November 11, 2018
4 mins read

ለ18 አመታት ያህል በትግራይ ክልል ታስሮ የቆየው ካሳሁን ሲሳይ ‹‹በትግራይ የሚታሰር አማራ የከፋ ግፍ ይፈፀምበታል›› አለ

18

በጎንደር ወልቃይት ተወለልዶ ያደገው ሲሳይ በአዲስ አበባ ከሚታተመው ጊዮን ከተባለው መፅሄት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ የታሰረው መስከረም 11 ቀን 1986 እንደነበር አስረድቷል፡፡ መጀመሪያ በትግራይ ሽሬ ከተማ ከጓደኛው ጋር መታሰሩን የገለፀው ሲሳይ ጓደኛው ከአምስት አመት እስር በኋላ እዛው እስር ቤት መሞቱን ገልፆዋል፡፡ ስለጓደኛው አሟሟት ተጠይቆም፡-
‹‹ታሞ ቢሞትም ለህመሙ መንስኤ የሆነ መድሃኒት ሰጥተው የገደሉት ግን ወያኔዎች ናቸው፡፡ በመድሃኒት ገድለውታል ብዬ ነው የማምነው›› ብሏል፡፡ በእስር ቤት የነበረውን ሁኔታ ሲያስረዳ ደግሞ ‹በጣም ከባድና ስቃይ የበዛበት ነው ማለት ይቻላል፡፡ የሻይ መጠጫ በሆች ትንሽ የፕላስቲክ ኩባያ እየተለካ የማሽላ ገንፎ ነበር የሚሰጠን፡፡ መኝታችን በእስኪሪብቶ ተለክቶ በተሰመረልን ጠባብ ክፍል ውስጥ ነው፡፡ በእንድ ክፍል ውስጥ ብዙ እስረኛ ከመኖሩ የተነሳ ሶስት እስረኛ በሰንሰለትና በቦንዳ አንድ ላይ ተጠላልፎ ነው የሚታሰረው፡፡ በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ ነው 24 ሰአት ሚሉ የምትታሰረው›› ብሏል፡፡

ለዘጠኝ አመታት ያህል ፍርድ ቤት ሲመላለስ ከቆየ በኋላ በትግራይ ውስጥ ሞት ተፈርዶበት እንደነበርም ለመፅሄቱ አስረድቷል፡፡ ሞት ከተፈረደበት በኋላ ይግባኝ ጠይቆ ምንም ምላሽ አለማግኘቱንም ገልጧል፡፡ ሲናገርም ‹‹ዘጠኝ አመት ከታሰርኩ በኋላ ነው ሞት የተፈረደብኝ፡፡ ያኔ መቀሌ ይግባኝ ብዬ ነበር፡፡ እዛም ከስድስት ወር በኋላ ውሳኔው ይፅና ብለው ተስማሙ፡፡ በጣም የሚገርመው ቀን ሰብረው፣ አቃቤ ህግ በሌለበት፣ እኔ ባልቀረብኩበት፣ ያለክርክር ነው ውሳኔው መፅናቱ ይፋ የተደረገው፡፡›› ብሏል፡፡ ነገር ግን የተፈረደበት የሞት ውሳኔ ተግባራዊ ሳይደረግ በ2003 መስከረም ወር በምህረት እንደተለቀቀ ተናግሯል፡፡

ስለወ/ሮ አዜብ መስፍን የተጠየቀው ካሳሁን ሲሳይ ‹‹ከአዜብ ጋር ዝምድናችን የቅርብ ብቻ ሳይሆን እህቴ ማለት ናት፡፡ ግን እሷ እንኳን ለኔ ለእናቷም አትሆንም፡፡ እንኳን ቤተሰብ የአገር ሰው የሚባል እንዲቀርባት አትፈልግም›› የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ግዮን መፅሄት ‹‹ወ/ሮ አዜብ የትግራይ ተወላጅ ናቸው?›› የሚል ጥያቄ ያነሳለት ካሳሁን ሲመልስ
‹‹አንድም ትግሬ የለባትም፡፡ ይልቅ የትግራይ ሙሽራ ናት ብትል ያስኬዳል፡፡ የወልቃይት ተወላጅ የጎንደር ሰው ናት፡፡ የእሷ አያት ደጃዝማች ጎላ ጣሊያን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲመጣ በተደረገ ውጊያ ያኔ ሰባት መድፍ ማርከዋል፡፡ መድፉ ከባድ ስለነበርና ከቦታው አልነሳ ሲላቸው እያንዳንዱ መድፍ ላይ ጎላ ጎሹ እያሉ ስማቸውን ፅፈውበታል፡፡ እኚህ ሰው ጥርት ያሉ ጎንደሬ፣ የእናቷ አባት ናቸው›› በማለት አስረድቷል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=f9ZDJjIZNkI

2 Comments

  1. Do not forget that Abiy is also a zombie Amara Gondare just who came as Metec/effort’s mother of corruption Azeb Mesfin is. Zombies are spineless that are easily manipulated by anyone, especially by us Tigrigna speakers.Azeb is free so what does it say about us Tigrigna speakers who are worshiped by the Gondare Zombie Amaras. Lately more and more of their Gondare Zombie women are wearing our shuruba and dancing like us too. They just badmouth us TIgrayans when we are not around so they be on the good side of Other Amaras like this guy Kasahun Sisay above is doing.The Gondares are jealous of our Tigray culture. For generations Gondares worshiped us Tigrayans as if we Tigrayans are the only human beings they encountered, then they turn back to other Ethiopian people bostfully hypocritically telling them how great the Gondares are and how Gondares along with Tigrayans are the Golden people.The Gondares got a severe identity ego crisis which is making them lead their life as a zombie.One thing is for sure they like to immitate Tigrayans and Eritreans every chance they get. If they don’t have the chance to immitate us they immitate anyone they find be it Oromos, Kaffa’s … Now Abiy’s team zombie Gondares are doing their best to be on the good side of Eritreans so they can learn a thing or two from Eritreans to immitate so they could show off immitating Eritreans to other Ethiopians bostfully. This zombie behaviour is getting transmitted to other Amaras lately.
    Gondares are copying everything, this behaviour forced them to end up with a lost self esteem now other Amaras are showing that they are zombies too even though the last 27 years was spent to revive them back to humanity. Now since Abiy is born in Jimma he is copying Kaffa’s claim to be the place where coffee originated. This years coffee day is celebrated in Jimma rather than Bonga,Kaffa where it was usually celebrated. Jimma is claiming to be the place where coffee originated .
    Ki kikiki

Comments are closed.

92475
Previous Story

ፕሮፌሰር መረራ ‹‹የጠመንጃ ፖለቲካ ማብቃት አለበት›› አሉ

92481
Next Story

የቀድሞው የፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ታሠሩ | ቀድሞው የማእከላዊ ምርመራ ምክትል አዛዥ እየታደኑ ነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop