ቅዱስ ጊዮርጊስ በቱኒዚያው ክለብ 3 ለ 1 ተሸነፈ

(ዘ-ሐበሻ) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እየተካፈለ የሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በደጋፊው ፊት በቱኒዚያዊ ክለብ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 ተሸነፈ። በውድድሩ በከቱኒዚያና ማሊ ክለቦች ጋር ተድልድሎ በመጫወት ላይ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬ ኦገስት 18፣ 2013 በምድቡ መሪ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 በመሸነፍ ደጋፊውን አንገቱን አስደፍቷል።

ሲ ኤስ ሰፋክሲን በምድቡ ያደረጋቸውን ሶስት ጨዋታዎች በማሸነፍ 9 ነጥብ እየመራ የሚገኝ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ስታዲ ማሊን አሸንፎና በኢቶልዲ ሳህልና ሲ ኤስ ሰፋክሲ ተሸንፎ በ3 ነጥብ ይዟል፡፡ በደጋፊው ፊት የቱኒዚያውን ሲ ኤስ ሰፋክሲን የገጠመው ጊዮርጊስ ጨዋታው ከባድ እንደሚሆንበት የስፖርት ተንታኞች ይናገራሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይድረስ ለአማራ አክቲቪስቶችና የሚዲያ ሰዎች! - ይነጋል በላቸው
Share