደርጋታል ።  እነዚህ ከ50 ዓመት በፊት ፣ በወቅቱ ባለው ነባራዊ ሁኔታ አሥገዳጅነት ህሊናቸው ውሥጥ በተሰነቀረ የጥላቻ መርዝ  የታመሙ ወያኔዎችና ርዝራዦቻቸው ፣ እሥከ አሥተሣሠባቸው ይጠፋሉ ። ይኽ ከፋፋይ ና የሰው እና የዜግነት ጠላት የሆነ የፐለቲካ ሥርዓት እሥካልተቀየረ  ጊዜ ድረስ ፤ በአገር ምድሩ ሤጣናዊ   ድርጊትና የድረሱልን ጩኸቱ  እንደማያባራ እወቁ ።

ነገ ተነገወዲያ ፣ የሰሜኑ እኩይ እና ከኢትዮጵያዊው ክቡሩ እና ጨዋ አስተሳሰብ ያፈነገጠ  እና ኃይማኖታዊ ሥነምግባርን  የጣሰ  ድርጊት በሁሉም ክልሎችም እጅግ መስፋፋቱም አይቀርም ። ( የዮናታንም ( The devils advocacy የተባለ የሆሊውድ ፊልም ዓይነት ) ሥብከት ይኽንኑ የተቀናጀ ኢትዮጵያን የማፈራረስ አጀንዳ የሚያመለክት ነው ብዬ አሥባለሁ ። ማንም እየተነሳ ለምን “ በዋቄ ፈታ “ ታምናለህ ሊለኝ አይችልም ። ምን አገባው ? እያንዳንዱ የኃይማኖት አሥተሣሠብ ከህግ ተቃራኒ እሥካልሆነ ጊዜ ድረስ ይከበራል   ። የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትና አሥተምህሮም በኢትዮጵያ ትልቁን የህዝብ ቁጥር የያዘ ነውና  ሊከበር ይገባዋል ። አንድአንዱ ሰባኪ አወቅህ ፣ አወቅህ ሲባል “ እኔ ኢየሱስ ነኝ ። “ እንደሚል በኢትዮጵያ የኃይማኖት  ታሪክ ተደጋግሞ መታየቱንም አሥታውሱ ። በግሌ “ አዩም ሆነ ዮናታን ) ለእኔ   ተራ ሟቾች  ናቸው ። ከሞቱ በኋላ  የሚፈጠረውን   የሲኦልና የገነቱን ቅጣት  ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያቅላቸው ። …

ተጨማሪ ያንብቡ:  Ethiopia: Muslim Protesters Face Unfair Trial

እና ዛሬ ከጎጠኞች  ጋር ተዳብለወ በኃይማኖት ሥም ህዝብን የሚከፋፍሉ የነማን ቅጥረኞች እንደሆኑ የታወቀ ነው ። እሥቲ ለልማት እና ለደሃው ህዝብ እንሰራለን ካሉ በሚሊዮን የሚቆጠርን ወጣት ወደ ሥራ የሚያሰማሩ የተለያዩ ለአገር የሚበጁ ፋብሪካዎችን በአገራችን እንዲገነቡ ለወሬ ብቻ የሚደጉሟቸውን ፈረንጆች ይማፀኑ  ። አገር የምትገነባው እኮ ፀሎት ከሥራ ጋር ሲጣመር እንጂ ቸርች ውሥጥ ዝንጥ ብሎ በርዕቱ አንደበት በማውራት  አይደለም ።…

ዛሬ እና አሁን ፣ መርዘኞቹም ሆነ መርዙ ሳይኖር  ፤ በጥቅም የተሣሠሩ ፣ መሞታቸውን የዘነጉ ዘረኞች ና ጎጠኞች ከ 50 ዓመት በፊት    በሚሰቃዩበት ህመም እየተሰቃዩ ነው።   እነዚህ   ህሊናቸው የታመመ  ፖለቲከኞች እና ደቀመዝሙሮቻቸው ፤ ቢያንስ  በተፈጥሮ ሞት   ከምድሪቱ እሥካልጠፉ ጊዜ ድረስ ዜጎች አጭርና ጣፋጪ መሆን የሚገባትን ህይወታቸውን በስቃይና በሰቆቃ መኖራቸውን ይቀጥላሉ ።

በበኩሌ እነዚህ እብድ ፕለቲከኞች ከኢትዮጵያ ጥርግርግ አድርጎ ፈጣሪ እንዲያጠፋቸው እና በአገራችን የዜጎች ሰብዓዋ መብት እና የዴሞክራሲ መብት ተከብሮ ፤ ፍትህ ለሁሉም እኩል ተዳርሶ … ህግም በአገራችን የሁሉም የበላይ ሆኖ ፣ የሁሉም ሰው መብት በቋነቋ ሥም ሳይረገጥ ዜጋ በአገሩ እንዳሻው  ተዞዙሮ በመሥራት ህይወቱን አጣፍጦ ፣ለትውልዱም ጥሪት አፍርቶ የሚሞትበት መልካም ሥርዓት እንዲመጣ እፀልያለሁ ። …

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share