August 27, 2013
13 mins read

የሞረሽ አባል ነኝ- ለምን ሞረሽ?

ስለ ሞረሽ ከመናገራችን በፊት የሞረሽን ምንነት መገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነገሮችን በቅጡ ከተረዱ ለማማትም መረጃን መሰረት ማድረጉ የተሻለ ይሆናል የሚል እምነት አለኝ፤
ሞረሽ የሚለውን ቃል ከደስታ ተክለወልድ መዝገበ ቃላት ስንፈልገው ከዚህ በታች ያለውን ትርጉም ይሰጣል፤
ሞረሽ (የሌሊት ጥሪ፥ እከሌ ሞተ፦አለፈ ተጎዳ ወዘt) ብሎ ይፈታዋል።

ልክ ስሙም እንደሚያመለክተው ሞረሽ ያለ ረዳት ከኖሩበት፦ እትብታቸውን ከቀበሩበት፦ ከከበሩበት በመንግስት አስተባባሪነት ለሚፈናቀሉት፦ ለሚገደሉት፦ አማሮች ጩኸታቸውን ለማሰማት የተመሰረተ ማሕበራዊ (civic) ድርጅት እንጂ አልፎ አልፎ በአንዳንድ ዜና ማሰራጫዎች እንደሚወራው የአማራ የፖለቲካ ድርጅት አይደለም አላማውም አማራውን ስልጣን ለማቆናጠጥ የሚታገልም አይዶለም።
ከዚህ ቀደም መአህድ የሚባል ነፍሳቸውን ይማርና ሕክምና በወያኔ እስር ቤት ተነፍገው በሞቱት በፕሮፌሰር አስራት የሚመራ ድርጅት ነበር፤ ይህ ድርጅት አመሰራረቱ አማራው ከሚደርስበትና እየደረሰበት ከነበረው ጥቃት ለመከላከል እንጂ የአማራን የበላይነት ለማንጸባረቅ አልነበረም፤ ከፕሮፌሰሩ ሕይወተ ህልፈት ማግስት ግን ውስጣቸው በነበረ ሽኩቻ ድርጅቱ ፈርሶ በመትኩ መኢአድ ተቋቁሟል።
ሞረሽን ከመአህድ የሚለየው ታዲያ ምንድን ነው? ለሚለው መልሱ አጭር ነው ይኸውም የፖለቲካ ድርጅት አለመሆኑ ነው፦ ስልጣን ላይ ለመውጣት የሚታገል ቡድን አለመሆኑ ነው፤
በኔ እምነት አማራ የሚባለው ማነው? ለሚለው ጥያቄ መልሱ እንደመላሾቹ ማንነት የተለያየ ትርጉም አግኝቷል፤ እኔ እንደምረዳው አፉን በአማርኛ የፈታ ሁሉ አማራ ነው፤ ሁላችንም እንደምናውቀው ጎዣም፦ ጎንደር፦ ሰሜን ሸዋ፦ ከፊል ወሎ (ጥንት ስሙ ድፍን ወሎ ቤተ አምሐራ) በአማራነት ይታወቃሉ ስማቸው ግን አማሮች ሳይሆን ጎዣሜ፦ጎንደሬ፦ ወሎዬ፦ መንዜ ወዘተ በመባል ነው።
“እንደ ወያኔና መሰሎቹ ቲኦሪ ግን “አማራ ” የሚለው ቃል፦ አማርኛ ቋንቋ በሚነገርባቸው አካባቢዎች ውስጥ የሚኖረው አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ በሙሉ በአንድ ላይ ሁኖ የሚታወቅበት መለያ ነው፤ ወያኔና መሰሎቹ……የሚሰጉትን ሕዝብ በመነጠል ለማጥቃት የሚያስቸልን ስልት ለመንደፍ ከማሰብ የተከተለ ትርጉም ነው። እንዲህ አይነቱ አካሄድ ደግሞ በወያኔና በኦነግ ዛሬ የተጀመረ አይደለም። በተለያዩ ግዜያት ኢትዮጵያን ለማጥቃት የመጡ የውጭ ሃይሎች በሙሉ ሀገሪቱን ለማዳከምና ለመከፋፈል ሲሉ በነደፏቸው ስልቶች ውስጥ ማእከላዊ ስፍራን ይዞ ይገኝ የነበረ ነው። የኢትዮጵያዊነት እና የአማራነት መለያዎች ህብር ከዘላለም ቁምላቸው gve 54″
ህዋሃት እንደ ትልቅ ጠላት የሚያያቸው ታላቁ አጼ ምኒሊክ የጦር መሪዎቻቸውን ስናይ (ደጃዝማች መሸሻን፦ ደጃዛማቸ ባልቻን፦ ራስ ጎበናን፦ ራስ አሉላን፦ ፊታውራሪ ሀብተግዮርጊስን ወዘተ) አንድ ያደረጋቸውና በሹመት ያሳደጋቸው ኢትዮጵያዊነት እንጂ ጎሳቸው አልነበረም። ዛሬ በወያኔ ዘመን ከዋኖቹ 25 ታላላቅ ጀኔራሎች 20 ትግሬዎች ናቸው፤ የየከፍለ ጦሩ ዋና አዛዦች በሙሉ ትግሬዎች ናቸው።
ሲገዛ የኖረው ጨቋኝ አማራ እየተባለ በወያኔና በመሰሎቹ የሚወራው ፤ ለምሳሌ የመጨረሻውን የኢትዮጵያ ንጉስ ተፈሪ መኮንንን ስንመለከት በእናታቸው አባት ኦሮሞ ሲሆኑ በእናታቸው እናት ደግሞ ጉራጌ ናቸው፤ አባታቸውን ስንመለከት ራስ መኮንን አባታቸው ኦሮሞ ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ አማራ ናቸው፤ ስለዚህ ከራስ ተፈሪ አማራነት ኦሮሞነታቸው ያመዝናል፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማሮች አማርነታቸው አፋቸውን በአማርኛ በመፍታታቸው እራሳቸውን ከአማራ መመደባቸው ነው፤ ይህ ደግሞ ምንም እንኳን በጎሳ እራሳቸውን ላደራጁ ባይመቸም የግለሰቦች መብት ነው፤ የኔም አማራነት ከንደዚህ አይነቱ የተለየ አይዶለም።
በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ የተቀረው ከዛ የሚከተል ነው፤ እንደ ሰው እንደ ሰብአዊ ፍጡር የህዋሃት መንግስት ትግል ከጀመረበት ግዜ አንስቶ እስከዛሬ በተለይ በአማራው ላይ የሚያካሄደው የጠላትነት ዘመቻ ይህንን አዲሱን አመለካከቴን እንድይዝ አስገድዶኛል።
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ስለ ኢትዮጵያዊነት ይህንን ይላሉ “ኢትዮጵያዊነት ብዙ የተለያዩ ህብረተሰቦች የተዋሃዱበት አካል መሆን ነው፤ ኢትዮጵያዊነት ከጎሰኝነት በላይና ውጭ የሆነ አጠቃላይ ማንነት ነው፤ ገጽ 31 ኢትዮጵያ ከየት ወዴት”
ስልጣን ላይ የወጣው መንግስት ስለ አማሮች እንዲህ ያስባል “የአማራ ገዢ መደቦች የትግራይ ሕዝብ ጠላቶች ናቸው፤ ታሪካችንና ቅርሶቻችንን ያጠፉት አማራዎች ናቸው፤ ለድህነትና ለስደት የዳረጉን አማራዎች ናቸው፤ በአማራ የተወሰዱት እንደ ወልቃይት ጸገዴ፦ሑመራ አሉ ውሃና ሌሎች የትግራይ መሬቶች እናስመልሳለን ታሪክ አጉዳፊው ገጽ 71 ከገሰሰው እንግዳ” ታጋይ ገሰሰ ውስጥ አዋቂና የወያኔ የትግል አጋር የነበሩ በመሆናቸው ወያኔን ጠንቅቀው ያውቃሉ፤
በተባለውም መሰረት ከአማራው ላይ የተጠቀሱት ቦታዎች ተወስደው ወደ ትግራይ ተደምረዋል፤ አማራውንም ጨቋኝ ብሎ በመሰየም በሌሎች ጎሳዎች ያለ ተከላካይ እንዲመታ አድርገዋል፤ ዛሬ በአሜሪካ ከሕዝብ በዘረፉት ብር ነዳጅ ጣቢያ ከፍተው የተንደላቀቀ ኑሮአቸውን የሚመሩት ታምራት ላይኔ ህዋሃትን ወክለው በምስራቅ ኢትዮጵያ አማራውን ካስጨፈጨፉት አንዱና ዋንኛው ናቸው።
አማርኛ ተናጋሪውን ወገን በጠላትነት መድበው ጨቋኝ ብሔር ይሉታል፤ ሌሎቹ ሁሉም በጀምላ ተጨቋኝ ብሔሮች ሆነዋል።
የአማራውን ቁጥር ለመቀነስ በሚደረገው ትግል ለሌላ በሽታ መከላከያ ነው እየተባለ ሴቶቸን በአማራው ክልል ብቻ በግዳጅ የእርግዝና መከላከያ መርፌ እንዲወጉ ይደረጋል፤ አሉባልታ ሳይሆን በተጨባጭ መረጃዎች ተገኝተዋል የዋሆቹ ሴቶች ለምን መውለድ እንዳቃታቸው ስለማያውቁ በየአድባራቱ ስለት ይሳላሉ፤ ይህ አንድን ዘር ለማጥፋት የሚደረግ በመንግስት የተቀነባበረ ስራ ከዘር ማጥፋት ወንጀል የሚለይ አይደለም፤
እነ መለስ ይላሉ ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ” አማርኛ ተናጋሪውንና የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዩን የሚመነጥሩት ኢትዮጵያን ለማጥፋት በሚሞክሩበት ግዜ አላስኬድ ስላላቸው ነው” በቅርቡ የወያኔ ቁንጮ የሆኑት ስብሃት ነጋ በመኩራራት አማራውንና ኦርቶዶክሱን እንዳያሰራራ አርገን መተነዋል ብለዋል።
ለመንግስትም ያመጣለት ውጤት የአማራው ሕዝብ ቁጥር ማሽቆልቆል ነው በሀዋሃት መረጃ መሰረት የአማራው ሕዝብ ቁጥር በሁለት,ት ሚሊዮን ወርዷል።
ወያኔ ባስተባበረው ጦርነት ሀረርጌ አርባ ጉጉ አማሮች ከነሕይወታቸው ገደል ተከተዋል፦ ቤታቸው ውስጥ ሰዎች እያሉ ተቃጥሏል፦ቆዳቸው እንደእንስሳ ተገፏል፦ ይህ ሁሉ በፊልም የተደገፈ መረጃ አለው፤ በአቶ ሽፈራው ሽጉጤ የተፈረመበት ማዘዣ በቅርቡ ከቤንቺ ማጂ ዞን ጉራ ፋርዳ ህገ ወጥ ተብለው አማሮች መፈናቀላቸው በምትካቸው ደግሞ ቻይኖች፦ ቱርኮች፦ አረቦች እየተጠሩ መሬት ይታደላሉ; ይህ መፈናቀል በዚህ አላበቃም ወደሌሎች ቦታዎችም ተዛምቷል። ቤንሻንጉል ጉምዝ ተመሳሳይ ግፍ ተፈጽሟል።
ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ወይም በህጋዊ መንገድ ሀገሪቱ ዉስጥ የሚገኝ የዉጭ ዜጋ በመረጠዉ የሀገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖርያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገዉ ጊዜ ከሀገር የመዉጣት ነፃነት አለዉ ይላል የሀገሪቱ ሕገመነግስት ነገር ግን ይህ መብት አማራን አይመለከትም የሚል ስንኝ ባይሰፍርበትም በመካሄድ ላይ ያለው ግን የአማራውን ቦታ ከሕግ ውጪ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚኖሩ የውጭ ዜጎች ነው።
እንግዴህ ይህን ሁሉ ከላይ ያሰፈርኩትንና ሌሎች ያላሰፈርኳቸውን በአማራው ላይ የሚደረገውን ግፍ በራሴ ላይ ካልመጣ አያገባኝም ማለት ስለአላስቻለኝ ሞረሽን ለመተባበር ተነስቻለሁ፤ አማራ ባትሆኑም እንደሰብአዊ ፍጡር አንድ ሰው አማራ ስለሆነ ብቻ ይሄ ሁሉ ተዘርዝሮ የማያልቅ ግፍ ሊፈጸምበት አይገባም ብለን ኢትዮጵያውያን በሙሉ በህብረት ልንነሳ ይገባል፤ ወያኔ አማራን የጠላው በኢትዮጵያዊነት አቋሙ እንጂ በሌላ አይደለም፤ ይህ አቋም ደግሞ መቼም ፍንክች አይልም።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
ታዛቢው

15 Comments

    • We will not go away but will stay in put as your nightmare. You will go to your grave dreaming about the demise of Amharas.

  1. ወያኔ እንኳን ያላለውን ከሸዋ ከፍለህ “ሰሜን ሸዋ” ከወሎም ከፍለህ “ከፊል ወሎ” ነው አማራ እያልክ ነው። ለመሆኑ ይህ የሚያስከትለውን ችግር ተረድተኸዋል? ማንንስ የበለጠ እንደሚጠቅም አዙረህ አይተኸዋል? ሞረሽ ብዙ ጊዜ ተነግሮት እየሰማና እየተማረ አይደለም። “አንድ ጅል የተከለውን ሃምሳ ሊቅ አይነቅለውም” የሚባለው እንደዚህ ዓይነቱ ነው። ጥቂት መጻሕፍት ስላነበቡ ብቻ ፖለቲከኛ መሆን አይቻልም። ሞረሽ በዚህ በያዘው አካሄዱ ለአማራው ራሱ ድርጅቱ ትልቅ ሸክም ነው የሚሆንበት። ይህ ነው የሚባል አስተዋጽዖ ላያበረክትለት እየማቀቀ ያለው አማራ በበለጠ የሚመታበትና በሌሎቹ ወገኖቹ ዘንድ በጥርጣሬ እንዲታይ ስም ነው የሚሆንበት። እባካችሁ ንቁ! ካልሆነ ግን አይደለም አማራውን እናንተ ልትወክሉት ይቅርና እናንተን ማን እንዳቋቋማችሁና የማንን ተልእኮ እንደምታስፈጽሙ የበለጠ ግልጽ እየሆነ ይመጣል። ይህን ምክር ተጠቅማችሁ የበሰለ፣ በመረጃ የጎለበተ፣ ጊዜውን የዋጀና በትክክል የአማራውን ተክለ ሰውነት፣ ግርማ፣ አርቆ አስተዋይነትና ክብር የሚመጥን ጠንካራ ድርጅት እንድትመሠርቱ ምኞቴ ነው።

    • SOL

      Talk is cheap. If you have the guts and want to do something worthwhile, get down from your high horse and join MORESH. If not keep your unsolicited comments to yourself. MORESH is doing something meaningful while your likes are talking and staying put.

      • Girma,
        First of, the article (by the so called “ታዛቢው”) is written in Amharic. That was why my comment was in Amharic. Now, from the number and nature of comments you put forward here (3 out of a total of 8 comments, and all your comments against people commenting on the Amharic article) it is most likely you are the writer of the Amharic article in the first place. That being said, why are you hiding yourself behind a fake name (“ታዛቢው”) for a “just cause”? Secondly, why are you cursing and bashing everybody here instead of addressing the issues head on? Once again, your imbecile cursing and arrogance will not help “Moresh Wogene” nor the great Amhara people. In fact, to the contrary. Your preference to use bad words against me and others here, instead of answering legit concerns and questions shows only one thing. You are either not the member of “Moresh” or you are an infiltrator. If “Moresh Wogene” approves your notion of “ሰሜን ሸዋ” and “ከፊል ወሎ”, then it will be one more step forward to unveil whose mission it is promoting. No human being can be that stupid, being arrogant and not addressing fellow people’s genuine concerns, and at the same time claim he/she stands vanguard to the Amhara people.

  2. Dear Moresh member,
    Please read in detail about Ethiopia and the so called Amhara, then you can write to inform others. By now ur knowledge of Amhara is by far limited. Our enemies have better knowledge of Amhara than u. You smell more as a TPLF or OLF than to the Amhara party

    • min abatchu tinchachalachu? hulachihum Amhara ayedelachihum-in fact do not call us Amhara, if you want to use the more formal name, say it as it is-Bet Amhara not Amara-dedeboch! sima yihen tsuhuf aqrabi-hulum afun yefeta Amhara new sitil atafrim? ena ye meles leje simhal em Amhara lithon new? midire deqalawoch zerachihun sataqu sitqeru wed Amhara guya tiwesheqalachu! ya demo mane new-yalekew demo professor getachew Haile-sima esu oromo new esat kale meteyiqun sima-ende esu ayenetochu new bahilachinin tarikachin, zerfew ewnetenjaw Bet Amharawin(wolloyewn ) ye qemut-semyarachu yiqerale enante ye shewa gujelewoch tetenqequ- ye Bet Amharawin identity serqachuma atikebrum enjam lijochachew tensitenal tarikachinin linadis mikinyatum balebetochum enja silehonen-ena eyandande wolloye yalhonk tig yize teqemet-zim bilachu sayigebachu ende ergo zimb tiliq atibelu-bisbis hula! beteref yaw ke galla gar yadegew amara nege bayu aseffa negash ke amara yiliq ye harar qotu yiqerbenjal bilwal ena min abatu yanchachewal ende wef? moresh moresh eyalik erashin sataq atilefadediben! Ahunim behone Bet Amharaw wolloye new! wollo demo ye kemisse ena bati galla sefari sim ayedelem-midir amara nege bayi minunim sayaq yiqebatiral! este 7 geze wollo bile chuhu amarenja mehonu yigebehal. @wudua-thank you this morons does not what the fuck they are talking! get over from us-
      Yimer Besha
      ke Adeyan Amhara qebele -dessie(dessye)zurya
      ye kemissie ena bati sefari galloch aleqa!
      P.S. enege ye kemissie ena bati sefari galloch ande qeqit layi ye shewa gizat wetaderoch neberu -ye minilikem wetaderoch abizanjawoch galloch nebru

      • Who the hell you think you are to question anybody’s Amaranet? MORESH members do not want any kind of advice from Woyanes and their foot soldiers. Sid Adeg Balege!

        • @ze habesha-
          le eze wirgat girma tebeyew yesetewiten asteyayet lemin approve aladerkewim? gid yelem-yihe gujele zerun emayaq bisibis-afun be amaranja silefeta Amhara yimeselwal ena ende esu yalutin hulu teqebelu yilenal! endezama behone hailessilasie le Amharaw dehina neger badergu neber, ya gujele ye shewaw mengistu le amharaw melkam neger yaderg neber…abu sintu geltu gar gunche alfa kirkir enadergalen bakachu. ayzon ahun beqirbu ye rasachinin website enkefitalen.

  3. Stupid is what Stupid does. So, you are saying that Wello Is not Amara. Even if we say there are some oromos, who migrate to the area sometime ago, Wello has never been under the control of others. So, please stop talking rubbish as you don’t understand the boundaries of Amara. All Ethiopia was once under the control of Amara and you must know this before you write. You can be fool, but you cannot play foul. So, SHUT UP! Long live the Amara people throughout Ethiopia.

  4. Dear Abraham
    have you read the article carefully? wello is mentioned in the article als ( Bete Amhara) now it is not about the bounderies it is about the suffering of Amharas where ever they are. instead of hair splitting lets join our forces together. let’s not be blind about ethnicity just like TPLF. Our unity must be the power which brings us together. if you have slogan of long live Amhara start with protectings the interest of Amhra

    • dedeb nehe-sima tsufun abitertiro manbeb yemechil ayimro alen! ena atizebarq-demo moresh join argu sitil atiferam? yemanim gujele tarikachin sayaq endehum maninetachinin azabito ke emyay sibisb bisbis gar mesrat ketikmu gudatu yamezinal-enege dorzew hulu Amhara new yemelu geltuwoch nachew! qetilom shifraw shigute Amhara new sayilun yiqeral!

  5. Amharas have all the rights to stand for themselves. I think, you guys (all immigrants who reside inside Oromiyaa and other regions) may need to go back to Gonder and Gojjam, join your people in Gonder and Gojjam to liberate Amhara people and land from Wayane.

    Freedom to all!!

    • this is for i am oromo Look Engda sisenbet ageru yimslwal first you have to know your backgournd history who is immigrants oromo or amhara we are actually doing great job and we will teach you who is immigrants our brave AMHAR people will come soon and take over our beloved country Ethiopia

Comments are closed.

Previous Story

መንግሥት ለተፈጠረው ችግር በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ እንጠይቃለን!!!!

tplf rotten apple 245x300 1
Next Story

“ምን አዲሱ ትውልድ ብቻ የነገውም ዕዳ ውስጥ ተነክሯል”

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop