October 27, 2023
7 mins read

የአማራ የሕልውና ትግል ላማረኛ ቋንቋ የከፈተው ትልቅ ዕድል

ሳይደግስ አይጣላም

Screen Shot 2021 09 05 at 125001 AM 600x223 1

አማረኛ ቋንቋ ማናቸውንም ነገር በቀላሉ ለመገለጽ የሚያስችል እጅግ በጣም ቀና፣ ቅን፣ ተጣጣፊና፣ በዚያ ላይ ደግሞ ውብ ቋንቋ ነው፡፡  ባጭሩ ለመናገር ደግሞ አማረኛ እንዳበጁት የሚበጅ ድንቅ ቋንቋ ነው።  ይህን እንዳበጁት የሚበጅ ድንቅ ቋንቋ በስርዓቱ በማበጃጀት፣ እንግሊዘኛን ጨምሮ ዐበይት ከሚባሉት ከማናቸው የዓለም ቋንቋወች ጋር አቻ እንዲሆን ብቻ ሳይሆን እንዲበልጥም ማድረግ ይቻላል።   አማረኛ የሚበጃጀው ደግሞ የቆሸሸውን በማጽዳት፣ የተሳሳተውን በማረም፣ የተዘበራረቀውን በማደረጃጀትና አስፈላጊወቹን አዳዲስ ቃሎች በመፍጠር ነው፡፡  አስፈላጊወቹን ቃሎች ለመፍጠር ደግሞ ግእዝን የሚያህል ተቀድቶ የማያልቅ የቃላት ምንጭ አለው።

ዐረብኛን ከተለያዩ ቋንቋወች ጋር በማዳቀል ትናንት የተፈጠረው፣ የላቲን ፊደል የሚጠቀመው መናኛው የስዋሂሊ ቋንቋ የምሥራቅ አፍሪቃ ወል ቋንቋ (lingua franca) ለመሆን ሲበቃ፣ አፍሪቃዊ ፊደል ያለው፣ እንዳበጁት የሚበጀው ታላቁ የአማርኛ ቋንቋ ግን ድንበር ሊሻገር ያልቻለው፣ የጦቢያን ቢሮክራሲ ባብዛኛው የተቆጣጠሩት፣ አማረኛን እጅግ አምርረው የሚጠሉት የትግሬና የኦሮሞ ልሂቃን አንቀው ስለያዙት ብቻና ብቻ ነው፡፡  ከነዚህ የኦሮሞና የትግሬ አማራ ጠሎች ጋረ በመተባበር አማረኛን የሚወጉት ደግሞ ባማረኛቸው እንዲያፍሩ ተደርገው ጥራዝ ነጠቅ እንግሊዘኛ መፃፍና መናገርን ከምሁርነት የሚቆጥሩት የነ ዋለልኝ መኮንን ግርፎች ናቸው።

በደርግ ዘመን የአማረኛ ትምህርት ከዩኒቨርስቲ እንዲወገድ ያደረጉት አማራ ጠሎቹ የትግሬና የኦሮሞ ልሂቃንና የነሱ አጫፋሪ አማራ ተብየወች ነበሩ፡፡  ለምሳሌ ያህል በ1976 ዓ.ም የፍልስፍና ትምህርት ባዲሳባ ዩኒቨርሲቲ ባማረኛ ተሰጥቶ አመርቂ ውጤት ቢያስገኝም፣ አማራ ጠሎቹ የትግሬና የኦሮሞ ልሂቃን እንዲሁም አማራ ነን ባይ አጫፋሪወቻቸው  ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስተው ትምህርቱ ባማረኛ መሰጠቱ እንዲቀር አድርገዋል፡፡  በኦነግ ዘመን ደግሞ የጭራቅ አሕመድ የትምህርት ሚኒስቴር የሆነው ብርሃኑ ነጋ አማርኛ ቋንቋ በትምህርት ዐይነት ደረጃ እንኳን እንዳይሰጥ ከፍተኛ ዘመቻ ጀምሯል።  ይህን ዘመቻውን የጀመረው ደግሞ በራሱ ባማራ ክልል ውስጥ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ ነው።

በሌላ በኩል ግን ሳይደግስ አይጣላምና የአማራ ሕዝብ ሊያጠፉት የተነሱትን ወያኔና ኦነግን በማጥፋት ሕልውናውን የማስጠበቅ ዘመቻውን እንደ ሰደድ እሳት አቀጣጠሎ ያያቶቹን መሬት ከፀራማሮች እያፀዳ ነጻ ማውጣት ጀምሯል።  ስለዚህም በነዚህ ነፃ በወጡ ቀጠናወች ውስጥ ሮሞ ወይም ትግሬ ይቀየማል ብሎ ሳይሰጋ ወይም ደግሞ ይሉኝታ ሳይሰማው እንግሊዘኛን ሙሉ በሙሉ ባማረኛ በመተካት ልጆቹን ሙሉ በሙሉ (ሁሉንም የትምህርት ዐይነቶች) ባማረኛ እያስተማረ እንደ ጃፓንና ኮርያ አገሩን በፍጥነት የሚያሳድግ ትውልድ በፍጥነት የመፍጠር ትልቅ ዕድል ተከፍቶለታል።  ይህ መቸም የማይገኝ ዕድል ሊያመልጠው ስለማይገባ ደግሞ እስክንድር ነጋንና ዘመነ ካሴን ጨምሮ ሁሉም ያማራ ሕዝባዊ ትግል አመራሮች በፍጥነት ሊተገብሩት ይገባል።

እንግሊዘኛ እንግሊዞች በቅኝ ወረራ ዓለም አቀፍ ቋንቋ እንዲሆን ያደረጉት፣  ውስጡ ለቄስ የሆነ፣ በግድ እንጅ በውድ ሊመረጥ የማይችል ቅጥ ያጣ ቋንቋ ነው፡፡  በተለይም ደግሞ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ለሰገል (science) እና ኪንሲን (technology) ሊያገለግል የቻለው አመቺ ሁኖ ሳይሆን በዓለም ልሂቃን ያላሰለሰ ድካም ነው፡፡  ስለዚህም የአሜሪቃ ኃያልነት ሲያከትም፣ የእንግሊዘኛም ዓለም አቀፍ ቋንቋነት እንደሚያከትም ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡  ለምሳሌ ያህል እንግሊዞኝ የዜሌንስኪ (Zelensky) ቀንደኛ ደጋፊወች የሆኑት ለዩክሬን ሕዝብ አስበው ሳይሆን፣ ራሺያ ድል አድርጋ የምዕራባውያንን የበላይነት ላንዴና ለመጨረሻ ከሰበረች፣ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እንዲሁም የራሷ የእንግሊዝ አገር የመጨረሻው መጀመርያ (the begining of the end) መሆኑን በርግጠኝነት ስለሚያውቁ ነው፡፡

የፈረንጅ ቅጥቅጦች የሆኑት የትግሬና የኦሮሞ ልሂቃን እንግሊዘኛን አመለኩ አላመለኩ፣ የአማራን ሕዝብ የማይመለከት የነሱ የራሳቸው ጉዳይ ነው፡፡  ባማንነቱ የሚኮራው የአማራ ሕዝብ ግን የሱ የራሱ የሆነ፣ እንዳበጁት የሚበጅ ምርጥ ቋንቋ እያለለት፣ ሳይቸግረው ጤፍ እየተበደረ፣ ፈረንሳይ ሲነግስ ፈረንሳይኛ፣ እንግሊዝ ሲነግስ እንግሊዘኛ፣ ቻይና ሲነግስ ቻይንኛ እየተጠቀመ ከቋንቋ ቋንቋ የሚንጦለጦልበት ምንም ምክኒያት የለውም፡፡

 

መስፍን አረጋ

[email protected]

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

Go toTop