November 1, 2022
8 mins read

ዕዉነት እና ሞት  በምኞት አይቀርም

ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም.  ጦርነት የተጀመረበት ሳይሆን የስልጣን ክፍፍል እና ድልድል ስግብግብነት የተነሳ የጦርነቱ ማግስት ነዉ ፡፡

ይህም ጦርነት መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. መጀመሩን ያስታዉሷል፡፡ የአሮጌዉ ኢህአዴግ የስም ለዉጥ እና መንፈራገጥ  ሲጀመር  ከዓመታት በኋላ ተከታዩ ኢህአዴግ  “ብልፅግና ”ሲደላደል  የነባሩ አህአዴግ  ቁንጮ ትህነግ በተከታዩ ኢህአዴግ  እና በህገ- ኢህአዴግ /ህገ- መንግስት ተስፋ መቁረጥ የጫካዉን የ1960ዎች  ድብቅ አመል  በብሶት ሰይፉን ጥቅምት ሀያ አራት ሁለት ሽ አስራ ሶስት ዓ.ም. መዟል፡፡

EPRDF Prospertyfሆኖም ትህነግ ሳይነሳ እንዲወድቅ  የሆነዉ በራሱ የማይደርቅ  የጥላቻ እና የበላይነት ዕብሪት ዕኩይ ፍላጎት  ኢትዮጵያን ለማፍረስ እና የዓማራን ህዝብ ዳግም ወረራ እና ምዝበራ ለማካሄድ ጦርነት ተከፈተ ፤ በዓማራ እና በኢትዮጵያ ህልዉና እና ደህንነት ፡፡

ጦርነቱ ሲያገርሽ   የትህነግ በትግራይ ምርጫ ማካሄድ እና ይህም ነባር እና ተከታይ ኢህዴግ ህገ- መንግስት መሰረት አድርጎ የነበር ትንቅንቅ ነበር ፡፡

ለዚህም የተከታይ ኢህአዴግ የህግ-የበላይነት ለማስከበር ሲል አባት ትህነግ-ኢህአዴግ በህገ መንግስት -ህገ ኢህአዴግ መሰረት በህዝብ ምርጫ የተገኘ የክልል አስተዳደር ኃላፊነት ነዉ የሚል ነበር ፡፡

በዚህ መኃል ወረራ እና ዳግም ምዝበራ የታወጀበት የዓማራ ህዝብ ህልዉናዉን በክንዱ ለማስከበር የህልዉና እና የብሄራዊ ደህንነት የመራጋገጥ ትግል ማድረግ እንዳለበት አዉቆ የመከላከል መስዋዕትነት ከፍሏል፡፡

በዚህም ሁለቱንም የጉየጦርነቱ መነሻ እና መዳረሻ ተዋናያንን  በመታደግ አሁን ባሉበት ደረጃ እንዲደርሱ እና አሁን ላይ ለመነጋገር እና ለመደራደር በማብቃት ምክነያት ሆኗል፡፡

ዛሬ ላይ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና የዳር ድንበር ጉዳይ ለድርድር ማቅረብ ሌላዉ ከጦርነቱ እና ከሚጠበቀዉ የአባት እና ልጂ ስምምነት ጋር የሚጣረስ ነዉ ፡፡

የጦርነቱ ጅምር እና የስምምነቱ እንደምታ  የብሄራዊ እና የሉዓላዊነት ጉዳይ ከሆነ የሱዳን የኢትዮጵያን ግዛት መያዝ፣ከኢትዮጵያ ግዛት የኤርትራ ጦር አለ ፤ይዉጣ የሚሉት ትህነግ እና ግብረ አበሮች ዕዉነት ከሆነ በድርድሩ ሱዳን፣ኤርትራ፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የዓመታት የዕልቂት እና ሞት ቀንበር ተሸካሚ -ዓማራ ህዝብ መኖር እና መተባበር ብቻ ነዉ በድርድሩ የኢትዮጵያ እና ህዝቧ ኅልዉና እና ብሄራዊ  አደጋ ከስጋት ሊድን የሚችለዉ ፡፡

የህዝብ እና የብሄራዊ ዳርድንበር ሉዓላዊነት ስጋት መባል ያለበት የፖለቲካ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ከዚህ በላይ የኢትዮጵያ አንድነት ፣የህዝቦች ሉዓላዊነት እና የዓማራ ህዝብ ሠባዊ፣ ተፈጥሯዊ ፣ ብሄራዊ እና ዓለማቀፋዊ መብት እና ነፃነት ዕዉን የሚሆንበት አዉድ ሲኖር እና ሲረጋገጥ ብቻ ነዉ ፡፡

የዘገየ ዕዉነት  ዉሸት እንደማይሆን ሁሉ የዘገየ ሞትም እንደማይቀር  በማወቅ ለማይቀረዉ ግን ለሚድበቀበቀዉ የብሄራዊ  አንድነት እና ሉዓላዊነት ሥጋት በሆኑት የዉስጥ ነቀርሳዎች ላይ ሳይቃጠል በቅጠል ብሎ መፍትሄ መሻት ያስፈልጋል፡፡

ከየትኛዉም ቡድን ጥቅም እና ፍላጎት በላይ ህዝብ እና የአገር ሉዓላዊነት ጥቅም ፤ስም እና ችግር ቅድሚያ ሊሰጥበት ይገባል ፡፡

በኢትዮጵያ የቆ ታሪክ እና መልካምድራዊ አቀማመጥ የኢትዮጵያ ግዛት አካላት የነበሩትን የጎንደር ፣ የወሎ እና የጎጃም ክ/ሀገር ግዛቶች አካላትን ወልቃይት፣ ራያ እና መተከል  ብሄራዊ የግዛት አንድነት ስጋት የሆኑት ትህነግ እና ግንባር ድርጂቶች በህገ- ኢህአዴግ ጠርንፈዉ የተከሉት“ ዕሳት እና ሥጋት ነዉ” ፡፡

ለዚህ ነዉ ጦርነቱ ቅድመ ሆነ ድህረ  1983 ዓ.ም  መነሻዉ የባተዉ ያን ጊዜ ነዉ ፡፡ ዛሬ የጥቅም ግጭት እንጂ  የብሄራዊ ስጋት  አሜኬላ ብቅለት ያኔ ከግማሽ ምዕተ ዓመት አስቀድሞ ነበር ፤ነዉ ፡፡

ኢትዮጵያ የምትድነዉም ፤የምትታመመዉም  በራሷ ልጂ ነዉ ፡፡ ከራሷልጆች ዉስጥ ይህ ክማሽ ክ/ዘመን ዓመታት በፊት ጀምሮ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና የህዝብ ህልዉና ስጋት ዳፋ ቀማሽ የሆነዉን የኢትዮጵያን ህዝብ እና ዓማራ ህዝብ ነፃነት እና ህብረት ጆሮ ሊሰጠዉ ይገባል፡፡

ህገ -ኢህአዴግ ለዘመናት አግላይ እና ገዳይ ሆኖ በኖረበት ከህዝብ እና አገር ጥቅም በላይ የሚታይ የፖለቲካ ጥቀም እና ወገንተኝነትም ሆነ ህግ በኢትዮጵያ ሠማይ ስር  ከኢትዮጵያ እና ከብዙኃን ህዝብ በተለይም ከዓማራ ህዝብ ህልዉና እና ነፃነት መፃኢ ሁኔታ አኳያ መቃኘት እና መታየት አለበት ፡፡ሁላችንም ግማሽ ዕዉነት  አለመኖሩን አዉቀን ከታሪክ እና ከነባር ብሄራዊ ችግር በመማር ወደ ሙሉ ነጻነት እና ዕዉነት መትጋት ይጠበቅብናል፡፡

ወደድንም ጠላንም ዕዉነት እና ሞት በምኞት አይቀርም ፡፡

“አንድነት ኃይል ነዉ !”

Allen Amber

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop