እንሆ፣ ዕቅድ “ሐ“ (Plan C) ተጀምሯ! ትንቢት ከነገር ይቀድማል! – ሲና ዘ ሙሴ 

“ የእግዚአብሔርም ክብር በሲና ተራራ ላይ ተቀመጠ፥ ደመናውም ስድስት ቀን ሸፈነው፤  በሰባተኛውም ቀን ከደመናው ውስጥ ሙሴን ጠራው። ”

— ዘጸአት 24፥16

ይኽ ፀሐፊ አንድ ጥያቄ የኢትዮጵያ ህዝብንና መንግሥትን ይጠይቃል ? ኢትዮጵያዊያን ሠላም አለ የምንለው እኛ መኖርያ ቤት ውሥጥ ሽፍቶች ፣ ወንበዴዎች ፣ ቀማኞች ፣ ዘራፊዎች ፣ አራጅ ና ገዳዮች ገብተው ቤተሰባችንን በጭካኔ ሥላልገደሉ እና ሥላልዘረፉ ነውን ? መንግሥትሥ “ ሠላም አለ ። “ የሚለን ፣  የተደራጀ ፣ ለሁሉም ግዳጅ ዝግጁ የሆነ የመከላከያ እና የፊደራል ኃይል ሥላለኝ ቤተመንግሥቴን እና ቤተሰቤን እሥከዛሬ ማንም ጫፋቸውን አልነካም ።   ”  በማለት አሳቤ ነውን ? …

አገር በሽብር ኃይሎች እየተናጠች ፤ እንዴት ሠላም  አለኝሥ ይባላል ?  በመንግሥት ውሥጥ ሌላ መንግሥት የመሠረቱ ህቡ ሃይሎች እያሉ እንዴትሥ በዜጎች አእምሮ ውሥጥ  ሠላም ሊኖር ይችላል ? በሙሥና የተዘፈቀ ፣ በምቾትና በድሎት ባህር የሚዋኝ የደህንነት ከፍተኛ ባለሥልጣን እያለ እንዴት አገር ሠላም ትሆናለች ?  እነ ብር አምላኩ በየክልሉ ሥልጣን ይዘው ፤ እግዚአብሔር ተረስቶ እንዴት አገር ሠላም  ትጎናፀፋለች ?

ሥለ እግዜር ሲነሳ ፣ በቅርቡ ፣ አንድ የ19 ዓመት እንቦቃቅላ  ልጃቸውን በዚህ ትርጉመ ቢሥ እምሮ ቢሥ  የወሮበሎች ሥብሥብ   ( ቋንቋን እንደመጨቆኛ መሣሪያ  በማየትሰውን በቋንቋውና በመጠሪያ ሥሙ በሚፈርጅ ከዘመናዊ ሥልጣኔ እና ከዓለም ነባራዊ የኑሮ ዘይቤ እጅግ እርቆ በ15 ኛው ክ/ዘ አሥተሣሠብ እየኖረ ባለ አረመኔ ቡድን ። ያጡ እናትን ላፅናናቸው ቤታቸው ጎራ ብዬ እንዲህ አሉኝ “…እግዚአብሔር  መፍትሄ ያምጣልን ? ‘ እርሱ ያብርደው ! ‘ ትለኛለህ ልጄ !  እርሱም አቅቶታል መሠለኝ … ?  ለዚች አገር ያለመከፋፈል ከእኔ ቤት እንኳን አምሥት ሥጋዎቼን ገብሬለሁ ? እና ምን ተገኘ ? አራቱ በሰሜን ተሰው ። ለዚች ዛሬም ሊከፋፍሎት ከሚጠሩ ሤጣኖች ጋር ተናንቀው ። ዛሬ ደግሞ እትብትህ በተቀበረበት  በቀዬህ ፣ በታዛህ ፣ ‘ እግዜር በፈጠረልህ መሬት  የአግዜሩን መሬት ቀምተውት የእኔ ብቻ ነው ። ‘ በማለት በቋንቋ  ተቧድነው በጅብ መንገድ በሚጎዙ  ኦነግ ሸኔ በተባለ ቅፅል ሥም በሚቀሳቀሱ ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች እዚሁ መሐል አገር ልጄን ተነጠቅሁ ። … ጎጆ ቀልሰህ ፣ አፈር ገፍተህ እየኖርክ … ጠፍጥፎ ያልሰራትን መሬት … የኔነው እያለ… ይሄ  ገንዘብ አይኑንን ያወረው ህሊና ቢሥ ቅጥረኛ ንብረትህን አውድሞ አንተን በየቀኑ ሲያርድህ … እንዴት ፈጣሪ ሠላም ያመጣል  ብለህ ታሥባለህ ? ” በማለት በምሬት ጠየቁኝ ።

እኔም ፤ ”  እውነት ብለዋል ። ሰው ከአራት ኪሎ ብዙም ሳይርቅ እየታረደ ነው ። ዕውቁ ጋዜጠኛ  ታምራት ነገራ ፣ ብዙም ባራቀ ወቅት በተራራ ሚዲያ በዩቲየቡ  እንደተነበየው ፤ ‘ ይኽ ፅንፈኛ … ድርጊት በአጭር ካልተቀጨ ጠቅላይ ሚኒሥትራችንን ዶክተር  አብይ አህመድን የሚበላ ነው ። ‘ ምናልባትም  ሰውየው ፣ ‘ ሤጣናቱ ምንም አያመጡም ! ‘ ብለው እጃቸውን አጣጥፈው ፣ በትወራ  ብቻ ‘ አንድነት ! አንድነት ! ‘ እያሉ ከተሞኙ ፣ እርሱ እንዳለው   ‘ አሥከሬናቸው በአራት ኪሎ ቤተመንግሥት ደጃፍ  መጎተቱ አይቀርም ‘  ። ” አልኳቸው ።

ዛሬ ና  አሁን የምናሥተውለው የሤጣን ተግባር ይኽንኑ ቀፋፊ ትንቢት  መልሰን እንድንል  ያሥገድደናል ። ይኽንን ግምት ” የሤጣን ጆሮ አይሥማው ። ” ማለት አይቻልም ። ሤጣን እጅግ  ተራብቶ ጆሮ ብዙ ሆኗልና !  ዛሬ እና አሁን ፣ በኦሮሚያ ባሉ የፊደራል ዩኒቨርስቲዎች እንኳን ጥቂት የማይባል “ የሤጣን ጆሮ አለ ። “  ( አሥደናቂው ነገር የፊደራል ዩኒቨርስቲዎች ዛሬም የሤራ ፖለቲካ መዘውር እና በኦህዲዳዊ ካድሬዎች ፤ በብአዴን ፤ በህወሓት ወዘተ ካድሬዎች መመራታቸው ነው ። ሜሪት አያሠራም ። ከኢህአዴግ እሥከ ግልብጡ ብልፅግና ያውና አንድ ብቻ ሣይሆን የባሰ ካድሬያዊ አመራር  ቀበሌ ድረስ ተዘርግቶ ዛሬም ድረስ እንደ ጭከቃ ሹም ህዝብን ያሰቃያል  ። ህዝብን ለፖለቲካ ወጥመድ የሚያዘጋጅና የምርጫ ማጭበርበሪያ ሥውር መድረክ የሆነው ፤  የካድሬ መናሀሪያ ፈርሶ በትክክለኛው የማዘጋጃ አገልግሎት ካልተተካ ሠላም  በአገር ይመጣል ብሎ የሚያሥብ ጅላንፎ ብቻ ነው ።  ወዳጄ እንደ ኮሮና የሚዛመተው ቫይረሥ መፈልፈያ ቀበሌ  እንደሆነ ህዝብ ያውቃል ። የቫይረሱን በሽታ የሚያሥተላልፈውም ሆድ  አደሩና በዘረፋ የተካነው ከኢህአዴግ ወደብልፅግና የተቀየረው  ካድሬ ነው ። አካፋን ቀለም ብትቀባው ያምራል እንጂ ግብሩን አይቀይርም ። አካፋ አካፋ ነው ።  ካድሬ ሆይ ብጠላኝም ጥለኝ ፣ ‘ መልከ ጥፉን በሥም መደገፍ አይቻልም ።’  እልሃለሁ ። ደግሞም ግማሽ ሉጩ ግማሽ ጎፈሬ መሆን ለተመልካቹ ያሥጠላል ። ያደናግርማል ። በቀኝ በኩልና በግራ በኩል ሲታይ ። ቀኙ ተላጭቷል ግራው ጎፈሬ ነው ። ለእሥታይል ከሆነ ብቻ ይኽ አይነቱ “  በፍላሎታሞች “ የሚወደድ ይሆናል  ። በፍላሎት ዓለም ለሚዎኙ “ አይፈራም ! ጋሜ አይፈራሞች ! “  ይኽ ኖርማል ነው ። ህይወትን በ360 ዲግሪ ለምንመለከት ግን ይህ እብደት ነው  ። ‘ እሥቲ ከባላቶሊ ቁርጥ እና ከሜሲ ቁርጥ የቱ ያምራል ? ‘  ፍላሎታሞቹ ይመልሱ  ። …

ተጨማሪ ያንብቡ:  ማነዉ ፈሪዉ ተቀዋሚ ወይስ ህወሃት/ ኢህአደግ?

ዛሬ ፣ ዛሬ የሤጣን ጆሮ የበረከተበት ፣ ቅዱሣን እና መልዓክት የፈጣሪን ይቅርታ ለማግኘት የሚማልዱበት ወቅት ላይ ደርሰናል ። ሙሴ ያጋጠመው ፈተና በኢትዮጵያዊያን ላይ ተደግሟል ። ኢ _ አማኒያን ሰዎችን ያለርህራሄ እያረዱ ነው ። በሴጣን ፈረሥ እየጋለቡ ። ኦሮሚያ እየተባለች በቋንቋ ነገሥታት በምትመራ ክልል በደም እጃቸውን እየታጠቡ ነው ። ትላንት  እንደ ፊውዳል በትውልድህ ዘርህ ተቆጥሮ ለሹመት እና ለሥልጣን እንደምትበቃ ሁሉ ፣ ዛሬም በኦህዴድነት አሥመሣይ ካድሬነትህ እና በቋንቋህ እንዲሁም ምሥጢር ጠባቂ ሌባነትህ እየተሞላቀቅህ በሰው ደም እየሠከርክ ነው ።  በአማራም ፣ በትግሬም ፣ በአጠቃላይ በሁሉም ክልሎችም በብዙም ሆነ በጥቂት ይኸው እውነት አለ ።  በተመሣሣይ መልከ ነው ፣ ለሹመትና ለሽልማት የምትበቃው ። ህሊና እና የራሥህ እውቀትና እግር ካለህ በጥበብ የላቅህ ፣ ሰው መሆን ብቻ የምትፈልግ ኦሮሞ ፣ ትግሬ ፣ አማራ ፣ ሱማሌ ፣ ሲዳማ ፣ ወላይታ ወዘተ ። ግን ማንም እዚህ ጠባብ እና ህሊና ቢሥ ቡድን ውሥጥ እንድትገባ አይፈቅድልህም   ።

እግዚአብሔር በፈጠራት ምድር ፣ በተለይም በኢትዮጵያ ህግ አሥከባሪ ፀረ _ ዳያቢሎሥ መንግሥት በወጉ ባለመደራጀቱ ነው ህሊና ላለው ለሥጋው ሳይሆን ለነፍሱ ላደረ ጠቢብ የከፍተኛ አመራርም ሆነ በተዋረድ ያሉ የህዝብ ማሥተዳደር ፣ የሥልጣን ክብር የተነፈገው  ። እግዛብሔርን ሥለሚያከብር።  እግዚአብሔር ግን አለ ። ሤጣኖቹ ግን በድፍን ኢትዮጵያ ሰውነትን ቀብረው ቋንቋ ሆነው ፀረ ሰው በመሆን  የሥልጣን ወንበር ላይ  ፊጥ ብለዋል ። በተለይም በኦሮሚያ ከግብፅ በመጡ ፣ በግብፅ በሠለጠኑ ፣ በግብፅ በሚከፈሉ ፣  በነጃዋር በህቡ በሚመሩ እና በወያኔ ፕላን ሲ ( Plan C ) በተካተቱ  እጅግ ምሥጢራዊ በሆነ መንገድ ” ኔት ወርክድ ” በሆኑ ፤ እየተፈፀመ ያለው አገር የማፍረስ እንቅስቃሴ ሀገር ወዳዶች ቸል የማይሉት ተግባር ነው ።

በዚህ በረቀቀ መረባቸው እየፈፀሙት ያለውን ፀረ ሠላም እንቅሥቃሴ የኢትዮጵያ ልጆች ፣ በተለይም የአገር መከላከያ ሠራዊት ከቶም አይረሳውም ። ሣይበቀላቸውም በዝምታ አያልፍም ። የኢትዮጵያ ምሣሌ በመሆኑ ።  መንግሥት ህዝብ  ሠላም እንዳያገኝ ባለማሠለሥ እየጣሩ ባሉት ፤ በገንዘባቸው ኃይል ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ( የመከላከያን ፣ የፓሊሥን እና የደህንነትንም ይጨምራል ። ) በደካማ ጎናቸው ( በተደበቀ ሱሳቸው  ፣ ፀባይ እና ዓመላቸው ) በመግባት  የእነሱ ሎሌ በማድረግ ፣  አገርን በማያባራ ትርምስ ውሥጥ ለማሥገባት ፣ አገር ወዳድ መከላከያውን ፣ ፌደራል ፖሊሥን ለከንቱ መሥዋትነት የሚዳረጉትን በምሥጢራዊ ዕቅድ ማሶገድ ካልቻለ ፣ አገራችንን ጠላቶቻችን እና የውጪ ጅቦች  ተቀራምተው እንደሚበሏት ዛሬ ይበልጥ ግልፅ እየሆነ መጥቷል   ። እንዴት ቢሉ የአገር መከላከያ ሠራዊቱ ና የፊደራል ፖሊሱ እንዲሁም ሙያቸውን የሚያከብሩ የክልል ፖሊሶች በከንቱ ህይወታቸውን አሰየተነጠቁ ናቸውና ! ያልተገባ መሥዋትነት እነዚህ ውድ እና ብርቅ  አገር ወደድ ኢትዮጵያዊያን መክፈላቸው ፣ ነገ የሚያመጣው ጦሥ ደግሞ እጅግ መጥፎ ሊሆን እንደሚችልም መንግሥት ማወቅ አለበት  ። በበኩሌ ክፉው እና አገር አጥፊው ነገር ከመከሰቱ በፊት ፣  ጠቅላይ ሚኒሥቴር አብይ  ኮሶን ለኢትዮጵያ ሲሉ በተገቢው አቅጣጫ በማሾር በህዝብ ቅቡልነት ያለው ማራኪ ግብ ቢያሥቆጥሩ እመርጣለሁ ። ይኽ እድል ለቀድሞው ጠ/ሚ  መለሥ ዜናዊ  በአንድ ወቅት ተሠጥቷቸው ነበር ። ሆኖም አልተጠቀሙበትም ። …

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን መጥላት ፤ ማጥላለት ኢትዮጵያዊነት ሊሆን አይችል!!!

ለጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ ባልተሰወረ መልኩ ፣   በብሔር ብሔረሰብ ሥም ፣ እየተጠቀመ ያለው ህዝብ አይደለም ። የትም ክልል ደሃ ተከባብሮ እየኖረ ነው ። ከ85 % በላይ ህዝብ ደሃ ነው ። የቋንቋዊ ዘረፋም ተጠቃሚ አይደለም ። እድርና ባልትነው አንድ ነው ። ጉልቱ እና መኮመሪያ ጣሳው አንድ ነው ። እርፍ ና ደጋኑ አንድ እና ያው ነው ። ምጣዱ ፣ ድሥቱ ፣ ጀበናው አንድ ነው ። የሚበላው እንጀራ፣ ቂጣው ፣ ቆሎና ንፍሮው ሣይቀር አንድ ነው ። ያም ይኼም በጪሥ የሚጨናበሥ ነው ። ያም ይኼም በብድር መብራት እና በቤት ኪራይ መከራውን እየበላ ያለ ምሥኪን ነው ።  … የተቀረው ጥቂቱ 5% ደግሞ   ለቋንቋ መሥፍንቶች እና መኮንንቶች በማደግደግ እና ጭራ በመቁላት  ሀብት ና ንብረት  ያፈራ ነው ። …

ይኽ የሚያሣብቀው መንግሥት ማወቅራዊ ህመም እንዳለው ነው ። በሽታው እጅግ ጥልቅ እና ጋንግሪን የፈጠረ መሆኑ በግልፅ እየታየ ነው ። እናም አካሉን ጨርሶ ወደ ጭንቅላቱ ጋንግሪኑ ከመዝለቁ በፊት ፣ የተበላሹ እግሮቹን ቆርጦ ሊጥላቸው ግድ ይሆንበታል ።  ይኽ ቱሁት ምክሬ ነው ። ጋንግሪኑ ግልፅ ፣ የማይቀለበሥ አደጋ እያሥከተለ ነው ።  የአገር አለኝታዎች እያሣጣ ያለ የሚያሥቆጭ ብቻ ሣይሆን እጅግ የሚያናድድ አደጋ እየጋረጠ ነው። በየቀኑ አሰያሥሞተ ነው ። ራሳቸውን መከላከል በማይችሉበት ሁኔታ በጠራራ ፀሀይ ለግዳጅ የወጡ አልኝታዎቻችንን በከንተሐ እያጣን ነው ።አዲስ አበባ ባንዲራ አትስቀሉ በሚሉ በግብፅ ወሮበሎች ተከባለች ።  ህዝብ ፣ ገንዘብ በሚከፈላቸው   በታጠቁ ሺፍቶች  በደፈጣ በየቀኑ  ይረሸናል ። ” ወታደራዊ ኦፕሬሽን እና ግዳጅ በጠራራ ፀሐይ ”  ውጡ እየተባለ የአይናችንን ብሌኖች በፈሪ በትር እናጣለን  ። በሞታቸው እንበግናለን ።  እርር ጭሥሥ እንላለን ። ህሊና አለንና ። የሞቱት እንደ እየሱስ ነውና !! ….

ከዚህ ተነስቼ አገር ወዳዱ የመንግሥት ከፍተኛ አመራር ፣  በኦሮሚያ ያለውን ህገወጥ አደረጃጀት ማፍረስ አለበት ። እላለሁ ። ሳይዘገይ ፣ ሚሊሻ የተባለውን ፣ ለመዝረፍ ከየቀበሌው የተመለመለውን በከተመሠም ሆነ በገጠር ያለውን ፣  ማፍረስ አለበት ። ሃምሳ ፐርሰንቱ  ለዘረፋ የተሰማራ ነውና ። ያለአንዳች አሉባልታ ሃምሳ ፐርሰንቱ  ጭለማን ተገን አድርጎ የሚዘርፍ ነው ። ይኽ ሐሰት  እንዳይደለ  የትኛውም የከባድ መኪና አሽከርካሪ ይነግራችኋል ። ከዚህ ይልቀሰ ወጣት የሆነውን የሚሊሻ ሃይል በጥንቃቄ መልምሎ “ የፈጥኖ ደራሽ “ ልዩ ኃይል በማቋቋም ፀረ ሽፍታ ኃይል በፊደራል ደረጃ ማቋቋም ይበጃል ። ይኽ ሃይል በሲቪልም በጋራ ተንቀሳቅሶ የሚሠራ ወይም ግዳጁን የሚፈፅም ሃይል ሆኖ ቢሠለጥንም መልካም ነው ። ካሥፈለገም ከልዩ ኩማንዶ ጋር በማቀናጀት በአጭር ጊዜ የተረጋጋ ሠላም በአገር ማምጣት ይቻላል ።

እንዲህ ዓይነቱን የሠለጠነ እና የነቃ ፣ በምሥጢርም የሚንቀሣቀሥ ልዩ የአገር ደህንነት ኃይል በመፍጠር   የዛሬውን  የፕላን C እንቅስቃሴ  ማሥቆም እንደሚቻል አምናለሁ ። የእሾህ መድሃኒቱ እሾህ ብቻ ነው  ። ነፍሰ ገዳይን ልትገድለው ይገባሃል ። ያለ አንዳች ምህረት ።  የመንግሥት ተመጣጣኝ ይሉሃል ይኼ ነው  ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የደርግና የወያኔ የውይይት ክበብ - ከአንተነህ መርዕድ (ጋዜጠኛ)

ዛሬ በከንቱ የሚሞላቀቅብህን አንተ ዘረኛ እና በዩልንታ የተሸበብክ ካልሆንክ በሥተቀር ቸል ልትለው አይገባም ። ቸልታ ካበዘህ የታምራት ነገራ ትንቢት ይፈፀማል ።  ኦሮሞ ካልሆንክ ብቻ ሣይሆን አንተ “ ሰው ነኝ ። “ የምትል ኦሮሞ ከሆንክ አንተ በረሮ ነህና ትታረዳለህ ። የሚልህ  የግብፅ ቅጥረኛ ከእሥር በለቀቅኸወሰ ሃይል በፕላኒ ቢ የሚመራ ኃይል ነበር ። ዛሬ ወደ ፕላን ሲ ተሸጋግሮልሃል ።…

ይኽ  ኃይልበገንዘብ እጅግ የፈረጠመ በመሆኑ አንተን ገንዘብ በመሥጠት እያነሆለለ ፣ በተቀዳሚ ሥራህ ላይ እንዳታተኩር በማዘናጋት ወደ እርድህ እየገፋህ እንደሆነም እወቅ ። በቤትህ ውሥጥ ያለውን ወታደራዊ ዲሢፕሊንም መርምር ። ሥላለው ገንዘብ መናገር ከጀመረ እጅግ አደገኛ ሁኔታ ውሥጥ እንደምትወድቅ እወቅ ።የአገር መረመ በመሆንህም ጦሥህ ለአገር ይተርፋል ።

ገንዘብ  መንጋ የመፍጠር ችሎታ እንዳለው ጋሼ ጃዋር ትላንት አሜሪካ ሆኖ አሣይቶሃል ። ዛሬ በፕላን ቢ ደግሞ የበለጠ እያሥመሠከረ ወደ ፕላን ሲ ተሸጋግሮልሃል ። የተማረውን ይኸው በመንግሥት ዩኒቨርስቲ በኔት ወርኩ አማካኝነት ገንዘቡን እየረጫ ፣ ሃሺሹን እያሥማገ ያሥጮኸዋል ።  ያልተማረውን ደግሞ ፣ በየጫካው አሠልጥኖ  እና በየከተማው እራሥህ  የሠለጠንከውን ሚኒሻ መልምሎ በሃሰት ፕሮፖጋንዳው ጀንጅኖ ረብጣ ብር ከመክፈል ባሻገር  ሥጋ እያበላ ና አረቄ እያጠጣ  ነፍሰ ገዳይ እንዲሆነ ጫካ ወስዶ ሰው ያሳርዱሃል ።  አሠልጣኞቹም አትዮጰያዊ ናቸው ብለህ በአውሮፕላን ይዘሃቸው የመጡ የግብፅ ሠላየች ናቸው ይባላል ። እነዚህ ፀረ ኢትዮጵያዊያን  ከወያኔም ጋር ነበሩ … ። ተመሬያለሁ ያልከውን በየዩኒቨርስቲ ያለኸውን የዓለምን ተፈጥሯዊ የዘመናት ጉዞ  ፤ ” ከአፈጣጠሮ ጀምሮ ያለውን የቅርቡን የ 5000 ዓመት ጉዞ   ” ያለመረዳትህ በእጅጉ ይገርማል ደ “ ለእዚህ ይመሥላል የታሪክ ትምህርት እንደ አንድ ጠቅላላ እውቀት በየዩኒቨርስቲው እንዳይሰጥ እና ይህ ፍላሎታም ወጣት ዓለምን  ከሣይንሥ እና ከሃይማኖት አንፃር   እንዳያውቃት የተደረገው ?

ዛሬ በመላው ኦሮሚያ የሚስተዋለው ይኸው ታሪክን ያለሠረዳት  ድንቁርና ነው ። የግብፅ እና የቅኝ ገዢዎቻችን ሴራን ከታሪክ እና ከተፈጥሮ አንፃር ያለመረዳት ያመጣውም ጦሥ ነው ። ሙቅ የሚያኝኩት ባለ ረብጣ ብሮች ያሰማሯቸውን ፣ ከመንግሥት በላይ መንግሥት የሆኑትን ፣ ገዳይ እና አሠቃይ  ጋንጊሥተሮች በመፍራት መንጋ ሆኖ መገኘት የከሰተው ችግር ነው ።  …  ትላንት  በነጀነራል ጃጋማ ኬሎ ዘመን ቅኝ ገዢዎች ይህንኑ  የመከፋፈል እና የጭካኔ ሤራ ፈፅመዋል ። በአምሥቱ ዓመት የአርበኞች ትግል ወቅት ይኸው ተንፀባርቋል ። ዛሬ ና አሁን በጠቅላይ ሚኒሥቴር  አብይ አህመድ መዋቅር ውሥጥ   ለፈጣሪ ያደሩ ሰዎች  ሤጣንን ተዋግተው ማሸነፍ እሥካልቻሉ ጊዜ ድረሥ ይኸው ግፍ ይቀጥላል ።

ሆኖም ” ሊነጋ ሢል ይጨልማል ። ” እንደሚባለው ፣ ይህ ሰቆቃ ከፈጣሪ ጆሮ አልደረሰም ማለት እንዳልሆነ ሁሉም ማወቅ አለበት ። ሠላም ያለውም የሚገኘውም በእግዚአብሔር ነው ።  ዛሬ እና አሁን መንግሥት ይኽንን ተገንዝቦ ” ይበቃል ! ” እንደሚል ተሥፋ አደርጋለሁ ። ትላንት “ ፕላን C ይቀጥላል ። ይኽንንም ታዩታላችሁ ።” ብዬ እንደነበርም አትዘንጉ ! ይኽንን ያልኩት ፈጣሪ በሰጠኝ አእምሮ ያለማባራት ፣ የሚከሰቱ ፀረ – ሰው ድርጊቶችን    ገጣጥሜ በማየት ነው ። ይኽንን እውነት ፣ አገር ወዳድ  የመንግሥት የደህንነት ተቋም ዓባላት እና መከላከያ ሠራዊቱ እንዲገነዘብልኝ እፈልጋለሁ ። የኢትዮጵያ ጠላቶች ነገ “ በፕላን ዲ “ ሊከሰቱ እንደሚችሉም ቀድሞ በመረዳት ከወዲሁ መዘጋጀት እንዳለበትም ለማሳሰብ ነው   ። ትላንት ቀድሞ ቢዘጋጅ ኖሮ በኦሮሚያ ዩኒቨርስቲዎች  ፕላን C  በተቀናጀ መልኩ አይከሰትም ነበር ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share