October 2, 2024
12 mins read

ኳሷ ያላችው እስክንድር ነጋ ጋር ነው – ግርማ ካሳ

Eskinder

እስክንድር ነጋ በኢትዮ360 ቀርበ ነበር፡፡ ማስታወቂያውን አስቀድሞ ስለሰማሁ ቃለ ምልልሱን አደመጥኩት፡፡

እንደሚታወቀው፣ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ አንድነት ድርጅት የሚባለውን መቋቋምና፣ የድርጅቱ መሪ እስክንድር ነጋ መሆኑን ተከትሎ፣ ከሶስት ወር በፊት በፋኖ አመራሮች መካከል ውዝግብ ተነስቶ፣ አብዛኛውን ህዝብ አንገት ማስደፋቱ የሚታወስ ነው፡፡

በቃለ ምልልሱ እስክንድር ነጋ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ አንድነት ድርጅት አመሰራረት ሂደት በዝርዝር ለማሳየት ሞክሯል፡፡

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ አንድነት ድርጅት ከተቋቋመ ሶስት ወር ሆኖታል፡፡ አሁንም ከዚህ ድርጅት ጋር በተገናኘ፣ እስክንድር ነጋ በሜዲያ ቀርቦ ማብራሪያ ለመስጠት፣ ህዝቡን ለማሳመን መሞከሩ፣ ድርጅቱ ከህዝብ ቅቡልነት አንጻር ችግር እንዳለበት አመላካች ነው፡፡ ያ ባይሆን ኖሮ በስንት አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ አስተያየት መስጠት ሲገባው፣ ከሶስት ወራት በኋላም ድርጅቱን ለህዝብ ለመሸጥ ባልሞከረ ነበር፡፡ አንድ በሉ፡፡

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ አንድነት ድርጅት የግለሰቦች ሳይሆን ድርጅቶች በጋራ የመሰረቱት እንደሆነ እስክንድር ያስረዳል፡፡ ሰባት ድርጅቶች፣ በሻለቃ ባዬ የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎንደር፣ በዘመነ ካሴ የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ በምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ ወሎ እዝ፣ በአቶ አሰገድ መኮንን ይመራ የነበረው፣ አሁን በኢንጂነር ደሳለኝ የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ እዝ፣ በሻለቃ መከታው የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ፣ በሻለቃ ሃብቴ ወልዴ የሚመራው የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝና ፣ በራሱ በእስክንድር የሚመራው እንድ እዝም ሊቆጠር የማይገባው የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት ናቸው፡፡

እነዚህ ሰባት ድርጅቶች አመቻች ኮሚቴ ሲመርጡ፣ የድርጅቱ ስምና መተዳደሪያ ደንብ ሲያጽድቁ በሙሉ ስምምነት ( unanimous consent) እንደሆነ ነው እስክንድር የገለጸው፡፡ ያንንም ተከትሎ ሁሉም የቃል ኪዳን ሰነድ ፈርመዋል፡፡ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ አንድነት ድርጅትም የእስክንድር ድርጅት ሳይሆን ሁሉም ፋኖዎች፣ እነ ዘመነ ካሴን ጨምሮ፣ ያቋቋሙት ድርጅት ነው ማለት ነው፡፡ ከሌሎች ምንጮችም ያሰባሰቡት መረጃ የሚጠቁመው፣ የቃል ኪዳን ሰነድ እስኪፈረም ድረስ የነበረውን ሁኔታ እስክንድር እንደገለጸው ነው፡፡ ሁለት በሉ፡፡

95% የሚሆነውን ጨርሰው፣ ችግር የተፈጠረው መጨረሻ ላይ መሪ ማን ይሁን በሚለው ላይ ነው፡፡ ቀደም ሲል እንደነበረው ሁሉም የተስማሙበት መሪ ቢመርጡ ኖሮ፣ ምርጫ የሚለውን ትተው፣ በ unanimous consent ቢያደረጉት ኖሮ፣ ሁሉም የሚቀበሉት መሪ ከሌለ የቡድን አመራር (collective leadership) ቢያደረጉት ኖሮ ሂደቱ 100% በስኬት ይጠናቀቅ ነበር፡፡ ትልቁ ስህተት የተሰራው እንግዲህ እዚህ ጋር ነው፡፡ ጉዳዩ የህልውና ትግል ሆኖ፣ የቆንጅና ውድድር ይመስል፣ ወይንም በሰላም ጊዜ የሚደረግ የፖለቲካ ፉክከር ይመስል ወደ ምርጫ መኬድ አልነበረበትም፡፡

ለዚህ ስህተት ደግሞ እስክንድር ብቻ አይደለም ተጠያቂው፤ ሁሉም የፋኖ መሪዎች እነ ዘመነ ካሴም ሳይቀር ተጠያቂዎች ናቸው፡፡፡ ሁሉም ተሳስተዋል፡፡ አንዱን ኮንኖ ሌላውን ከፍ ማድረግ አይገባም፡፡ ሶስት በሉ፡፡

ወደ ምርጫ ሲገባ መጀመሪያ ሶስት በኋላ ሁለት እጩዎች እንደቀረቡ እስክንድር ይናገራ፤ል፡፡ ሶስተኛው እጩ ማን መሆኑን ባይገልጽም፣ እኔ ባለኝ መረጃ ሶስተኛው እጩ አቶ አሰገድ መኮንን ነበር፡፡ በኋላ አቶ አሰገድ ራሱን ከእጩነት ያወጣል፡፡ ዘመነ ካሴና እስክንድር ነጋ ብቻ ቀሩ፡፡

ዘመነ ካሴ፣ የዝናቡን፣ የምሬንና የአስገድን ድምጽ ብቻ እንዳገኘ እስክንድር ነጋ ይናገራል፡፡ ከዚያ በኋላ ስብሰባው ይቋረጣል፡፡ ሂደቱ ሊቀጥል አልቻለም፡፡ በሌላ ጊዜ እንደገና ሂደቱ በአዲስ ለማስጀመር እንደተሞከረ መሰብሰብ እንደተቻለ እስክንድር ይናገራል፡፡

ስብሰባው፣ በመጨረሻ የተደረገው ስብሰባ ሲሆን የስብሰባውም ይዘት በሚያሳዝን ሁኔታ እንዲለቀቅ ነው የተደረገው፡፡ በነዚህ በተለቀቁ ኦዲዮውች የፋኖ ስም ነው የተዋረደው፡፡ ህዝብን አንገቱን እንዲደፋ ነው የተደረገው፡፡

መጀመሪያ ላይ እስክንድር ነጋ በሰብሰባው እንዲሳተፍ ሲጠየቅ፣ አቶ አሰገድ መኮንን፣ “የትኛውን ኃይል ነው የሚመራው ? እንደ ፋኖ እዝ አንድ ጠቅላይ ግዛትን ወክሎ ይምጣ እንጂ፣ በራሱ እስክንድር መሳተፍ አልነበረበትም” የሚል ተቃውሞ አስሞቶ ነበር፡፡ እነ አስረስ ማሬ ፣ እነ ምሬ ወዳጆ ፣ ከአቶ አሰገድ ጋር ተስማምተው፣ መጀመሪያዉኑ እስክንድር ነጋ በሰብሰባዎቻቸው እንዲገኝ መፍቀድ አልነበረባቸው፡

በዚህ ስብሰባ እስክንድር ነጋ ለእጩነት ቀረበ፡፡ የእስክንድር ነጋን እጩነት የተወሰኑ መሪዎች ተቃወሙ፡፡ መስፈርት ያሟላል፣ መስፈርት አያሟላም የሚል ክርክር ተነሳ፡፡ ዘመነ ለእጩነት ሲቀርብ ምንም ያላሉ፣ እስክንድር ሲቀርብ ያን ያህል፤ ተቃውሞ ማስነሳታቸውና ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸው ተገቢ አልነበረም፡፡ መጀመሪያዉኑ በምርጫ መሪ እንዲመረጥ መስማማት አልነበረባቸውም፡፡ አራት በሉ፡፡

ከዘጠኝ አመራሮች አራቱ ከተቃወሙ በኋላ፣ ከዚያ በመቀጠል የነበረውን ሂደት እስክንድር ነጋ አላብራራም፡፡ ቃለ ምልልሱ በዋናነት እርሱን ትክክለኛና ዴሞክራሲያዊ ሌሎችን ችግር ፈጣሪ አድርጎ ለመክሰስ ነው የሞከረው፡፡ ይህ በራሱ የእስክንድርን አካሄድ አደገኛነት አመላካች ነው፡፡ በሂደቱ እርሱም ተጠያቂ ነውና፡፡

“እኛ ከፈለግን መሪነቱን ልንሰጣቸው እንችላለን፡፡ የስልጣን ችግር የለብንም፡፡ ግን ህግ መከበር አለበት፡፡ እነርሱ የበላይ እኛ የበታች፣ እነርሱ የፈለጉት ካልሆነ ብለው የፈለጉት እየሆነ እኛ ደግሞ ከነርሱ በታች ሆነን ልንቀጥል አንችልም፡፡ በድርጅቱ ውስጥ ሁላችንም እኩል መሆን አለብንም” የሚል አስተያየት ሰጥቷል፡፡ ይህ ትክክለኛ አባባል ነው፡፡ አንዱ የበላይ፣ ሌላው የበታች ሊሆን አይችልም፡፡

እሺ የስልጣን ችግር ከሌለበት፣ ፍላጎቱ በፋኖ አደረጃጀቶች ውስጥ ማንም የበላይ ሳይሆን፣ በቅንነት፣ በእኩልነት ፣ በመከባበር ትግሉን መምራት ከሆነ፣ ለምን ከመሪነቱ ተነስቶ፣ የቡድን አመራር እንዲኖር ሁኔታዎችን አያመቻችም ? እስክንድርን ተክቶ ዘመነ ካሴ መሪ መሆን አይችልም፡፡ ማንም ዘመነ በእስክንድር ነጋ ይተካ ያለ የለም፡፡ እነ ዘመነ ካሴን የሰሩት ስህተቶች ገብቷቸው፣ ባለኝ መረጃ፣ አሁን እነርሱም፣ መሪ እንሆን እያሉ አይደለም፡፡ የቡድን አመራር መኖሩንም ይደግፋሉ፡፡

እስክንድር ነጋ ወደ ጫካ ስገባ፣ አብረውት ወደ ሰማኒያ ፋንዎች እንደነበሩ፣ ከነርሱ 15 ሕይወታችው እንዳለፈ ገልጿል፡፡ እነዚህ ጀግኖች እግዚአብሄር ነፍሳቸውን ይማር፡፡ታዲያ እስክንድር፣ ለነዚህና ለሌሎችም የተሰው ፋኖች ክብር፣ አሁንም በየጫካው ከዘረኛው አገዛዝ ጋር እየተፋለሙ ላሉ ፋኖዎች ደህንነት፣ ለአገርን ለህዝብ ሲል፣ ለምን ከግትር አቋሙ ፈቀቅ ማለት ተሳነው ? ለምን እርሱንም ያካተተ የቡድን አመራር እንዳይኖር በሩን ይዘጋል ? ለምን በሽማግሌ ወይንም በውስጥ መስመር ከርሱ ጋር ካልተስማሙት ጋር ከመነጋገር በሜዲያስ ወጥቶ ሌሎች የፋኖ መሪዎችን ይኮንናል ?

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ስሙ፣ ህገ ደንቡ ሁሉም በሙሉ ስምንነት ከጸደቁ፣ ችግሩ የነበረው አመራር ላይ ከሆነ፣ ድርጅቱን ማፍረስ ባይገባም፣ የተሰራው 95% እንዳለ ሆኖ፣ ከምርጫ በፊት ወደነበረው ሂደት ብቻ በመመለስ፣ የቡድን አመራር (collective leadership) እንዲኖር ማድረግ አስቸጋሪ አይመስለኝም፡፡ እንግዲህ ኳሷ ያላችው እስክንድር ነጋ ጋር ነው፡፡

3 Comments

  1. ግርማ ካሳ በተራ ቁጥር ፬ ዘመነ ካሴን ተቀብለው እስክንድርን ያለመቀበላቸው ያልከውን ብታጠራልን። ከጽሁፍህ እንዳየነው እስክንድር ያለው ጦር 80-15 ሁኖ ሳለ ስም ያለው የሚመራው ጦር ሳይኖር ለምሳሌ የወሎ፣ የጎንደር•••እንዴት ቦታን ወክለው ከመጡት ጋር አንድ ሊሆን ይችላል? እርግጥ እስክንድር የአዲስ አበባን ፋኖ መስርቶ በአካባቢው ቢንቀሳቀስና እነሱን ወክሎ ቢገኝ ምክንያታዊ ይሆን ነበር እዚህ ላይ የቀድሞ ጥረቱንም ዘንግቼው አይደለም። ዘመነንና እስክንድርን ያመሳሰልክበትን መንገድ ብታስታርቅልን።

  2. Ato Girma better shut up rather than perpetuating ur wishful thinking. Disreagading the universal fact, that Eskindir Nega is the only one who kindeled FANO survival struggle. U try in vain to give more cradiet to the former ANDM surrogates rather. You better stop ur nonsense regading Eskindir Nega the great. In Addis Ababa in his birth place he has been persecuted by so savage Gallas lead by Abiy Ahemed and Shimels, recent nomadic settlers in Shoa Ethiopia. since 1750 AD.

    • I used to think the same way about Eskinder until the last interview he gave to Ethio360. He is another power monger, not a democrat. He doesn’t have Amhara humbleness.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

1
Previous Story

ጦርነቱ አማራ ክልል ብቻ ከመሰለን ተሳስተናል!

193903
Next Story

”ኦሮሞ አያመሰግንም” ዐቢይ ፤ ”ላሟም ጥጃዋም የኦሮሞ ሆናለች” ሽመልስ

Latest from Blog

blank

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ
blank

ፖለቲከኛው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት ፖለቲከኛው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል
blank

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ
blank

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop

Don't Miss