October 27, 2023
5 mins read

የኮንጎ፣ የኮሪያ ዘማቾች እና የኢትዮጵያ አብዮታዊ ሰራዊት ሁሌም በክብር ሊዘከሩ፣ ሊታወሱ  ይገባቸዋል!!

image 12

አገርህን ጠላት እንዳይደፍራት ወታደር ሆነህ ጠብቃት፣ እንደ አባቶችህ ጀግና ሆነህ አሳያት፣ በጀግንነት ታሪክ ሥራላት። ታሪክ ያለው ከወታደርነት ነው፣ ጀግንነት ያለው ከወታደርነት ነው። ጀብዱ ያለው ከወታደርነት ነው፣ ታላቅ ስም ያለው ከወታደርነት ነው…።›› የሚል የአባቶቻችን የጀግንነት የአደራ ቃል ውርስ አለን እኛ ኢትዮጵያውያን፡፡

በርግጥም ደግሞ ታሪካችንን ስንፈትሽም- ታላቁ የዓድዋ ድል የአርበኝነት፣ የወታደርነት ውጤት ነው፡  የአምስት ዓመቱ የጣልያን ወረራና የኢትዮጵያዊያን ድል የወታደርነት ውጤት ነው፡፡ ካራማራ የወታደርነት ውጤት ነው፣ የኢትዮጵያ የተከበረ ታሪክ የወታደር ታሪክ ነው፡፡ ለምን ሲባል ኢትዮጵያ የተከበረችው በጀግኖች ልጆቿ፤ በወታደሮች ብርቱ ክንድ ነውና፡፡

ዛሬ እኔም፣ አንተም ሁላችንም የቆምንባት የኢትዮጵያ ምድር በቀደሙ ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን ደምና አጥንት መሠረትነት የተገነባ ነው፡  ታሪክ እንደሚነግረን በኢትዮጵያ ጉዳይ ሁሉም አርበኛ፣ ሁሉም ጦረኛ ነው፡፡ ሁሉም ሰንደቁን አስቀድሞ ይገሰግሳል፡፡ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን በየዘመናቱ ጀብዱ እየሠሩ ዛሬ ላይ ኮርተን የምንኖርባት አገር፣ ኮርተን  የምንናገረው፣ በአሸናፊነት የምንመሰክረው ታሪክ አኑረውልናል፡፡

ከጉንደት እስከ ጉራዕ፣ ከዓድዋ እስከ ማይጨው፣ ከኦጋዴን እስከ ካራማራ… ያበበ የኢትዮጵያውያን ጀግንነትና እምቢ ለነፃነቴ ባይነት፣ የኢትዮጵያ ድንበር ሳይገድበው አውሮፓ ምድር ሮም/ጣሊያን ድረስ ተሻግሮ ዓለምን ያስደመመ፣ በኮሪያ ልሣነ ምድር፤ በአፍሪካ (በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በሱዳንና በሶማሊያ ምድር የኢትዮጵያ ሰራዊት በተጋድሎ ድልና በሰላም አስከባሪነት ትልቅ ስምና ዝናን ያተረፈ ነው።

እነዚያ ጀግኖች ታሪክ ሠርተው፣ ስማቸውን ከመቃብር በላይ ትተው ‹አገሩን ያስደፈረ ታሪክ ይውቀሰው፣ አፅማችንም እሾህ ሆኖ ይውጋው› ብለው ቃል ኪዳን አስረው፣ አደራ ሰጥተው በክብር አልፈዋል። ትናንትና በመስቀል አደባባይ ለ116ኛ ጊዜ በተከበረው የመከላከያ ሰራዊት ቀን በኮንጎና በኮሪያ ዘምተው ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ በጀግንነትና በድል ከፍ ያደረጉና በክብር ያስጠሩ  አባቶቻች ተዘክረው ነበር። በወታደራዊ ሰልፍ ትርዒትም /Military Parade/ ዐይተናቸዋልና ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ክብር ተሰምቶናል። ታሪካችን ምልዑና የተከበረ  ማድረግ የምንችለው  ትናንትናን ጥለን ዛሬን አንጠልጥለን አይደለምና የኢትዮጵያን በነጻነትና በሉዓላዊነቷ አስከብረው ያቆዩልንን የትናንትና ጀግኖቻችንን ሁሌም በክብር ልንዘክራቸው ይገባል፡፡

በዚህ የጀግንነት ገድል ታሪክ ውስጥ ደማቅ ታሪክን አሻራ ከተዉ ኢትዮጵያውያን መካከል- ከበርካታ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ታላቅ አኩሪ ታሪክን ለሀገሩ ያስመዘገበውን አርበኛውንና በተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪ በመሆን ኮንጎ ድረስ የዘመተውን የወላጅ አባቴን አኩሪ የታሪክ ቅርስ ፎቶዎች ላጋራችሁ ወድድኹ፡፡

ምስሉ የኢትዮጵያዊው ጀግና አርበኛ እና በኮንጎ የተባበሩት መንግሥታት ሰላም አስከባሪ ሆነው ያገለገሉትና እስከ በሕይወታቸው እልፈት ድረስም በጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር በጸሐፊነት ያገለገሉት ወታደራዊ መኮንን፣ አርበኛው፣ የመ/አ ወርቁ ደስታ ምስሎች ናቸው፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ “ይድረስ ለእገሌ” ማለቱ ሰለቸኝና ተውኩት እንጂ ዛሬም መጻፍ የፈለግሁት የአማራን ዕልቂት ለመታደግና የኢትዮጵያን ትንሣኤ ለማብሰር እየተዋደቁ ላሉት ወገኖቼ ነው – በፋኖም ይሁን በሌላ ስም፡፡ ኢትዮጵያን ወደቀደመ ክብሯ ለመመለስ የነገድና

ጀልባዋ አትሰምጥም፤ የሚሰምጥ ግን አለ!

[ማስታወሻ ከፍል አንድ፣ በዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ኦፍ ጃዋር አንድ ኢትዮጵያ ተብሎ በእንግልዝኛ ወጥቷል] (https://zehabesha.com/of-jawar-and-ethiopia/) ባለፈው ሰሞን፣ ጃዋር መሐመድ ከደረጀ ኃይሌ ጋር  በነገራችን ላይ ክፍል ሁለት ባደረገው ቃለ ምልልስ ላይ ተመስርቼ ገንቢ አስተያየት ጽፌ በኢንግሊዝኛው ዘሐበሻ ድረ ገጽ ላይ አሳትሜ ነበር። አስተያየቴ በዚህ ቃለ ምልልስ

ስለ ጃዋርና ኢትዮጵያ (ክፍል ሁለት)

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

Go toTop