August 16, 2023
6 mins read

የጂብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል ፤ የሟች ችኩል ገዳይን ይከተላል !

አህያ ጂብ ሲያይ ከመራቅ ይልቅ ይጠጋል ፡፡ እንዲዉም አንድ የጂብ እና የአህያ ንግግር እና ስምነት በቀልድ መልክ ይነገራል ፡፡ ቀልድ ደግሞ ነባራዊ ህይወትን በስማ በለዉ የሚገለፅበት አዝናኝ፣አስተማሪ እና ታሪካዊ ይዘት አለዉ ፡፡
በአንድ ወቅት ጂብ እና አህያ በአንድ ወንዝ ከላይ እና ታች ሆነዉ በቅርብ ርቀት ዉሀ ሲጠጡ ጂብ ሆይ ስበብ ሲፈልግ አህዮን የወንዙ ዉኃ ደፈረሰ ይላታል ፡፡
አህዮም እንኳን ታዝዛ እንዲሁ ጂብ ስታይ ራሷን ከማራቅ እና ከመጠበቅ ይልቅ እየተንቀጠቀጠቀጠች መቅረብ ተፈጥዊ ግዴታ እንደሆነ ተለማድዋለች ፡፡
እናም መብላት ስልጣኑ እና መብቱ የሖነዉ ጂቦ ትዕዛዝ አህዮ ሆይ ነይ ከፍ በይ ሲላት መጠጋት እነ መበላት ዕጣ ፋንታዋ አድረጋ የጠለማመች አህዮ መሄዷ አይቀሬ መሆኑን ሆዷ እያወቀ መምጣቱንስ ልምጣ ግን …….. ብላ ጠየቀች ይባላል ፡፡

ወደ እኛ አገር ነባር ሁኔታ ሲመለስ ኢትዮጵያ እና ህዝቧ ለራሳቸዉ እና ለአገራቸዉ ሉዓላዊ የማይገሰስ ተፈጥሯዊ መብታቸዉ ሆኖ ሳለ ካለፉት ሶስት አሰርተ ዓመታት ጀምሮ ዕጣ ፋንታቸዉ ን ሁሉ ለኢህአዴግ ሰጥዉ ዕረፍት አልባ ዕንቅልፍ ተኝተዉ በሁንም በህልምም ህይወትም ሞትም እንዳል ክ ብለዉ ሁሉን ክፉ ነገር አስተናግደዋል ፡፡
ኢህአዴግም የመብት ፣ የይገባኛል ፣የነፃነት ……ጥያቄ ለሚየነሳ ሁሉ አንዴ የተልባ ወጥ አንዴ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ ብትነሱ አትራመዱ ፤ በትናገሩ አትኖሩ በማለት እንደ አባጂቦ ገርፎ ጯሂ፤ አደፍርሶ አደፍራሽ ፤ በድሎ ተበዳይ …እያለ ህዝብ የሁሉ ነገር ተሸካሚ አህያ አድርጎት የሁሉ ነገር ባለቤት ሲሆን ፤የሁሉ ነገር ተጠያቂ ደግሞ ህዝብ ከሆነ ብዙ ዓመታት (1983 ዓ.ም ጀምሮ) ተቆጥረዋል ፡፡

ሆኖም ኢህአዴግ ለዘመናት በኢትዮጵያ እና አማራ ህዝብ ጀርባ ሆኖ እየማለ በተቃራኒዉ በጥላቻ እና በዕብሪት ለዓማታት አገር እና ኅዝብ ዕየገደለ የሰላሳ ዓመታት የተጫነበት የመከራ ቋጥኝ እና ባላሳለሰ ሁኔታ ዕየደረሰበት ያለዉ ዕንግልት፣ ስደት ፣ ዉርደት እና ሞት መነሻ እና መድረሻ የዓማራ ህዝብ ሆኖ ተከሳሽ እና ተወቃሽ በማድረግ ብዙ የመከራ እና ስቃይ እንዲሳልፍ ተደርጓል፡፡

ኢትዮጵያ የእስር እና የአሳር ምድር ሆና ለሁሉም ዕንድትበቃ ሆና የተረከብናት ታላቅ እና ሰፊ አገር ሆና ሳለ በእኛ አንሶ በማነስ አሳንሰታናል፤ ኢትዮጵያ የዕስር እና አሳር ምድር ሆና በደም እና ዕንባ ጎርፍ ተሸርሽራ እንድትጠብ ሆናለች ፡፡

ዛሬም ለምንገኝበት የጦርነት አዙሪት ለመግባታችን በድንገት የሆነ ሳይሆን ጦር አምጣ እያሉ ምድር ለሚደበድቡት አዲስ አይደለም ፡፡ አሁን አሁን የሚባለዉ በዕዉነት ቀድሞ ከታሰበዉ ዉጭ ግጭት፣ ህግ ማስከበር ….ሲባል የሚያሳስበን ለሁሉም ኢትዮጵያዉያን እና ኢትዮጵያ አንድነት የማይበጂ ተጨፈኑ ለማኛችሁ የሚለዉ አስተሳሰብ እና ማሳበብ የሚረባን አይደለም ፡፡

መንስኤ ሳይታወቅ የበሽታ መድኃኒት መገመት እንደማይቻል ሁሉ በኢትዮጵያችን ሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል መንስዔዉ የዓማራ ኅዝብ የትህነግን ወረራ ለመቀልበስ ስንቅ ያለዉ ሰንቅ ፣ትጥቅ ያለዉ ትጥቅ ይዞ እንዲዘምት ሲሆን ተጠይቆ እንጂ ታጥቆ አልነበረም ፡፡

በዚህም ህዝቡ በላቡ ያልነበረዉ በደም ዋጋ ከጠላት የታጠቀዉ ጠብ መንጃ “ጥቁር ጠበንጃ “ለማስወረድ የተለያየ ጥረት ተደርጎ ያልተቀበልነዉን አንሰጥም መባሉ ኢህዴግ በኃይል በማንበርከክ ለማስመለስ የተጀመረዉ የጥቁር ታሪክ ሙጃ ዘር ነበር ፡፡

የዓማራ ህዝብም ንብረታችሁን አምጡ ፤ ትጥቅ ፍቱ ማለቱ ይሁን ግን ምን ታስቦ ነዉ የሚለዉን ህዝብ ለምን ቢልም ሰሚ ያጣ ህዝብ ከመሞት መሰንበት ብሎ መከላከል ማድረጉ በምን ዋጋ እና ስሌት በደል ላይ በደል እንዲጫንበት ስለምን ይፈለጋል ?

“አንድነት ኃይል ነዉ !”

Allen

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
Go toTop