ገንቢ ፀፀትንና ልባዊ ይቅርታ መጠየቅን እየሸሸን ፈፅሞ የትም አንደርስም!

June 29, 2024
ጠገናው ጎሹ

በዚህ ሂሳዊ አስተያየቴ ከሰሞኑ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በኢትዮጵያ የአሚሪካ አምባሳደር ጋር ስለ አደረጉት ውይይት በፎቶ ግራፍ ተደግፎ የቀረበ ዜናን መነሻ ያደረገ ነው። ይህንን እንደ ምሳሌ/እንደ ማሳያ ተጠቀምኩበት እንጅ በዚህ ረገድ ያለብን ፈተና ዘርፈ ብዙና ሥር የሰደደ (wide and chronic)  የመሆኑን መሪር እውነትነት ዘንግቸው አይደለም።

በመሠረቱ  እጅግ አስከፊ በሆነ ፖለቲካ ወለድ መከራና ውርደት ወስጥ የሚጓጉጠው  (የመከራ ዶፍ ሰለባ የሆነው) ህዝብ  የሚያሳስበውና የሚቆጨው ማነኛውም ኢትዮጵያዊ በግልብም ሆነ በቡድን በየትማኛውም ጊዜና ቦታ አወንታዊ አስተዋፅኦ የማድረጉ አስፈላጊነት የሚያጠያይቀን አይመስለኝም።    ይህ ማለት  አስፈላጊና ገንቢ የሆነ ሂሳዊ  አስተያየት  (ትችት)  አያስፈልግም  ወይም ይህንን ማድረግ አላስፈላጊ ተጠራጣሪነትን እንደ ማራመድ ተደርጎ መወሰድ አለበት ማለት አይደለም።።

ከዚህ አንፃር ነው የሁለቱ  ግለሰቦች ከአሚሪካ ከፍተኛ ዲፕሎማት ጋር የመነጋገራቸውን ዜና በመልካም ዜናነት መቀበል ትክክል ቢሆንም ጥያቄ ማንሳትም ተገቢ የሚሆነው። ያለምንም ጥያቄና ሂሳዊ አስተያየት ወይም ያለምንም እንከን አልባነት ማለፍ ግን ትክክል አይሆንም። ፈፅሞ አይጠቅምም።

እንደ መግቢያ ይህንን ካልኩ ወደ ጥያቄ አዘል አስተያየቴ ልለፍ።

1) መቸም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወለድ መከራና ውርደት ያሳስበኛል ከሚል አካል/ወገን ጋር ስንነጋገር የአማራ ፋኖ እና የሌሎች የትግል ባለድርሻዎችና ተጋሪዎች  ጉዳይ መነሳቱ አይቀርምና በዚህ ረገድ ተገቢው ጥንቃቄና ፖለቲካዊ ጥበብ ሊኖረን ይገባል።ምክን ቱም  ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አደረጃጀቱና ፍኖተ ካርታው ወደ ዴሞክራሲያዊ  የአንድነት ብስራት አዋጅና የተግባር ውሎ ተሸጋግሮ ለዚህ የድል ግስጋሴው ያግዝ ዘንድ ማንዴት/ይፋዊ ሃላፊነት ካልተሰጠን በስተቀር በግል ወይም በቡድን  ደጋፊነት ከምናደርገው አስተዋፅኦ አልፈን መሄድ ያለብን አይመስለኝም። የአነዚህ ሁለት ወገኖች (የገዱና የይልቃል) የጥረት ይዘትና አቀራረብ ከዚህ አንፃር ስለ መሆኑ ወይም ስላለመሆኑ እርግጠኞች ነን ይሆን?

2) ሀ/ በተለይ ደግሞ እንደ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አይነት ከወጣትነት እስከ ባለ ግራጫ ፀጉር የእድሜ ርዝማኔ የህወሃት ኢህአዴግ እጅግ እኩይ ዓላማ  አስፈፃሚ እና ራሱን ብልፅግና ብሎ የሰየመው እጅግ ሴረኛና ጨካኝ የኦህዴድ-ኢህአዴግ ጉልቾች አንዱ በመሆን “እኛ ለሥልጣን ሳይሆን ለአገር ስንል ነው” የሚል እና የፖለቲካ ሥልጣን ከመያዝ እውነታና ወሳኝነት አንፃር ሲታይ እጅግ የወረደ ዲስኩር የደሰኮረ እና በአብይ አህመድ በቅጡ እንኳ ሳይነገረው ከወንበር ወንበር እያቀያየረ መናገር የሚችል አሻንጉሊት አድርጎ ሲገለገልበት የነበረ ሰው ሌላው ቢቀር ከምር የሆነና ገንቢነት ያለው ፀፀትና ይቅርታን ለመግለፅ የሞራል አቅም የተሳነው ምን አይነት ትርጉም ያለው ግብአትነት እንዳለው መጠየቅ በደምሳሳው ማግለል የሚሆነው እንዴት ነው? ለ/ ከምንም በፊት ከምር የሆነ ፀፀትንና ይቅርታን በግልፅ እና መሪር አስተማሪነት ባለው የፖለቲካና የሞራል ሰብእና ለመግለፅ ወኔው ከሌለን ለግዙፉና ለመሪሩ የነፃነትና የፍትህ ተጋድሎ አስተዋፅኦ የምናደርገው እንዴት ነው?  ሐ/ በፊትም የህወሃት እኩያን የፖለቲካ ኢሊቶችን እና በኋላም የኦህዴድ/ብልፅግና ተረኞችን እኩይ ዓላማና አጀንዳ እጅ እያወጡ በማፅደቅ እንደ ደመ ነፍስ እንስሳት ከርሳቸውን ከመሙላት ያለፈ ሚና የሌላቸው የፓርላማ አባላት (ካድሬዎች) ስብሰባ ላይ  ዘመናት ያስቆጠረውን የህዝብ መከራና ውርደት የሚያንፀባርቅ ዲስኩር ማስማትን በአወንታዊነት ማየት ተገቢ ቢሆንም እውነተኛ በሆነ ፀፀት እና ገንቢ በሆነ (ከምር አስተማሪ በሆነ ይቅርታ) ካልታጀበ በእጅጉ ጎደሎ የሆነ የፖለቲካ ሰብእና አይሆንም እንዴ? መ/ እንዲህ አይነት የፖለቲካና የሞራል ግልፅነትና ልዕልና የሚጎላቸው ወገኖች  አያድርገውና የሥርዓት ለውጥ ትግሉ ቢከሽፍና እኩያን ገዥ ቡድኖች የካድሬነት የመመለሻ በር ቢያዘጋጁ  ሰንካላና ወራዳ የሰበብ ድሪቶ እየደረቱ የመጀመሪያ ተሰላፊዎች ሊሆኑ እንደማይችሉ ምን ያህል እርግጠኞች ነን? ሠ/ የፖለቲካ ባህላችንና ታሪካችንም የዚህ አይነት አሳፋሪና መሪር ተሞክሮ ደሃ ነው እንዴ?  ረ/ ለመሆኑ እንደ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የመሰለ የእኩያን የጎሳ አጥንት ስሌት ፖለቲካ ፈጣሪና አስፋፊ ሥርዓትን በፍፁም ካድሬነት ከልጅነት እስከ ግራጫ ፀጉር እድሜ   አገልግሎ   በቃኝ ብሎ የተሰናበተን  ፖለቲከኛ የታሰበበት፣ የተደራጀና የተቀነባበረ፣ አካፈን አካፋ ብሎ ለመጥራት የማይገደው፣ ምን መደረግ አለበት የሚለውን ጥያቄ ቀጥተኛና ግልፅ በሆነ አቀራረብ ለመመለስ የሚችል ፣ እና እውነትም ከልብ በመፀፀት  ለነፃነትና ለፍትህ ትግሉ ጉልህ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው  የሚያሰኝ ያላሳለሰ ጥረት ሲያደርግ አላየንም/አልሰማንምና እንዲህ አይነቱን ፖለቲከኛ ምነው ብቅና ጥልቁ? ብሎ መጠየቅ ፖለቲካዊ ነውር  ነው እንዴ?

3)  ለብዙ ዓመታት በካድሬነትና በባለ ሥልጣንነት ተዘፍቀው የኖሩበትን ሥርዓት በሆነ ምክንያት ለቀው ሲወጡ ምንም ስህተት እንዳልሠሩ ያለምንም  ፀፀትና ይቅርታ ስለ ነበሩበት እኩይ የፖለቲካ ሥርዓት እንደ አዲስ ሲነግሩንና ሲተነትኑልን እኔስ/እኛስ ? ለማለት ፈፅሞ ወኔ የሌላቸው አቶ ገዱ አንዳርጋቸውንና አንዳርጋቸው ፅጌን የመሰሉ ወገኖችን በግልፅና በቀጥታ ፖለቲካዊው አመጣጣችሁና አኳኋናችሁ በእጅጉ ጎደሎ ነውና ህሊናችሁን ከምር መርምሩ ማለት  ካልቻልን ስለ የትኛው እውነተኛና ዘላቂ የነፃነትና የፍትህ  ሥርዓት ነው የምናወራው? ይህንን ከምር ወስደውና መርምረው በትክክለኛው ፍኖተ ነፃነትና ፍትህ ላይ ለመገኘት ፈቃደኞችና ዝግጁዎች የማይሆኑ ወገኖችን (ግለሰቦችን) ማባበል ግዙፍና መሪር ዋጋ የተከፈለበትንና እየተከፈለበት ያለውን መሠረታዊ የሥርዓት ለውጥ ትግል ይጎዳል እንጅ ፈፅሞ አይጠቅምም ብሎ መከራከር ትክክል ካልሆነ ሌላ ምን?

4) አንዳንድ ሁኔታዎችን (አጋጣሚዎችን) እየጠበቁና እያመቻቹ አደረግን ወይም እያደረግን ነው ለማለት ከሚያስችሉ ዜናዎችና ምስሎች (ፎቶ ግራፎች ወይም ተንቀሳቃሽ ምስሎች) ጋር ብቅና ጥልቅ ማለት ከጠቀሚታው ይልቅ አሳሳችነቱ (አዘናጊነቱ)  ያመዝናልና  ከዚህ አይነት ጋግርታም (chronically poor) የፖለቲካ ባህል ለመውጣት በግልፅና በቀጥታ መነገጋገር ይኖርብናል።

5) በዚህ ረገድ ህልውና፣ ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነት፣ ሰላምና የጋራ እድገት የሚሰፍንባትና የሚረጋገጥባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በአንፃራዊነት እጅግ አበረታችና ተስፋ ሰጭ ተጋድሎ በማካሄድ ላይ ከሚገኙት ከአማራ ፉኖዎች እና ከሌሎች የዴሞክራሲ አርበኞች ብዙ ይጠበቃል። ጋግርታሙ የፖለቲካ ባህል ማለትም የወንበር ሽሚያ፣ የአድርባይነት ደዌ፣ የጎጠኝነት አባዜ፣ በግል ኩርፊያ የአንድነት ስንጥቅን ከመድፈን ይልቅ የማስፋት፣ የግልብና የግል ስሜት ሰለባ የመሆን፣ መከራና ውርደት መቀበልን እንደ ፅድቅ መንገድ አድርጎ የማመንን (ራስን የማታለልን) ፣ የሥርዓት ለውጥ ሳይሆን የጉልቻ ለውጥ ባለ ድርሻ የመሆን  ወራዳነትን፣ በራስ ውድቀት ትግሉ ቢቀለበስ ” ፈጣሪ ባይለው ነው” የሚለውን ጨምሮ ሰንካላ የሰበብ ድሪቶ የመደረትን፣ ወዘተ  አስቀያሚ ፈተና የጊዜን ወርቃማነት እና ሌሎች የትግል ግብአቶችን ግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የፖለቲካና የወታደራዊ አንድነት ሃይልን (አደረጃጀትን) እውን በማድረግ ካላለፍነው እዚያና እዚህ የምናያቸው የብቅና ጥልቅ የፖለቲካ ጨዋታዎች ጠልፈው እንደማይጥሉን ዋስትና የለንም።

እናም ልብ ያለው ልብ ይበል!

12 Comments

  1. ገዱ አንዳርጋቸው እንዲህ ደፍሮ አልፎ ተርፎ እንዲህ ፊት ለፊት መፍትሄ እፈልጋለሁ ብሎ ይመጣል ብሎ መገመት የማይታሰብ ነበር ግና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ነው ይቻላል ለአብይ እስካደሩ። አረጋዊ በርሄ፣ቀጀላ መርዳሳ፣ሌንጮ ለታ/ባቲ፣ብርሀኑ ነጋ፣አገኘሁ ተሻገር፣ዳውድ ኢብሳ፣ጁዋር መሀመድ —- በወንጀል ፍሬ ተንደላቅቀው የሚኖሩ በመሆኑ ሊገርመን አይገባም። አቡን እንዳይወጣና እንዳይገባ በተከለከለበት የአብይ ምስራቅ አፍሪካ ገዱ መንፈስ ሁኖ ነው የወጣው ወይስ ተልእኮ አንግቦ? የብአዴን የስራ ስኬት ጅላጅል መሆንና ተዋርዶ መባረርን አስቀድሞ መቀበል ነው። ንጉሱ ጥላሁን ዛሬ ላይ በባህል ሚኒስቴር የዘበኞች አለቃ ነው ይባላል ነገ ዝመት ይባላል ቀሪውን የምናየው ነው።

  2. ወንድም ጠገናው፦
    ቸኩለን እዳናሳስትና እንዳናደናቅፍ መጠንቀቁ ደግ ነው። የሚያወራው ብዙ ቢሆንም፣ ሁሉንም ወሳኝ ባለቤት መኖሩን ማስታወስ ይገባል። ምሁራን ከ1966 ዓ.ም. ጀምሮ ግራ ቀኙን ባግባቡ ሳያዩ መቻኮላቸው ያመጣውን ውጤት ባለፉት 50 ዓመታት አይተናል። ትዕግስት ጠቃሚ ነው።

  3. The significance of Masinga, the US ambassador to Ethiopia, posing for a photo with Gedu and Yilkal cannot be overstated. It sends a powerful message: Abiy acknowledges his inability to manage Ethiopia effectively, and changes are needed.

    In parliament, only Gedu and Christian have openly criticized the boy king. Christian ended up in jail, while Gedu outmaneuvered the shenanigans Abiy’s tactics and escaped Ethiopia.

    Picture this; Over the past six years, while one Shimelis has remained in office in the Oromia region, the Amhara region has seen seven head administrations change. This suggests the boy king is manipulating the political landscape in the Amhara region.

    While Gedu needs to clarify the situation, stop hiding, and expose Abiy’s conspiracy, Fano and its supporters should leverage Gedu and similar figures to gain support from Western diplomatic networks and challenge Abiy and his cronies.

  4. May I Just once again emphasize my point of view not to have unnecessarily conversation but to be clear?
    By the way, I thank all of you for your comments/opinions which are constructively relevant to the tragic situation in our country caused by the very stupid and brutal ruling elites of ethno-centric political gambling.
    Let me say the following about the very essence of my piece :
    1) I sincerely and strongly believe that the political personality of dismembering oneself from a very horrible political system of ethno- centrism that has committed unimaginable crime on innocent citizens for about 30+ years and posturing as a genuine politician who joins the struggle for freedom and justice without a real sense of confession ( regret) and apology is nothing but a terrible self-deception as well as deception of others. I other words, If one is not at least morally courageous enough to sincerely regret and say deeply sorry for having a bloody political background, it is both politically and morally wrong.How one claim that he or she is a person of freedom and justice if he or she has no deep and serious respect for the very essence or value of admitting horrible behavior and action against peoples’ interest??? Absolutely disturbing!

    2) I argue that these guys such as Gedu Andargachew and Andargachew Tsige and others were among the terrible politicians who are not and cannot be immune from unequivocally though criticism for being parts of the most bloody politics of ethno/centrism . So, is it too much or unfair to ask them to officially and truthfully confess and apologize for what they did when they turn their backs on their old masters (bosses) and join the struggle for freedom and justice???
    3) It must be underscored that for diplomacy to holds a real meaning and be one of the means to get things changed for the better!, it must be conducted by the right person with credible or impactful political and moral standard !!! It is no simply a a matter of whoever does involve as long as he or she has acquaintance/ familiarity with others who are parts of that diplomatic affairs .
    4) I never said and will never say that people like Gedu and Andargachew must be rejected from any endeavor in the process of the struggle . What I strongly believe and say is that if we really want to bring about a real and irreversible democratic system, the very quality of those who play exemplary role must be considered seriously. It must not be whoever interested is welcome. And one of the most desirable and impactful factors in this regard is a well shaped and unshakable political and moral personalities.
    5) The political culture of not calling a spade a spade or not telling things as they are on effective and timely fashion because of the unsubstantiated fear that things will get worse is a very clumsy political argument. Why and how asking those old guards of EPRDF and so called Prosperity party who distanced/dismembered themselves to express real sense of regret and sincere apology and then be parts of the struggle for the birth of democratic country is too much or unfair???
    Thank you once again guys!

  5. Deat TG:-
    First, I get your message and the deep sincerity, and honesty embedded in it. It is not that I do not share your concern, but I have a greater one relating to a Motherland which has been continuously bled by the “learned” generations since the 1960s. I want us to be extremely careful that we do not hamper the progress of an upcoming development which has promises to take us to a democratic governance like that of Mandela’s South Africa at one stroke. I would welcome even the devil so long as the devil follows my instructions.

    Mandela worked with the Zulu leader and even went as far as announcing that he would go on his knees to Chief Buthelezi to solicit his cooperation in the transition negotiations during 1991-1994. That was how he worked and succeeded in creating a united and democratic South Africa less hat 4 years after being in prison for 27 years.

    The people that you target appear to be working on the issue in a manner that is fully consistent with the objectives publicly announced by those same ones, the principals, that are shedding their blood for its achievement. Those out in the field cannot possibly do what Gedu and those of you in the Diaspora can do. There is a sort of division of labor that is consistent, but not officially sanctioned. All are working towards the same goal.

    Given this positive present contribution which can best be done by the targeted individuals, I am just saying that since suspicions of falsehood, honesty, regret, integrity and the like will eventually be exposed and cleared up when it comes to actual implementation by those who own the process and have been sweating and bleeding to create a democratic Ethiopia, rest assured that they know all imposters (like Lidetu Ayalew, for example) who need to be eventually weeded out. Let us have the patience to get essential things done first even by the devil so long as it is an essential contribution to the common cause. When there is a divergence, that must be promptly stopped, but that is not there at the moment.

    Please note that, at a higher level, the French and Germans that killed each other in the 1940s are now the joint drivers of the EU. Let us have the work done first, as planned by the principals, and leave out the clean up of who is who to the stage when we come to implementing the democratizing process. Mind you, there will be several occasions when the principals will have to deal, negotiate and work with even OLF and TPLF , among others, to bring about the birth of a truly democratic Ethiopia. Gedu and the like, under strict technical guidance and joint mission, will come in handy at such fora since they know them best.

  6. As the saying goes, “trust but verify.”
    Ethiopia currently feels like a toxic waste dump, a prison, and an insane asylum under the boy king who is afraid of both international and domestic media.

    He fears that his lies and deceptions will be exposed, which is why he hides behind the curtain and preaches to his complacent parliament officials like a Protestant pastor. His behavior is destructive and narcissistic. Abiy is not just a liar; calling him that is a category mistake. A liar acknowledges the existence of the truth, whereas a bullshitter denies it entirely. Even if Abiy accidentally speaks the truth, no one will trust him anymore.

    For the young generation in Ethiopia to have any chance of survival, it is crucial that they hold Abiy and his cronies accountable for their actions. Even better, they should aspire to become future leaders and educators themselves. They cannot afford to passively stand by as the “boy king” continues to destroy the country and endanger their lives.

    That being said, the optimistic Pollyanna in me believes there is hope for a brighter future and more peaceful coexistence in Ethiopia. I am not saying it will be easy, but it is possible. As Mahatma Gandhi stated, “We must be the change we wish to see.” Before we can change the world, we need to change ourselves.
    Imagine this: the elephant in the room is the deceptive Abiy and his cronies!
    We must work to unite all the Fano leaders from the four provinces, particularly the Shewa Fano, to end the killings and displacement in the Amhara region. And then by collaborating with other fighters who are fighting against the deceptive Abiy, we can a bring peace and security to Ethiopia.

  7. ጠያቂ በሌለበት አገር ተጠያቂ አይኖርም!
    የአቶ ጠገናው ጎሹ መልእክት ግልፅና እኔም ቀደም ሲል ገዱ የተባለው ጉድና ወንጀለኛ ና ይልቃል የተባለው አስመሳይ ለአሜሪካኖቹ የእወቁልን
    ማመልከቻ ማቅረባቸውን ስሰማ ተመሳሳይ አስተያዬት ህዝብ ለህዝብ በሚለው መድረክ ላይ ሰጥቼበት ነበር:: በዚሁ መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ያልቸውም ሰዎች የገዱን ወንጀልእኛነት ሳይጠይቁ በጭብጨባ የለውጥ ሃዋርያ አድርገው ሲያሞግሱት አይቼ የትዝብት ትችት ሰጥቻለሁ::
    ባዶ ቤት በቁንጫ ይወረራል በማለትም ድርጊቱን ገልጨዋለሁ::ገሎም ዘርፎም ሲበቃው በስርአቱ ፈቃድና እውቅና በውጭ አገር የወጣውን ሁሉ ካለምንም ጥያቄ መቀበሉ የቆዬ በሽታ ሆኗል::ስለፍትህ እዬጮሁ ፍትህ የጣሱትን በዝምታ ማለፍ ፍትህን በቃል እንጂ በተግባር ለመግለፅ የማይደፍር ሆኖ መገኘት ነው::
    የጭፍጨፋ ቅስቀሳ ያካሄደውን በቀለ ገርባን ዘርፎና አዘርፎ ገሎና አፈናቅሎ የወጣውን ታከለ ኡማን የጎሰኛው አገር አጥፊ የወያኔ ቡድን ነፍስ አባት የሆነው አቦይ ስብሃት ኧረ ስንቱ ተዘርዝሮ እንደ ንፁህ ዜጋ በነፃነት ሲምነሸነሹ ለፍርድ ይቅረቡ ብሎ ለመጠዬቅ ያልደፈረ ህዝብ ነገ ደግሞ አብይና ሌሎቹ ዕድል ገጥሟቸው ቢወጡ የአበባ ጉንጉን እንደማያቀርብላቸው አያጠራጥርም:: ተቃዋሚ ነኝየሚለው ጉልበቱና ድፍረቱ በራሱ መካከል ልዩነት ለመፍጠርና ትግሉን ከማዳከሙ ላይ ነው::
    ገዱም ሆነ ሌሎቹ የተሰጣቸውን ተልእኮ ይዘው የመጡ ወንጀለኞች ናቸው::አቶ ጠገናው ጎሹ እንዳሉት አካፋን አካፋ ማለት ተገቢ ነው:: የሚገርመው እነዚህን ሁለት አስመሳዮች ምን አገናኛቸው? ይልቃልስ ገዱ በሚወክለውና በሚመራው ስርአት ታስሮ አልነበረምን? ሁለቱንስ ውክልና ማን ሰጣቸው? የህዝብ ውክልና የሌላቸውን የአሜሪካ ባለስልጣናት በምን መልክ ተቀብለው አብረው ተቀመጡ? ምን ለማድረግ? ለኢትዮዽያ መከራ የአሜሪካ እጅ የለበትም ወይ? ወደፊትስ ቢሆን ለኢትዮዽያ በጎ ነገር ያስባሉ ወይ?
    እነዚህን ሁሉ እያነሱ መተቸት አስፈላጊ ነው::
    የጠላት ካምፕ ተቦረቦረ እያሉ አገር ሲቦረቡር ለኖረው ስርአት ያገለገሉትን ወንጀለኞች በክብር መቀበል ክብረቢስ መሆን ነው:: ሌሎቹንም በርቱ ቀጥሉበት የሚነካችሁ የለም የሚል መልእክት ማስተላለፍ ይሆናል::

  8. ወንድም አገሬ፦
    ተማርን የሚሉ “የአበሻ ፈረንጆች” ሲያደሟት ለኖረችው አገራችን በጣም እጨነቃለሁ። ገዱና ይልቃል ማን ውክልና ስጥቷቸው ነው የአሜሪካን መንግሥት ያነጋገሩ ብለህ ጥያይቀሀል። አንተስ ማን ወክሎህ ነው ዛሬ ስለ ኢትዮጵያ የምትጽፈው ? በጠቅላላ ዳያስፖራው በማን ውክልና ነው እስከ ዛሬ ብዙ በጣም ብዙ ሥራ ሲሠራ የቆየው ? በቅርቡ US Senate staff ያነጋገሩት ወንድሞቻችሁን “ማን ወከላቸው?” ብለህ ልትጠይቅ ነው ? እያስተዋልን እንሂድ እንጂ። ማን የኢትዮጵያ ባለቤት፣ ማን ጭሰኛ ነው ልትል ነው ? ሁላችንም በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል።

    አቶ ገዱንና አቶ ይልቃልን ከአውሬው ስብሐት ነጋና ከፀረ አማራ ጎጠኛው በቀለ ገርባ ጋር አመሳስለህ አንስተሀቸዋል። ኢትዮጵያን እውነት ታውቃታለህ ? በቀለ ገርባና ስብሐት ነጋ ምን ይሠሩ እንደነበሩና ዛሬም አሜሪካ ለምን እንደመጡ ታውቃለህ ? ገዱ በተወካዮች ም/ቤት ስላደረገው የሚያሳሥር ክርኳሪ ንግግር ሰምተሀል ? ከገዢው ፓርቲ ጋር መስሎ ቢኖር ኖሮ እኮ ሹመትም አይነፈግም ነበር። ለምን የአገሩ ጉዳይ ዛሬ ቆረቆረውና ከገዢው ፓርቲ አፈነገጠ ነው ክስህ ? አንድም ትችት ያልሰነዘርህበት ልደቱ አያሌው ቅንጅትን ያፈረሰና ብዙ ግሩም ወጣቶችን ለሞትና ለከርቸሌ ያበቃ ነጋዴ ነው። እናንተ መካከል ደህና ሰው መስሎ ይቀባጥራል። ለሚያውቁት ግን የለየለት ባንዳ ነጋዴ ነው። በቂ መረጃም አለ። ምናልባት የብርሃኑ ነጋን የእሥር ቢት መጽሐፉን ካገኘህ አንብበው። ጥሩ ይናገራል፣ ግን ተደጋግሞ እንደታየው አይታመንም።

    እኔ ገዱም ሆነ ይልቃል ጋር ግንኙነት የለኝም። ይልቃልን በዚህ ዓመት በዩቱብ ከዘመነ ካሤ ጋር ተቀምጦ አይቸዋለሁ። ዛሬ አሜሪካ በመሥራት ላይ ያሉት ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል በተባለው ቁልፍ ጉዳይ ላይ ነው። እናንት በዛ ያለ ጊዜ በውጭ ስትቀመጡ፣ ስለ ሽግግር መንግሥት አስፈላጊነት መቼ ተንፍሳችሁ ታውቃላችሁ ? እኔ እንዳየሁት፣ ኤፍሬም ማዴቦ፣ ዳኒኤል ክንዴ፣ እምቢልታና ሌላ አንድ ወይም ሁለት ሰው ነካክተውት ጠፉ። የእናንተን ስም ግን አላየሁም። ታዲያ ለአገሩ በመቆጨት የሚሠራን ሰው እየነካኩ ተስፋ ማስቆረጡ ምን ለማትረፍ ነው? እኔ ላይ እንደጻፍሁት፣ የምፈልገውን እስከሠራ ድረስ፣ ከስይጣን ጋር ቢሆንም እሠራለሁ። ዋናው ዓላማየ ኢትዮጵያን መታደግ ነው። ሰይጣን ኢትዮጵያን ከታደገ አብሮ መሥራቱ አይስፈራኝም።

    በነገራችን ላይ ኔልሰን ማንዴላ በ1982 ዓ.ም. ከ27 ዓመት እሥር በኋላ ተለቅቀው 26 ፓርቲዎችንና የሥርዓቱን ሹሞች ማስተባበር ሲጀምሩ፣ አንዱ እጅግ በጣም አክራሪ ተቃዋሚያቸው የዙሉው ልዑል ቡቴሌዚ ነበሩ። ማንዴላ እሳችውንም ቢሆን ለማግባባትና ወደ ድርድሩ ለማምጣት ተንበርክኬም ቢሆን እማጸናችዋለሁ ነበር ያሉት ። እንደዚያ አድርገው ከኩርፊያና ቂም በቀል ራሳቸውን አግደው ነው የዛሬይቱን ፌደራልና ዲሞክራሲያዊት ደቡብ አፍሪቃ በአንድ ምርጭ የመሠረቱት ። (እኛ 7 ምርጫ በተወላገደ ሥር ዓት መሠረት አድርገን ተወላግደን ቀረን።) ቂም በቀሉን ትተን ቆጭቷቸውም ሆነ ፀፅቷቸው አብረን እንሥራ የሚሉትን ባናባርር ለምዝብሯ አገራችን ጥሩ ነው። ፋኖስ ሲያወግዛቸው ሰምታችኋል ወይስ ለኢትዮጵያ የምናውቅ እኛ ብቻ ነን እያላችሁ ነው ? ከጳጳሱ ቄሱ እንደተባለው ነው ? ልብ ይስጠን !

  9. አቶ አንድንት ከሰይጣንም ጋር ቢሆን እሰራለሁ ማለትዎ ከምድራዊ ሰይጣን ከሆነው ከወያኔ ከኦነግ (ብልፅግናም) ቢሆን እሰራለሁ የሚል እንድምታ ያለው መሆኑን የተገነዘቡት አይመስለኝም:: ምክንያቱም ከነሱ የባሰ ወይ የተሻለ ሰይጣን የለምና! ገዱንና አቦይ ስብሃትንም የአንድ ድርጅት የኢሃዴግ መሪ ተዋንያን መሆናቸውን ዘንግተው ይሁን ክደው ለያይተው ተመልክተዋል ::: ገዱ ከስልጣን ሲባረር አፉን ከፈተ እንጂ ከዚያማ በፊት ትንፍሽ የማለት ድፍረትና ወኔ አልነበረውም:: ስለእኔ የሽግግር መንግስት አስፈላግነት ምን ብለህ ታውቃለህ? ድምፅህን አጥፍተህ ከመቀመጥ በቀር በማለት እነልደቱን ከመሰለው አጭበርባሪ ጋር ደባልቀውኛል:: ባያውቁት ወይም ባይገባዎት እንጂ ስለ ሽግግር ህዝባዊ መንግስት ስጮህ ከንገሡ ጊዜ ጀምሮ ከ50 ዓመት በላይ ሆኖኛል::እስከዛሬም ድረስ በሽግግር መንግስት አስፈላጊነት ሽንጤን ገትሬ እናገራለሁ እፅፋለሁም:: የጠቀሷቸው ፕሮፌሰር ዳንኤል ክንዴም ጋር በክፍላተሃገር ህብረት ውስጥ አብረን የሰራን ለሽግግር መንግስት ምስረታም የፃፍን የተናገርን ስንሆን እሳቸው ሊቀመንበር እኔ ፀሃፊም በመሆን ዓለም አቀፍ የኢትዮዽያውያን የትብብር ምድረክን ((International Ethiopians solidarity forum) ፈጥረን የቻልነውን አበርክተናል:: የትብብርን አስፈላጊነት አስተምረናል::
    ኢትዮዽያ የነገዱን አይነት አይተነው ጊዜ ተገለባባጭ ወይም አክሮባቲስቶችን ሳይሆን በገዱ የስልጣን ዘመን ለእሷ ሲሉ የተሰቃዩ ልጆቿን ታምናለች::
    ነገ ደግሞ አብይ አህመድ ተባሮ ተቃዋሚ ነኝ ቢል የአበባ ጉንጉን አንገቱ ላይ እንደሚያጠልቁለት ና ጉሮ ወሸባይ እንደሚሉለት አልጠራጠርም::የእንደርስዎ አይነቱ መኖር ነው ለፋሽስቶችና ለሌቦች የሞራል ጉልበትና ድፍረት የሚሰጠው::
    የትግል መጀመሪያው ጠላትና ወዳጅን ማወቅ ነውና ለዚያ ያብቃዎት !
    አገሬ አዲስ

  10. የኢትዮጲያ መከራ የአማራው ሰቂቃ ያቆም ዘንድ ትልቅ ጥበብና የፖለቲካ ሂደት ይጠይቃል:: በዚህ ወቅት ድሮ በኢትዮጲያዊነት ልዩ አክብሮትና እምነቱ የተነሳ የዘር ጉዳይ ብዙ የማያሳስበው አማራው ነፍጠኛው በሚል ላለፉት አርባ አምታታ የሚደረግበትን ጭፍጨፋና ማፈናቀል ለመመከት በራሱ ቀዬ በጀመረው ብርቱ የመስዋእትነት ትግል ደም ሳይፈስ ስርይት የለም በሚለው ቅዱስ መርህ በፋኖ ልጆቹ መስዋእትነት ማንነቱ ሊከበር ቀና ብሎ ሊኖርና ባግባቡም ለሃገራዊ ምክክር ሊቀመጥ በቃ ክብር ለጌታ ምስጋና ለሰማእታቱ ይሁን:: በዚህ ሁኔታ ግን ድሮ ወያኔ ዛሬ ብልጽግና የተባለው ከሃዲ ቡድን በሚያሰርፋቸው መልክተኞቹና በእኔነተ ፉክክር ያልስፈላጊ መከፋፈል ማየቱ ያሳዝናል:: አልፎ ተርፎም ባንድ መልክ ትግሉን መምራት ከአለም አቀፍ ማህበረስብ የሚቀርቡ ድርድሮች ላይ መተማመን መቀባበል ሲጠፋ በጣም ያሳዝናል:: ባለፈው በ ትርፕል ኤ AAA ሰሞኑን በጋዜጠኛ መአዛ ላይ ዛሬ ደግሞ በገድሉ አንዳርጋቸውና በይልቃል ላይ የሚሰነዘረው መጠን ያለፈ ዘለፋ የተገባ አይደለም:: በዚህ አምድ የተጠቀሰ የአፍሪካዊያን ህብረት ANC በማንዴላ መሪነት እጅግ የሚቃረኑ ማህበረስ ቦች አፕርታይድን ለማፍረስ የተጠቀሙበት ዘይቤ ለኢትዮጲያም የከፋ የጎሳ ፓለቲካ ማስወገጀ ሊጠቅ መን ስለሚችል ፈጥነን ከመፍረድ እንቆጠብ በየቀኑ የሚታረደው አማራና የምትፈርሰው ኢትዮጲያ ጉዳይ ግድ ብሎን ትግሉን ሁሉን ጸረ ጎሳ ታጋዮችን ሁሉ በሚያካትት መልኩ ማቀናበር ይሁንልን:: ገድሉ በሚቻለው መልኩ በአፋኙ ፓርላማ መደረግ የሚገባውን ተናግሮ የተሰደደ ነው ይልቃል ከጅማሬው ይህን ግፈኛ አገዛዝ የተፋለመ ነውና ነቀፋችን ሚዛናዊ ይሁን:: ሆኖም ግን የህዝባችንን ማለቅ መፈናቀል ለጥቅማቸው የሚያድርጉ በርስ በርስ ፉክክር የተሰማሩትን ለህዝባችን ማለው ተጠየቂ የሆኑ ባንዳዎችና ነፍሰገዳዮችን ለፍርድ ማቅረቡን ግን በፍጹም አንተውም -ፓስተር ዲጎኔ ሞረቴው

  11. ወንድም አገሬ፦
    “ባያውቁት ወይም ባይገባዎት እንጂ ስለ ሽግግር ህዝባዊ መንግስት ስጮህ ከንገሡ ጊዜ ጀምሮ ከ50 ዓመት በላይ ሆኖኛል::እስከዛሬም ድረስ በሽግግር መንግስት አስፈላጊነት ሽንጤን ገትሬ እናገራለሁ እፅፋለሁም:: ” ብለኸኛል። አግባብነቱ ላይ ብዙ ጥያቄ ነበረኝ እንጂ፣ እረ ጩኸታችሁንስ በደንብ ሰምቸዋለሁ። ነገር ግን፣ የሽግግር መንግሥት ስል ስለ ወቅቱ ሽግግር ነው እንጂ ስለ ኢሓፓው/መኢሶኑ የከሸፈ ታሪክ አይደለም። ዳንኤልንም ምናልባት ከአንተ በፊት አውቀዋለሁ። እኔ በዘመኑ ብኖርም ያኔም ሆነ ዛሬ የማንም ፓርቲ አቀንቃኝም አይደለሁም። ስለሆነም፣ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ፣ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከማንም ጋር አልተባበርሁም። አልተባበርም።

    ያለፈው አልፏል። ዛሬ ኢትዮጵያን ለውድቀት ካበቃንበት አረንቋ ለማውጣት እንዴት እንሸጋገር ነው የእኔ ችግር። አንዱ ወሳኝ ዘዴ፣ ሆደ ሰፊ መሆን ነው። ኢትዮጵያን መልሶ ለማቋቋም ከረዳ፣ ከወያኔ፣ ከኦነግና ከብልፅግናም ጋር አግባብነት ባለው መድረክ ለመነጋገር ዝግጁ መሆነ ነው። ራቅ ብሎ ቆሞ የሚሠሩትን አለማደናቀፍ ነው። ከጳጳሱ ቄሱ አለመሆን ነው። አሜሪካ ስለሚኖሩ ብቻ ለኢትዮጵያ የሚበጀውን ሁሉ አውቃለሁ አለማለት ነው። አንዱ ሌላውን ሳይረግጥ፣ እስካሁን እንደተደረገው፣ ድርሻ ድርሻችንን ብንሠራ፣ አገራችንን መልሰን እናቁቁማታለን። ኩታ በር በሚሠራው ሥራ ላይ እኔ ይበልጥ አውቃለሁ አለማለት ነው። ምክር ጥሩ ነው። የኩታ በሩን ሥራ ግን እዚያው ኩታ በር ያሉት ወንድሞችህ የተሻለ ይሠሩታል።

    ከዛሬ 50 ዓመት ጀምሮ ስለ ሽግግር መንግሥት መጮህም በቂ አይደለም። ይህም በተጨባጭ ታይቷል። የሽግግር መንግሥቱ ካልተሳካ፣ እውን እንዲሆን በቂ ዝግጅትና ድርጅት አልነበራችሁም ማለት ነው። ዛሬ፣ እነ አቶ ገዱና አቶ ይልቃል የሽግግር መንግሥት ያስፈልጋል ሲሉ፣ ሃሳቡ ከየት እንደመጣ መገመት አያቅትህም። እስቲ ከፕሮፌሶር ዳኔእልና ሌሎችም የድሮ ጓዶችህ ጋር ስለ ሽግግር መንግሥት ምሥረታ በዝርዝር ረቂቅ አቅርቡና እንነጋገርበት ። በባዶ ከመነታረኩ አይሻልም ? ስድብም ተሳዳቢን ያዋርዳል።

  12. አንድያቸውን፤ጁዋር መሃመድን፤በቀለ ገርባን ልደቱና ታምራት ላይኔን ጨምረው በስደት ያለ የሌባ መንግስት አቋቁመውልን ብልጽግና ሲወድቅ ስልጣን ተቀብለው ሌብነቱን ያሳልጡት።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

191614
Previous Story

ለ4ኛ ጊዜ የቀረበው አደገኛው ረቂቅ አዋጅ፤ የአዲስ አበባን ኅልውና አደጋ ላይ ወድቋል! ከጠለምት የወጡ መረጃዎች! | “ባህርዳርን መቀማታችን ነው…ሰራዊቱ አልታዛዝ ብሏል” | በሁለት ቀናት ውስጥ 30 አርሶአደሮች ተገደሉ፥ የአቶ አረጋ ከበደ ወንድም በፋኖዎች ተያዘ፥ | “እኛም ይበቃናል ለአብይ መሞት አንፈልግም” ሻለቃ |

191640
Next Story

ድንበር አቅራቢያ የተካሄደው ከባድ ውጊያ፣ የአየር መንገዱ ውል ሊፈርስ ነው፣ የመቀሌው አስፈሪ ሪፖርት፣ የእነ ደሳለኝ ጫኔ ፍጥጫ

Go toTop