የህዝብን  የዓማታት ዕስር እና አሳር በማሳነስ እና ማድበስበስ የኢትዮጵያን ችግር መንቀስ አይቻልም

እንደ አገራችን የዘመን አቆጣጠር ግንቦት ስምንት ቀን አስራ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አንድ ጀምሮ የኢትዮጵያ ህዝብ ለራሱ እና ለአገሩ ብሄራዊ ሉዓላዊነት ካለዉ ከፍተኛ ልባዊ ፍቅር እና አክብሮት የተነሳ ዕርስ በራሱ በመደማመጥ እና በመደራጀት ያለማንም መሪ አስተባባሪ አስካዛሬ ከብዙ ዉጣ ዉረዶች ጋር አንድነቱን አስቀጥሏል፡፡

ይሁንና ከዚያች ክፉ ቀን ጀምሮ ጠላት ኢትዮጵያ አለቀላት ያለዉን በዕዉነተኛ እና ሀቀኛ ኢትዮጵያዉን ለመበተን ቋፍ በደረሰችበት እና ያለ ዕረኛ እንደተተወ የበግ መንጋ በሴራ የነበረዉ ማዕከላዊ መንግስት ሲናጋ በለስ የቀናቸዉ የዉስጥ የኢትዮጵያ ጠላቶች ሁኔታዉ ከጠበቁት በላይ ኢትዮጵያን ለመመዝበር እና ለማሳከር ዕድሉን በማግኘት ወደ ስልጣን ኮርቻ ወጥተዋል ፡፡

በህዝብ ተጋድሎ እና ትግል ኢትዮጵያ ጠላት እንዳሰበዉ ሳትሆን ማየት አምኖ መቀበል ያቃተዉ ኢትዮጵያን ዳግም አፍርሶ ለመስራት እና በራስ ልክ ለማድረግ ህዝብን አባር እና ገባር ማድረግ እና የታሪክ ሽሚያ መፍጠር ፣የነበሩትን መልካም ሥራዎች እና ሠሪዎች ማጣጣል እና ማግለል ዋና  የቅስቀሳ እና ወቀሳ (ፕሮፖጋንዳ) ስራ ሆኖ ለሁለት አሰርተ ዓመታት ቀጠለ ፡፡

የሚሳዝነዉ ግን አሁንም በኢትዮጵያ ህዝብ  የደም እና የህይወት ዋጋ የሚከፈልባቸዉን ብሄራዊ  ትግሎች እና ጥረቶች በማሳነስ እና በማድበስበስ ዕዉነተኝነት እና ትክክለኛነት የሚመስላቸዉ ግለሰቦች በማን አለብኝነት ለህዝብ እና ለአገር ያላቸዉ ጥልቅ ጥላቻ እና ንቀት ዛሬም ሲያስተጋቡ ማየታችን በኃጢያተ እና በስህተት ጎዳና መመላለስ ለለመደ  በአገር ላይ ለሚደርስ ጥፋት እና ክህደት እንደ ልማት እና ታማኝነት መለማመዱ በተለይ በመሪ ኢህዴግ መገለጫ ጠባይ ሆኗል፡፡

ኢህአዴግ ላለፉት ሶስት አስርተ ዓመታት በአገር እና ህዝብ ላይ ደጋግሞ ያሳየዉ  ጥፋት እና ክህደት በምድር ላይ በሰዉ ልጆች ከደረሱት ሁሉ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ፡፡ ይህም ሆኖ “ስልጣን እና አረቄ እያደር ወደ ራስ  ” አንዲሉ  በአገር እና ህዝብ መከራ መስከሩ  ዕዉነቱን እየገለበጠ መናገሩ አዲስ አይሆንም ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአንድነትን ፓርቲና የምርጫ ቦርድ - ግርማ ሠይፉ ማሩ

በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ የሰሜን ምዕራብ ግዛት ያለዉ ወቅታዊ እና አሳሳቢ ሁኔታ መነሻዉ እና መድረሻዉ ዓለም የሚረዳዉ ሆኖ ከመንስዔ አስከ መፍትሄ በስክነት እና በጥልቀት ከማይት ይልቅ ዞትር እኛ ትክክል ህዝብ ስንኩል ነዉ ማለት ቀዉስ እንጂ ዘላቂ መልስ  አይሆንም ፡፡

በዓማራ ህዝብ ላይ የተዘራዉ የጥላቻ እና ማግለል ሴራ መነሻዉ በኢትዮጵያዊነትም ፤ በማንነትም ሆነ በብሄራዊ  ደረጃ የነበረ ተሳትፎ በተቀናጀ እና በተደራጀ ሁኔታ መገፋት መሆኑ ነበር ፡፡

ይህ ከሆነ ለዓመታት ሲጠየቅ እና ሲጠበቅ የነበር የፍትኃዊነት ፣ ሉዓላዊነት እና ማንነት ….ጥያቄ  ምን እንዳይሆን ብሎ ለዓማትት ማመቅ ያስከተለዉ መነቃነቅ ነበር ፤ ነዉ ፡፡

ዕኮ ለምን ይሆን ዛሬም ለብሄራዊ አብሮነት እና ደህንት የሕዝብን ብሶት እና ምሬት ከመጋራት ይልቅ የዕምየን   ላብየ  ችግሩንም ምንጩንም የተወሰኑ ፣ጥቂት ……እያሉ  ችግር ላይ ችግር መዝራት ፡፡

ለመሆኑ ጥቂት ማን ነዉ  ጥቂትስ ከየት ነዉ   ዕንኳን ብዙሃን ያለበት መሆኑ እየታወቀ  ጥቂት ከአንድ ቢጀምር አንድም ሠዉ ማንቱ እና ነፃነቱ የገሰስ አለበት ወይ ፡፡

ለመሆኑ ጥቂቶች ተነጋሪዎች ትክክል ሲሆኑ ብአዙኃን ኢትዮጵያዉያን ስለ ራሳቸዉ እና አገራቸዉ  ዕዉነተኛ እና ፍትኃዊ  የመብት እና የመኖር ነፃነት ሲሹ  ትክክል የማይሆኑት እንዴት ነዉ ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል ፡፡

በመላ ኢትዮጵያም ሆነ በዓማራ ማህበረሰብ ላይ የሚነሱ መሰረታዊ የማንነት እና ሉዓላዊነት ጥያቄ ዕዉንታቸዉ በራሱ በህዝብ ሲረጋገጥ እንጂ በጥላቻ እና በእኔ ብቻ ብሎ ማድበስበስ ፣ የህዝብን እና የአገርን የረጂም ዓመታት መከራ ማሳነስ ለኢትዮጵያዉያን ቀርቶ ለጠላት የትም ያህል ርቀት ቢሄድ ዉሸት እንጂ ዕዉነት አይሆንም ( ሀሰት +ክህደት =ሐሰት ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  “እንፈላለጋለን!” (ፀጋዝአብ ለምለም ተስፋይ)

“የኢትዮጵያም የዘመናት ችግር በማድበስበስ እና በማለባበስ(በመቅለስለስ) ሳይሆን ከዕዉነት እና ተግባር ጫፍ በመድረስ ብቻ ነዉ ፡፡”

ካለፈ ጥፋት ሆነ ስህተት አለመማር ፣ አለመመከር ፣ አለመሞከር  የንሰኃ ዕንቅፋት ፤ የፖለቲካ ክፋት ምልክት ” ለህዝብ እና ለአገር አለመኖር” ነዉ ፡፡”

 

“አንድነት ኃይል ነዉ  ”  !

 

አለን !

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share