February 9, 2024
5 mins read

ወድቃ አትቀርም የኛ እናት!

Flag

እንደ ተርብ በራ ወግታቸው፤ ሊደፍሯት ሲቅነዘነዙ፤
አለቃት ብሎ ቂማቸው፤ ዛሬም እንደ ትናንቱ፤
ባንዳ አሳድገው ላኩባት፤ የሚያገለግል በሆዱ፡፡

መርዝ እንደ ዲዲቲ ረጭተው፤ ያልደፈሯትን ወይዘሮ፤
ዛሬ ጠለፈው ወሰዷት፤ አምልገው ገብተው በጓሮ፤
ውሾችን ፓውንድ አጉርሰው፤ እያማለሉ በዩሮ፡፡

ጭንጋፍ ልጆቿን አንስተው፤ እንኩቤተር ውስጥ አኑረው፤
እንደ ጥንብ አንሳ አራብተው፣ እንደ ኖህ ቁራ ቀፍቅፈው፣
በቋንቋ አሙካ አንቅረው፤ በዘርም እድፍ አጥምቀው፤
እንደ ተምች አሰማሩባት፤ እንዲያዳክሟት ቆራርጠው፡፡

እርጥባን ንፍሮን እርዳታ፤ ለእድገት ለጤና እያሉ፤
እርጉም ልጆቿን ቀልበው፤ ወዳጄ ጓዴ እያሉ፤
የቋንቋ ካራ አቅርበው፤ ገላዋን እያስመተሩ፤
ምስጢሯን ሁሉ ገላልጠው፤ ድንግልናዋን ገፈፉ፡፡

የራሷን ድንበር ተሻግራ፤ የሰውን ምድር ባትነካም፤
አፍሪካን ነፃ በማውጣት፤ አለም ጠቅላላ ቢያውቃትም፤
ጎረቢቶቿን በፍቅር፤ ቡና እምትጋብዝ ብትሆንም፤
እጇ አመድ አፋሽ ነውና፤ ተኝተውላት አያውቁም፡፡

በሰላም በፍቅር እንዳትኖር፤ እንደ በፊቱ ተከብራ፤
አዳቅለው ለቀውባታል፤ ነክሶ እሚያናክስ ቡችላ፤
ታይቶም እማይታወቅ፤ የውሻና ጅብ ዲቃላ፡፡

በአፈሯ ጥጥን አብቅለው፤ ውኃዋን ለመስኖ አውለው፣
ፉሉን በባውንድ ጠቅልለው፤ ለቤቷ ውሾች አጉርሰው፤
ጀርባዋን ልጠው ወሰዱት፤ እንደ ፍሪንባ አውጥተው፡፡

በክብር አልባ ገዥዎች፤ በደላላዎች ተይዛ፤
የአርበኛ ያለህ ትላለች፣ ክብሯን ፈልጋ እማማ!

ልጆቿ ከውጪ ቢጮሁ፤ ቢያመልክቱ ለዓለምም፤
ሞቷን የሚመኝ እንጅ፤ የሚታደጋት አልታዬም፡፡

ፍትህ ጋጋሪ ወይዘሮ፤ የሰው መገኛ ብትሆንም፤
ማንም በእውነት መስክሮ፤ ፍርድ ሰጥቶላት አያውቅም፡፡

ከጀንበር መግቢያ አድሎ እንጅ፤ ፍትህ አይጠበቅም፤
ሮማውያኖች ፈርደው ነው፤ የተሰቀለው አምላክም፡፡

በኤደን ምስል ቢስላት፤ በክብር ቢያነሳት መጣፉም፤
የፍትህ ምድር እያለ፤ ቢያቆላምጣት ቁርአኑም፤
ቂመኛ ጠላትን እንጅ፤ ወዳጅ አፍርታ አታውቅም፡፡

በዓለማዊ ጥቅም ተይዘው፤ ልጆቿ ለግመው ቢተኙም፤
የእናት ትካዜ ውሎ ሲያድር፤ ጎናቸው ምድር አይነካም፤
እንደ ቀደምቶች በአንድነት፤ መነሳታቸው አይቅርም፤
ከጉድጓዱ ውስጥ ሊያወጣት፤ ፈጥኖ ይደርሳል አምላክም፡፡

ይሁዳ መቅቡጡን ልሶ፤ ጠቁሞ ችሎት ቢያውላት፤
ፈሪሳውያንም መስክረው፤ እንድትሰቀል ቢያደርጓት፤
ጲላጦስ እጆቹን ታጥቦ፤ የሞት ውሳኔ ቢሰጣት፤
በቋንቋ በዘር ካስማ ላይ፤ እጇን ከርችመው ቢሰቅሏት፤
በጎጥ እራፊ ከፍነው፤ በክልል ሳጥን ቢቀብሯት፤
እኔም እንደ አቅሜ ህልም አለኝ፤ ወድቃ አትቀርም የኛ እናት፡፡

ብድግ ትላለች እማማ፤ በቅዱስ ልጆች መስዋእት፤
መቃብርን ሰንጥቃ ወጥታ፤ ዳግም ልትሆን እመቤት፤
በእምነት በጸሎት በርትታ፤ ዳዊት በመዝሙር እንዳላት፤
እጇን ዘርግታ ወደ አምላክ፤ ቡራኬ ደርሷት ምርቃት፡፡

ወድቃ አትቀርም የኛ እናት፤ በክልል ሳጥን ቀብረዋት፤
ብድግ ትላለች እማማ፤ በጀግና ልጆች መስዋእት፤
መቃብርን ሰንጥቃ ወጥታ፤ ዳግም ልትሆን እመቤት፤
በእምነት በጸሎት በርትታ፤ ዳዊት በመዝሙር እንዳላት፤
እጇን ዘርግታ ወደ አምላክ፤ ቡራኬ ደርሷት ምርቃት፡፡

በላይነህ አባተ ([email protected])
የካቲት ሁለት ሺ ሰባት ዓ.ም.

GF4ZlvlWMAAuDVh

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው እና አሁን ላይ በአማራ ፋኖ በጎጃም የሁለተኛ (ተፈራ ) ክፍለጦር ሰብሳቢ የነበረው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ በክብር ተሰዋ። የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የህሎና አደጋ ለመቀልበስ ያለ

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሐዘን መግለጫ ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል !

January 22, 2025
ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

Go toTop