April 27, 2014
5 mins read

ጃኪ ጎሲ ተሾመ አሰግድን ይቅርታ ጠየቀ

በApril 24, 2012 ዓ.ም የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ዕትም ላይ ዝነኛው ድምጻዊ ተሾመ አሰግድ “በጠራራ ጸሐይ ተዘረፍኩ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፍረደኝ” ሲል ድምጻዊ ጎሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ) ካለፈቃዴ “የኔ አካል” የሚለውን ተወዳጅ ዘፈኔን ወስዶ ተጫውቷል በተቃውሞ ነበር። ከጊዜ በኋላ ድምጻዊ ጃኪ ጎሲ በጆሲ ሾው ላይ በመቅረብ “ከዚህ በኋላ ተሾመ ይህን ዘፈን የኔ ነው ብሎ መጠየቅ አይችልም፤ ለዜማና ግጥም ደራሲዎቹ ከፍዬበታለሁ” ሲል ተናግሮ እንደነበርም ይታወሳል።

ጃኪ ወደ ሰሜን አሜሪካ ሲመጣ ይታየው የተባሉ ጸሐፊ “ድምጻዊ ጎሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ) ከተሾመ አሰግድ ለወሰደው ዘፈን ይቅርታ ይጠይቅ ይሆን? ወይስ ማን አለብኝነት ያልፈዋል?” ሲሉ ተሾመ ከዚህ ቀደም የሰጠውን ቃለምልልስ በመጥቀስ አስተያየት ጽፈው ነበር። ወደ ኢትዮጵያ ሙዚቃ ኮከብነት እየተጓዘ የሚገኘው ጃኪ ይህን አስተያየት በብልህነት የተመለከተው ይመስላል። በዚህም መሠረት ትናንት በዋሽንግተን ዲሲ ባደረገው የመጀመሪያው የሰሜን አሜሪካ ኮንሰርቱ ላይ ሰው ባልጠበቀው ሁኔታ ዝነኛውን ድምጻዊ ወደ መድረክ በማምጣት አብሮት “የኔአካል” የሚለውን ተወዳጅ ዘፈን ካቀነቀኑ በኋላ ድምጻዊ ጃኪም ካለፍቃዱው ወስዶ በመስራቱ ይቅርታ ጠይቋል። ጨምሮም ዘፈኑን የሰራው ከመውደዱ የተነሳ እንደሆነ ገልጿል። አርቲስት ተሾመ አሰግድም “እዚህ ሃገር ሰንመጣ መንገዱን ያሳየን ሰው አልነበረም። ጥረታችን የቀድሞ ሙዚቃኞቻችን ውለታ እንዲህ በቀላል እንዳይረሳ ሙዚቃዎቹን ስትጫወቱ በፈቃድ ጥያቄ ጠይቃችሁ ተጫወቱ። [የኔ አካል] ከኔ በበለጠ ጃኪ ተጫውቶታል። አብልጦ ነው የተጫወተው፤ ሞቅ አድርጉለት” ብሎ አርቲስቱም ይቅርታውን ተቀብሏል። ጃኪም የሕዝብ ድምጽን ማድመጡ፤ ከምንም በላይ ይህን ስመጥር አርቲስት በመድረክ ጋብዞ እንዲታወስ በማድረጉ ዘ-ሐበሻ አድናቆቷን በዚህ አጋጣሚ እየገለጸች፤ አንባቢዎች በዘ-ሐበሻ የተጀመረው የጃኪና የተሾመ ጉዳይ መቋጨቱን በዚህ አጋጣሚ እንገልጻለን። መልካም የሥራ ዘመን ለሁለቱም።
የይቅርታውን ስነስርዓት ቪዲዮ ይመልከቱ

የግርጌ ማስታወሻ ጥቂት ስለስመጥሩ አርቲስት ተሾመ አሰግድ፦
በኢትዮጵያ ስመ-ጥር ከሆኑ ድምጻዊያን መካከል የሆነውና ብዙዎች “ኢትዮጵያዊው ስቲቭ ዎንደር” የሚሉት ተሾመ አሰግድ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በመስከረም ወር 1945 ተወልዶ በተወለደ በ5 ወሬ ዓይነ ስውር መሆኑን በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 2 ላይ በሰጠው ቃለ ምልልስ መናገሩ ይታወሳል። የመጨረሻ ካሴቱን ካወጣ 17 ዓመት ያለፈው ይህ ድምጻዊ እስካሁን ስንት ካሴቶችን ሰርተሃል በሚል ጥያቄ አቅርበንለት “ጥቂት ካሴቶችን አውጥቻለው:: ትዝታና ባቲ በሚባለው የሙዚቃ ቅኝት በፊሊፕስ አሳታሚነት በ1960ዎቹ አንድ ሸክላ አውጥቼ ነበር:: ከዛ በተረፈ ያልተሳካለት አንድ ካሴት ሰርቼ ነበር:: ከዛ ወዲህ ግን ጅቡቲ ለ5 አመታት ከቆየው በሗላ ከሮሀ ባንድ ጋር በመሆን ‘የኩባያ ወተት”ን ሰራሁኝ:: ይበልጥ ከሕዝብ ጋር ያስተዋወቀኝም ይሄ ሥራ ነው:: በሌላ በኩል ከነራሄል ዮሐንስ; አሰፉ ደባልቄ እና ኬኔዲ መንገሻ ጋር አንድ ካሴት; እንዲሁም ከማርታ አሻጋሪ; በዛወርቅ አስፋው እና ኤልያስ ተባባል ጋር በመሆን አንድ ኮሌክሽን ሰርቼ ነበር:: በራሴ በኩል 2ኛውን ሙሉ ካሴቴን “ደርባባዬ’ን አውጥቼ ነበር:: ብዙም በሕዝብ ዘንድ አልገባም:: ግን አልፎ አልፎ ሰዎች ያውቁታል::” ሲል መልሷል።

1 Comment

  1. Weregoch.were ena alubalta tetachu kumneger seru.your jornalizem quality is very poor you try hard to discourage jaki Josi but you are not successful .

Comments are closed.

gelemso
Previous Story

የክርስቲያንና የሙስሊም ፍቅር በገለምሶ (አፈንዲ ሙተቂ)

Gurage Kilele
Next Story

መንግስት በደቡብ ጉራጌ ዞን ከእምድብር ከተማ ወጣቶች ጋር በስተርጅና “ሌባና ፖሊስ” ጨዋታ እየተጫወተ ይገኛል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop