የዳንኤል ክብረት ጎቤልሳዊ ፍፃሜ

ሐሳዊ ተዋኙ (con artist) ጭራቅ አሕመድ ወደር የለሽ የሐሰት ትወና ክሂሎቱን በመጠቀም አያሌ ጉምቱ ጦቢያውያንን አይዋረዱ ውርደት አዋርዷል።  ከሁሉም በላይ ያዋረደው ግን ያለ ምንም ጥርጥር ዳንኤል ክብረትን ነው።  ከሞላ ጎደል ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚያደንቁትን ሰው አር እንደነካው እንጨት እንዲፀየፉት አድርጓል። ዳንኤል ክብረትን የኦሮሞ ፅንፈኞች ድሮውንም ቢሆን ስለማይወዱት፣ ተልዕኮውን የጨረሰ ሲመስላቸው በርግጠኝነት አጋድመው ያርዱታል። ትግሬወች እጃቸው ላይ ከገባ ያለ ምንም ጥርጥር በዘይት ይቀቅሉታል።  አማሮች፣ ጉራጌወች፣ ጋሞወችና የቀሩት ደቡቦች ደግሞ በጫጭቀው ቢጥሉት ደስታውን አይችሉትም።

የዳንኤል ክብረት አንዱና ብቸኛው መፅናኛው በዚህ ደርጃ ያዋረደኝ ተራ ሰው ሳይሆን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነው የሚለው ነው። ስለዚህም የጭራቅ አሕመድ የስልጣን ዘመን መርዘም ከራሱ ከጭራቅ አሕመድ በላይ ለዳንኤል ክብረት የሞት ሽረት ጉዳይ ነው።  ጭራቅ አሕመድ ከስልጣን ከተወገደ ወይም ከሞተ ዳንኤል ክብረት የውርደቱን ብቸኛ መፅናኛ ስለሚያጣና ሕይወቱ ምንም ትርጉም ስለማይኖረው ራሱን ብቻ ሳይሆን ልጆቹንና ባልተቤቱን ይገድላል

በዚህ ረገድ ዳንኤል ክብረት ከናዚው የቱልቀዳ (propaganda) ሚኒስቴር ከዮሴፍ ጎቤልስ (Joseph Goebbels) ጋር በብዙ ረገድ ይመሳሰላል።  ጭራቅ አሕመድ በዳንኤል ላይ ያለው ፍፁማዊ ተፅእኖ (influence)፣ አዶልፍ ሂትለር (Adolf Hitler) በዮሴፍ ጎቤልስ ላይ ከነበረው ፍፁማዊ ተፅእኖ ጋር አንድ ዓይነት ነው።  ዳንኤል ክብረት አልፋና ኦሜጋውን ጭራቅ አሕመድን ያደረገው፣ ዮሴፍ ጎቤልስ አልፋና ኦሜጋውን አዶልፍ ሂትለርን እንዳደረገው ነው።  ዳንኤል ክብረት ጭራቅ አሕመድን እንደ እየሱስ የሚመለከተው፣ ዮሴፍ ጎቤልስ አዶልፍ ሂትለርን እንደ መሲሕ ይመለከት እንደነበረው ነው።  ዳንኤል ክብረት በጭራቅ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስተርነት ላይ ሙሉ በሙሉ የተንጠለጠለው፣ ዮሴፍ ጎቤልስ ባዶልፍ ሂትለር ቻንስለርነት ላይ ሙሉ በሙሉ ተንጠልጥሎ በነበረበት ሁኔታ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ይቅርታ እና ይቅር ባይነት - በዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ስለዚህም ያዶልፍ ሂትለር ቻንስለርነት ገመድ ሲበጠስ፣ ዮሴፍ ጎቤልስ የሒወቱ ክር መበጠሱን አውቆ፣ ስደስት ልጆቹን በሳይናይድ (cyanide) መርዞ ከገደለ በኋላ ራሱንና ሚስቱን እንዳጠፋው፣ የጭራቅ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስተርነት ገመድ ሲበጠስ ደግሞ ዳንኤል ክብረት ተመሳሳይ ድርጊት ያደርጋል።

ስለዚህም የዳንኤል ክብረት ያሁኑ ሙሉ ትኩረት የጭራቅ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ገመድ እንዳይበጠስ ማድረግ የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ነው። ጭራቅ አሕመድን አሁን ላይ የሚመክረው፣ የስልጣኑ ዋና ተቀናቃኝ በሆነው ባማራ ሕዝብ ላይ የከፈተውን የጭፍጨፋ ዘመቻ ይበልጥ አጠናክሮ፣ መጨፍጨፍ የሚችለውን ያህል እየጨፈጨፈ ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ማርዘም የሚችለውን ያህል እንዲያረዝም ነው።

ፋኖ ወደ ዐራት ኪሎ ሲቃረብ ዳንኤል ክብረት ጭራቅ አሕመድን የሚመክረው ደግሞ የራሺያ ቀይ ጦር (red army) ወደ ራይክስታግ (Reichstag) ሲቃረብ ዮሴፍ ጎቤልስ አዶልፍ ሂትለርን የመከረውን ምክር ዓይነት ነው።  የዳንኤል ክብረት ብቸኛ ክብሩና ጌጡ ጭራቅ አሕመድ በመሆኑ ሳቢያ የጭራቅ አሕመድ በማናቸውም መንገድ መዋረድ የሱ መዋረድ ስለሆነ፣ ጭራቅ አሕመድ ሙቶም ቢሆን ሬሳው እንዲዋረድበት አይፈልግም።  ስለዚህም፣ ለጭራቅ አሕመድ ባፅንኦት የሚመክረው፣ የመጨረሻው ሰዓት ሲደርስ ራሱን በራሱ እንዲገድልና ሬሳውን ደግሞ እሱ (ማለትም ዳንኤል ክብረት) በቤንዚን አቃጥሎ ደብዛውን እንዲያጠፋውና፣ ጭራቅ አሕመድ አልሞተም፣ የዳንኤል ክብረት እየሱስ አርጓል ተብሎ እንዲወራ ነው።

የመጨረሻው ሰዓት እስከሚደረስ ድረስ ግን፣ ጭራቅ አሕመድ በዳንኤል ክብረት ምክር መሠረት ባለ በሌለ ኃይሉ አማራን መጨፍጨፉን ይቀጥላል።  ስለዚህም ፋኖ አማራን መታደግ የሚችለው የመጨረሻውን ሰዓት በተቻለው መጠን በማፋጠን ነው።  አልበለዚያ ይዘገያል፣ ጅብ ከሄድ ውሻ ጮኸ ይሆናል።

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ብአዴን ማን ነው? (ገብረመድህን አርአያ፣ አውስትራሊያ)

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

1 Comment

  1. አይ ዳኒ እንዲህ አንገቱ ዘምበል እንዳለች ምን እያሰበ ይሆን? ያለፈው ክብሩን ወይስ አሁን አልፎ የሄደውንና ወደፊት ቦታ የሌለውን አልባሽነቱን? በል ይመችህ ከዘመዶችህ ከእምነት ወንድሞችህ ሸሽተህ እነ አህመዲን ጀበል እነ ኡስታዝ እገሌ እነ ጁዋር መሃመድና እነ አብይ መሃመድ ላይ ወድቀሃል እነሱ ከተሻሉህ መልካም፡፡ የወደፊትህን ለማየት ጓጓሁ ከሃጢያት በላይ የገዘፈ ሃጢያት የሰራህ ይመስል ስርየትህ አልታይ አለኝ መንፈሳዊ ዘይትህ ተንጠፍጥፎ አልቋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share