November 22, 2023
3 mins read

አቡነ ኤርምያስ ሆይ፣ ቤተክሲያን በክብር የደፋችልወትን ቆብ በክብር ያውልቁ! 

Ermias 1 1

Ermias 1 1

አቡነ ኤርምያስ ሆይ፣ ቅድስት ቤተክሲያን አቡን (ማለትም የሐይማኖት አባት) ያደረገችወት ፍርድ ጠፋ፣ ግፍ ተንሰራፋ፣ ፍትሕ ጎደለ፣ ሕዝብ ተበደለ እያሉ ለተገፉ፣ ለተበደሉና ለተጨቆኑ መዕምኖችወ እንዲጮሁ መሆኑን ለርስወ መንገር አያስፈልግም።  ርዕት ቤተክሲያን መንፈሳዊ አባት ያደረገቸወት በሂወትወ ቆርጠው፣ ለመስዋዕትነት ራስወን አዘጋጅተው፣ ለፍትሕ ርትዕ በመቆም ግፈኞችን ያለ ምንም ፍራቻ አጥበቀው እያወገዙ በመንፈሳዊ መንገድ አጥበቀው እንዲዋጓቸው ነው።

እርስወ እያደረጉ ያሉት ግን በዳይም ተበዳይም እንዳይቀየሙወት ከበዳይም ከተበዳይም ጋረ የቆሙ እያስመሰሉ፣ እንደ ሸማኔ መወርወሪያ እዛና እዚህ እያሉ፣ እርስወን በማይመጥን በሚያሳፍር ሁኔታ መለሳለስና መቅለስለስ ነው።  ልወደድ ባይነት ደግሞ የሐይማኖት አባት ሳይሆን የፖለቲከኛ ባሕሪ ነው።  ስለዚህም የርስወ ተግባር ሙሉ በሙሉ የሚመሰክርብወት የሐይማኖት አባትነት ሳይሆን የፖለቲከኛነት ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ነው።

ሙሉ ፖለቲከኛ በመሆን የሚፈልጉትን ቡድን ሙሉ በሙሉ መደገፍ ሙሉ መብትወ ነው።  የሐይማኖት ካባ ለብሰው የፖለቲካ ደባ የመፈጸም መብት ግን የለወትም።  አለበለዚያ የሐይማኖት አባት በማድረግ ያከበረችወትን ቅድስት ቤተክሲያን ማራከስ ይሆንብወታል።  ስለዚህም እያራከሷት ያሉት ቅድስት ቤተክሲያን አውግዛወት የደፋችልወትን ቆብ ሳታወልቅበወት በፊት እስወ ራስወ በገዛ እጅወ እንዲያወልቁት ይመከራሉ።  በወያኔና በኦነግ የተዋረደቸው የቅድስት ቤተክሲያን ልዕልና እርስወ ከሚገምቱት በላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተቃረበ ስለሆነ፣ ቆብወን በገዛ እጀወ አውልቀው የቀረቸወትን እንጥፍጣፊ ክብር ለመጠበቅ ያለወት ጊዜ በጣም አጭር ነው።  ሳይመሽ ገሽሽ ይበሉ።

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

2 Comments

  1. ዻዻሱን በዚህ ደረጃ ለመተቸት ወይም ለመምከር እሳቸው ባሉበት ቦታ መሆንን አለበለዚያም እዚችው አጦቢያ ውስጥ ሆኖ ቢናገሩ አልያም ቢጽፉ ሀሳብዎ ሚዛን ይደፋ ነበር።

  2. ቤተክርስቲያን የዳፋችልዎትን ቆብ በፈቃድዎ ያውልቁ ከማለት ቤተ ክርስቲያን የደፋችልዎትን አስኬማ በፈቃድዎ ያውልቁ ለፖለቲካው ንግድ እንዲያመች ባርኔጣ ይድፍ ማለቱ አይቀልም?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

822
Previous Story

የደሴው ስብሰባ አገዛዙን አተረማምሶታል | “ፋኖን ገዝተን እናስረክባችኋለን” ካህኑ | ኤርትራ ጦሯን ወደ ኢትዮጵያ አስጠጋች

187275
Next Story

የአማራ ህዝብ ተበድሏል። ይህ መንግስት ለሁሉ ነገር ጥፋተኛ ነው። እኔ ፋኖን አልወቀስኩም። ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop