December 2, 2022
6 mins read

አልቃሽ እና አወዳሽ  -ህዳር ፳፱  

ጉልቻ ቢለወጥ……ወጥ ላይወጠወጥ  ቢወጠወጥ ላይጣፍጥ…..ቃል በቃል ቢተካ ከጋጋታ ያለፈ ጠብታ እርካታ የለም ፡፡

ከግማሽ ክ/ዘመን በፊት ታላቁ ኢትዮጵያዊ የስነፅሁፍ ሠዉ ደራሲ ፣ዶ/ር ከበደ ሚካኤል “ የኢትዮጵያ ህዝብ እብደገብስ ዛላ ነፋስ የሚከተል  ”ብለዋል የሚል አንድ መልዕክት ከዓመታት በፊት ተመልክቸ ስለነበር ዞትር ስለ እኔ እና ስለእኛ ሳስብ  ነገሩ ዕዉነት ስለመሆኑ አስከዛሬ ድረስ ዕዉነትነቱን ለአፍታ አልጠራጠርም ፡፡

ከዚህም በላይ የታላቋ ኢትዮጵያ አስካሁን  የመጨረሻዉ መሪ  ኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም  “ህዝቤ ወርቅ ሲሉት….ጠጠር ” ይላል  እንዳሉ እንሰማለን፡፡

እዚህ ጋ ከላይ የመጨረሻዉ መሪ ያልኳቸዉ መንግሰቱ ኃ/ማርያም ለኢትዮጵያ አንድነት እና ለዜጎች ዕኩልነት በዕዉነት ፣ በነፃነት እና በፍትኃዊነት ….ለመስራት እናለመምራት በሙሉ ልበ ቅንነት ፣ ብቃት እና ኢትዮጵያዊነት ማንነት መስራታቸዉን በተግባር ስለምናይ እና ነገ ታሪክ እና ትዉልድ እንደ አርሳቸዉ ለአገር እና ለህዝብ ክብር እና ዳር ድንበር የሚኖር መሪ እንዲኖር በትብብር እንደሚሰሩ (ታሪክ እና ትዉልድ) ስለምገምት ነዉ ፡፡ ኢትዮጵያን ከተሟላ ሉዓላዊ ዳር ድንበር ፣የባህር በር ባለቤትነት ፣በኢትዮጵያ ህዝብ በማንኛዉም መልኩ የማይደራደሩ መሪ መሆናቸዉን እኛ ብንክድ የኢትዮጵያ ጠላቶች እና ዓለም ያዉቁታል፤ይመሰክሩታል፡፡

እኛ ኢትዮጵያዉያን በዕዉነት ፣በአገራችን የጋራ ጉዳይ እና በልዩነት ላይ ሳንግባባ በሀሰት ላይ እንዴት እንደምንግባባ ባይገባኝም ሳንግባባ እንደተግባባን ማስተጋባታችን ደግሞ የመጨረሻዉ የመዉረዳችን ምልክት እና ሳንሰማ እንደሰማን፤ ሳይገባን እንደገባን ….ማጨብጨብ የምናቆመዉ መቸ ነዉ ፡፡

የማይገባንን እስኪገባን ዝም ማለት እና መረዳትን ለምን ችላ እንላለን ፡፡ በሰሞነኛ ነገር እየሰከርን እንዴት እና አስከመቸ በሞት እሳት ቆመን እንረማመዳለን….እናጨበጭባለን፡፡ በራስ ጥፋት እና ሞት መደሰት  ዕዉነተኛ ደስታ የሚሆነዉ እንዴት እንደሆነ ባይገባንም ለአመታት አየነዉ ከሞት ወደ ህይወት ፣ ከዉድቀት ወደ ዕድገት እንጂ እንዴት  ጨርቅ እና ወርቅ እንድ ሲሉን ሁለት እያልን ወደ ሲኦል እንነዳለን፡፡

ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዉን የኢህአዴግ ህገ-ደንብ ሥራ ላይ የዋለበት ህዳር ፳፱ ቀን ሲታወስ አገሪቷ ላይ ይህ ህገ-ኢህአዴግ ስራ ላይ እንዲዉል እና ኢትዮጵያ እና ህዝቧ የክህደት እና ሞት ቋጥኝ ከተደፋባቸዉ ጊዜ አንስቶ ምን አገኘን ምን አጣን ሳንል እና በቁስል ስቃይ እና በገደል አፋፋ ሆነን በየሰሞኑ ሰሞነኛ መሆናችን ከህይወት እንደተቆረጠ ቅጠል ለራሳችን መጥፊያ እሳት ማቀጣጠያ መሆናችን ከገብስ፣ ጠጠር እና ጨርቅ ወርደን አጥፊ እና ጠፊ መሆናችንን ያሳያል፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ እና በተለይም ኢትዮጵያ እና በህገ-ኢህአዴግ የተረሱት ፣የተገለሉት ብዙኃን ኢትዮጵያዉያን ላለፉት ሶስት አስርተ ዓመታት የደረሰባቸዉ እና እየደረሰባቸዉ ስቃይ እና ተጭኗቸዉ ያለዉ የመከራ ቀንበር አስኪሰበር ህዳር ሀያ ዘጠኝ አልቃሽ እና አወዳሽ ሆና ማስተናገዷ አስከመች ይሆን ፡፡

ለኢትዮጵያ አንድነት እና ዘላቂ ዕድገት ሁሉንም ኢትዮጵያዉያን እና የኢትዮጵያን ግዛቶች የሚገልፅ ህገ-ህዝብ(ኢትዮጵያ) አስካልሰፈነ ጊዜ ድረስ ህዳር ፳፱  ከግንቦት ፳ ቀን መወለዱን ሳንረሳ እየተወሳ እነኝህ ሁለት ዕለታት “ መረሳትም፤ መወሳትም ” ለኢትዮጵያ እና ብዙኃን ኢትዮጵያዉያን ያስገኘዉ መት ወይስ ትሩፋት ብሎ መረዳት ቢመሽም  ጭለማዉ በርትቶ ባለመንጋቱ ይታሰብበት የምን መዘናጋት ፤ የምን ዳግም ጥፋት ለምንድነዉ መርሳት   ፡፡

 

አንድነት ኃይል ነዉ ፡፡

Allen Amber

 

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop