August 16, 2023
3 mins read

የፖለቲካ ሥልጣን ቢኖረኝ (በቀለ ገሠሠ)

በህይወቴ የፖለቲካ ሥልጣን ተመኝቼ አላውቅም። ፍላጎቴ እግዚአብሔር ይመስገን ባገኘሁት ከፍተኛ ትምህርትና ዓለማቀፍ የሥራ ልምዴ ወገኔን ማገልገል ብቻ ነበር።
ዛሬ ግን በተለይ በአማራው ወገኖቻችን ላይ ያነጣጠረው የጅምላ ጭፍጨፋና መፈናቀል ስመለከት አንጀቴ ያራል፣ ልቤ ይቆስላል፣ በህይወት መሰንበቴን ያስጠላኛል። አማራ የትግሬ፣ የኦሮሞ፣ ወዘተ ህዝብ ጠላት ሆኖ አያውቅም። ያገኘውን ልክ ጥቅም አልነበረም። እንደ ሁሉም ዜጋ ጥሮ ግሮ ህይወትን አቸንፎ የኖረ ደግ ህዝብ ነው። ስለዚህ በምናብም ሆነ በተግባር ጭቁን ህዝባችንን ለመታደግና ውድ አገራችንን ከጥፋት ለማዳን ሥልጣን ቢኖረን የምንፈጽማቸው ተግባራት የሚከተሉትን ያጠቃልላሉ፣
ሀ) ሁሉ አቀፍ የሽግግር መንግሥት አናቋቁማለን፣ ዘረኝነትን፣  የወገን ጭፍጨፋ፣ መፈናቀልና ሰቆቃ እናቆማለን፣  በዘር ማጥፋት ወንጀል የሚሳተፉት በነፃ ፍርድ ቤት  እንዲጠየቁ እናመቻቻለን።  በመቀጠል የተለያዩ ፓርቲዎች ነፃና ፍትሐዊ በሆነ መልክ ተወዳድረው መንግሥት እንዲመሠርቱ እናመቻቻለን፣
ለ) ሕገመንግሥቱ እንዲለወጥ አናደርጋለን፣
ሐ) የተረጩት የውሸት ትርክቶች እንዲታረሙ አናደርጋለን፣
መ) ዕርቀ ሰላም እናወርዳለን፣ የማንም ዜጋ ህይወት በግፍ እንዳይጥፋ እንከላከላለን፣
ሠ) የተፈናቀሉትን ወገኖች መልሰን አነናቋቁማለን፣
ረ) ግፍ ለደረሰባቸው ወገኖች ካሣ እንከፍላለን፣
ሰ) ለገበሬው ሰላምና  ድጋፍ አናመቻቻለን፣
ሸ) ነጋዴው በነፃ ተዟዙሮ መነገድ መቻሉን አናረጋግጣለን፣
ቀ) ወጣቶች ጥሩ ትምህርት እንዲያገኙ እናመቻቻለን፣ እንደግፋለን፣
በ) የሀገር ኢኮኖሚ እንዲያድግ የሚገባውን ሁሉ ድጋፍ  እንሰጣለን፣ ለምሣሌ ጠፍ መሬቶች ማልማት፣ ወንዞቻችንን መገደብ፣ የመስኖ እርሻዎች ማስፋፋት ፣ የአካባቢ አየር ብክለት መከላከል፣ ወዘተ ።
ውድ ወገኖች፣
እላይ እንደጠቀስኩት ጥረቴ የመንግሥት ስልጣን ፍላጎት አይደለም፣ ሆኖም አያውቅም። ዋናው ምኞቴን ለመግለጽ ስለሆነ ተረድታችሁ ለዘላቂ ሰላምና ዕድገት  የሚቻላችሁን ጥረት እንድታደርጉ በትህትና እጠይቃለሁ፣
ቸሩ አምላካችን ይጨመርበት።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

Go toTop