October 7, 2023
6 mins read

የሰላም ዋጋው በእውነት ስንት ነው?  – ሙናች ከአባይ ማዶ ፊላው ስር  ገሳ ለብሶ እየቆዘመ 

በፕሮስታንት ጠንቋይ የሚመራው ጨካኙ እርኩስ መንፈስ ያደረበት ፋሺሽቱ ደም መጣጭ አብይ አህመድ አሊ
በፕሮስታንት ጠንቋይ የሚመራው ጨካኙ እርኩስ መንፈስ ያደረበት ፋሺሽቱ ደም መጣጭ አብይ አህመድ አሊ

በምድራችን ሰዎች ሲገናኙ “እንደምን አደራችሁ፣ እንደምን ዋላችሁና እንደምን አመሻችሁ” የሚባባሉት የሰላምታ ትክክለኛ ትርጉም ለብዙዎቻችን በደንብ የገባን እና የተረዳነው አይመስልም::

ጨለማን ተገን አድርጎ ንብረትን ብቻ ሳይሆን የሰውን ነፍስ ሳይቀር የሚዘርፈው ሌባ ወንብዴ የሚነግሥበትን እይታ አልቦ ጊዜን ምንም ሳንሆን አልፈን ብርሃን ላይ መድረስ ብቻ ሳይሆን፣ ሲደክም የዋለው ሥጋችን ያለስጋት ተዘልሎ በጤና እንቅልፍ ጠግቦ መነሳት መቻል ‘እንደምን አደራችሁ’ የሚለው ጥያቄ ቀላል የልማድ ጥያቄ ብቻ አይደለም! በተኛንበት ሰዓት ዘራፊና ገዳይ የነገሠበት ጊዜ ስለሆነ ጭምር እንጂ!
አብዛኛው ሰው የለመደውና የሚያውቀው ነገር ይቀልበታል! ሲርቀውና ሲያጣው ግን በጸጸት ዋጋ ከፍሎ ሳይቀር ሊያገኘው ይሻል “በእጅ ያለ ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል” የሚለው አባባል ይህን ሃሳቤን የሚገልጽልኝ ይመስለኛል::
ትምህርቴን ጨርሼ ሥራ በያዝኩበት ትንሽ ዓመታት ውስጥ ሰሜን ኢትዮጵያን እስከ ምጽዋ ወደብ፣ ምስራቅ ኢትዮጵያን እስከ ጅጅጋ፣ ደቡብ ኢትዮጵያን እስከ ሲዳሞ አዋሳ ላንጋኖ አርባ ምንጭ፣ ምእራብ ኢትዮጵያን መተከል ጉብላክና አጋሮን ድረስ ያለምንም ስጋት ተዘልዬ በደስታ ጎብኝቻለሁ ዛሬ ግን አይደለም ከአዲስ አበባ ከተማችን መውጣትም ሆነ መግባት ይቅርና ከቤትህ ጠዋት ወተህ ማታ መዳረሻ ማደሪያህ የት እንደሚሆን አንተም ሆንክ ቤተሰብ ጭራሽ ማወቅ አይችልም::
ትናንት በአገሪቱ ሙሉ ስፋትና ወርድ በደስታ እና በሰላም የፈነጨንባት ምድር ዛሬ ክቡር የሆነው ሰው በተገኘበት እንደ በግ ግልገል ተይዞ እየታሰረ የገንዘብ ማግኛ ዋና ምንጭ ሆኖ ስናይ ትናንት ለነበረው የጋራ አንድነትና ሰላማችን የሰጠነውን ዋጋ እና በሕዝባችን መካከል ዛሬ ላለው ሰላም የምንሰጠው ዋጋ ምን ያህል ነው? ብለን መጠየቅ ግድ ይላል::
ዛሬ በእውነት ተወልደን ሳንሰበር እየዘለልን ባደግንባት የጋራ አገራችን ውስጥ ያለው የሕይወት ትርጉም ምንድነው? እያንዳንዱ ሰው አስቦና አቅዶ ላልሆነው ማንነቱ ይህን ያህል መከራና ስቃይ ማየት እና መገደል አለበት? በዚህ እልህ አስጨራሽ ጥላቻና መሳደድ በእውነት አሸናፊና ተሸናፊ ይኖር ይሆን? እሺ እንደ ወያኔ ጊዜ ወይም ወቅት የሰጠው ወይም በለስ የቀናው አንዱ ወገን ያሸንፍ እንበል! የዛሬ ተሸናፊና ተገዳይ ነገ ዝም ብሎ አሜን በማለት የሚቀበል ልብ ያለው ይመስላችሁዋል?
አይደለም ተሰዳጅና ተገዳይ ይቅርና ገዳይና አሳዳጅ ሳይቀር በሠራው የጥል እና የክፋት ሥራው ሰላም አግኝቶ የተደላደለ ኑሮ ጨርሶ መኖር አይችልም! ሰው ተብሎ ሊጠራበት የተሰጠው ሕሊናው ካልደነዘዘ በስተቀር!
ስለዚህ ለተነሳንበት የሰላም ዋጋው ስንት ነው? ጥያቄ የእኔ የትንሽዋ አእምሮ መልስ አንተ ለሌሎች፣ ሌሎች ላንተ፣ እያንዳንዱ ለሁሉ፣ ሁሉም ለእያንዳንዱ ያለው ምልከታ እና አቀባበል ነውና ሁሉም የራሱን ኃላፊነት በአግባቡ ይወጣ! እንብሰል! እንደግ! አንዱ ለሌላው የሰላም ኑሮ ወሳኝ አጋር መሆኑን አውቆ ዛሬ ባለበት ላይ ሆኖ ነገን አሻግሮ በማየት ለትውልድ(ለልጆቹ)መልካም የሆነ ሌጋሲ ያቁም? ጥያቄ ነው!
ከዚህ በተረፈ የዛሬ ባለዕድል ጉልበተኛ ነገ እንደ ዛሬው TPLF ፀሐይ ልትጠልቅብህና ጨለማ ሊወርስህ እንደምትችል ረጋ ብለህ ካላሰብክ “የመውጊያው ብረት በአንተ ላይ ይብሳልና” እንደባለ አእምሮ ሰው ቆም ብለን እናስብ? ኑሮ ዛሬ ብቻ አይደለምና::
እመኑኝ አሸናፊና ተሸናፊ ፈጽሞ አይኖርም!
          ለጋራ ሰላምና እድገት
 ተከባብሮና ተቻችሎ መኖር የግድ ነው!
ሁሉም ለዚህ ዓላማ በጋራ ይሥራ፣!
ከታላቅ አክብሮት ጋር
ሙናች
ከአባይ ማዶ
ፊላው ስር
ገሳ ለብሶ
እየቆዘመ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop