August 9, 2023
9 mins read

ፋኖ ሆይ፤ ውሻን በርግጫ መምታት እንካ ሥጋ ማለት ነው

Abiy Ahmed 3 1 1
#image_title

ጭራቅ አሕመድ ቆርጦ የተነሳው አማራን በልቶ ለመጨረስ ነው፡፡  አማራን በልቶ ቢጨርስ ደግሞ ምዕራባውያን ጌቶቹ ዝንቡን እሽ እንደማይሉት በግልጽ አሳውቀውታል፡፡  ለነጻነቱ ቀናዒ የሆነው፣ በማንነቱ የሚኮራው፣ ነጭን ከመጤፍ የማይቆጥረው የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ቢጠፋ፣ ያፍሪካ አንድነት ምልክት የሆነችው አዲሳባ ደግሞ አማራና አማራዊነት ሙሉ በሙሉ የተወገደባት፣ አፍርቃዊ አፓርታይድ የነገስባት፣ የአፍሪቃውያን በጎጥ የመከፋፈል ዋና ምልክት የሆነች፣ አፍሪቃውያንን አንገት የምታስደፋ፣ አሳፋሪ ኦነጋዊ ከተማ ብትሆን ምዕራባውያን ደስታውን አይችሉትም፡፡

ስለዚህም የምዕራባውያን ሙሉ ድጋፍ ያለውን፣ በጭራቅ አሕመድ የሚመራውን፣ የኦነግንና የወያኔን ፀራማራ ጣምራ ጦር  ፊት ለፊት መግጠም፣ የእሳት ራት ከመሆን ውጭ ፋይዳ የሌለው አጉል ጀብደኝነት ነው፡፡  የጭራቅ አሕመድ ዓላማ ደግሞ ዘመናዊ መሣርያ እስካፍንጫው የታጠቀውን የኦንግንና የወያኔን ጣምራ ጦር ይዞ፣ የነፍስ ወከፍ መሣርያ ካነገበው ከፋኖ ጋር ፊት ለፊት ለመግጠምና፣ ፋኖን በዚያውም መላውን የአማራን ሕዝብ በመድፍ እየመደፈ፣ በንቦቴ (drone) እየነቦተ የዶግ ዐመድ ለማድረግ ነው፡፡

በሰው ኃይል በመሣርያና ባቅርቦት (logistics) ብዙ እጥፍ የሚበልጥህን ጠላት አንተ በመረጥከው መቸት (መቸ እና የት) እንጅ እሱ በመረጠው መቸት አትገጥመውም፡፡  ይህ ማለት ደግሞ ሌላ ምንም ማለት ሳይሆን የደፈጣ ውጊያ ማለት ነው፡፡  ስለዚህም ያማራ ሕዝባዊ ግንባር (አሕግ) በጭራቅ አሕመድ ከሚመራው የኦነግና የወያኔ ጣምራ ጦር ጋር መፋለም ያለበት በደፈጣና በደፈጣ ብቻ ነው፡፡  ለዚህ የደፈጣ ውጊያ ግብአት ይሆነው ደግሞ አያቶቹ ባርበኝነት ዘመን ይጠቀሙባቸው የነበሩትን ዘዴወች ከማስታወስ በተጨማሪ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አሥሩን የሰንሹን (Sun Tzu) የማጥቃትና የመከላከል መርሖች ልብ ሊል ይገባል።

  1. ድልማድረግ በራስ ሁኔታ፣ ድል መደረግ ደግሞ በጠላት ሁኔታ ይወሰናል፡፡  ስለዚህም ጠቢብ የጦር አዛዥ በራሱ በኩል ሊያከናውናቸው የሚገባውን ሁሉ በጥንቃቄ አከናውኖ አመችውን ጊዜ ነቅቶና ተግቶ በትእግስት ይጠባበቃል፡፡  ታላቆቹ ጦረኞች ትዕግስትና ጊዜ ናቸው፡፡  ጊዜ የሰጠው ቅል ዲንጋ ይሰብራል፡፡  
  2. ኢተረችነትበመከላከል ችሎታ፣ ረችነት ደግሞ በማጥቃት ችሎታ ይወሰናል፡፡  ጠላት ሲበረታ ተከላከል፣ ሲደክም አጥቃ፡፡
  3. ጠቢብየጦር አዛዥ የሚያጠቃው መጠቃት ያለበትን እንጅ ለማጥቃት ሲል ብቻ አያጠቃም፡፡
  4. ጠቢብየጦር አዛዥ የሚከላከለው መካላከል ያለበትን እንጅ ለመከላከል ሲል ብቻ አይከላከልም፡፡
  5. ጠቢብየጦር አዛዥ ሲያጠቃ የሚከላከል፣ ሲከላከል የሚያጠቃ ያስመስላል፡፡
  6. ጠቢብየጦር አዛዥ ሲያስፈልግ እንደ እሳተ ገሞራ ከምድር ይፈነዳል፣ ሲያስፈልግ ደግሞ እንደ መብረቅ ከሰማይ ይበርቃል፡፡
  7. ጠቢብየጦር አዛዥ ሲያስፈልግ እንደ ንፋስ ይፈጥናል፣ ሲያስፈልግ ደግሞ እንደ ተራራ ይቆማል፡፡
  8. ጠላትህ ሲጠናከር ሽሸው፣ ሲዳከም አጥቃው፡፡  በግንባርህ ሲመጣብህ በጀርባው፣ በቀኝህ ሲመጣብህ በግራው እየተዟዟርክ አዋክበው፡፡  አወይ አተኳኮስ ወይ ደፋር መሆን፣ ሲሄድ መቀለቻ ሲዞር ግንባሩን፡፡ጠላትህ ሲረጋጋ ባሉባልታ አሸብረው፣ ሲያርፍ በትንኮሳ አዋክበው፡፡  ካጋም እንተጠጋ ቁልቋል ረፍት እየነሳህ፣ እዚህም እዚያም እየበሳሳህ፣ ዘላለም አስለቅሰው፡፡
  9. ጠላትህትይዝብኛለህ ብሎ የማያስበውን፣ ከያዝክበት ደግሞ ባስቸኳይ ሊያስለቅቅህ የግድ የሚያስፈልገውን ቦታ ሳይስበው በድንገት ያዝበትና ሥራህን ቶሎ ሠራርተህ ሳያስበው በድንገት በመውጣት ትሄድበታለህ ብሎ በማያስበው መንገድ ትሄድበታለህ ብሎ ወደማይገምተው ቦታ በፍጥነት ሂድ፡፡
  10. እንደመብረቅ በድንገት በርቀህ እንደ አውሎ ንፋስ በድንገት ንፈስ ፡፡  መብረቅ ድንገት ይበርቃል እንጅ ከየት በኩል እንደሚበርቅ አይታወቅም፡፡  አውሎ ንፋስ በድንገት ነፍሶ የሚጠራርገውን ይጠራርጋል እንጅ ከወዴት እንደሚነፍስ አስቀድሞ አይታወቅም፡፡  ሲበርቅ ቢጨፍኑ ከመወጋት አይድኑ፡፡
  11. ጠንካራ ስትሆን ደካማ፣ ደካማ ስትሆን ጠንካራ፣ ሩቅ ስትሆን ቅርብ፣ ቅርብ ስትሆን ሩቅ፣ ዝግጁ ስትሆን አልዝግጁ፣ አልዝግጁ ስትሆን ዝግጁ መስለህ ለጠላትህ ታይ፡፡  ጠላትህን እንቁ አሳይተህ እነቀው፡፡
  12. ማጥቃትህስኬታማ እንደሚሆን እርግጠኛ ልትሆን የምትችለው ጠላትህ የማይከላከለውን ስታጠቃ ብቻ ነው፡፡  መከላከልህ ስኬታማ እንደሚሆን እርግጠኛ መሆን የምትችለው ጠላትህ የማያጠቃውን ስትከላከል ብቻ ነው፡፡  በማጥቃት የተካነውን መከላከል፣ በመከላከል የተካነውን ማጥቃት ትርፉ ትልቅ ሽንፈት ነው፡፡

 

ያማራ ሕዝብ ሕልውናውን ማስጠበቅ የሚችለው የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግሥት ገርስሶ፣ የሚገባውን ሥልጣን ይዞ፣ ዘላለማዊ ጠላቶቹን ወያኔና ኦነግን ለዘላለም ሲያስወግድ ብቻና ብቻ ነው።  ከሕልውና ጠላት ጋር ያልሞት ባይ ተጋዳይ የሞት ሽረት ትግል አድርጎ ወይ መግደል ወይ መሞት እንጅ መደራደር፣ መሽማገል የሚባል ነገር የለም።     

 

መስፍን አረጋ

[email protected]

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

January 20, 2025 ጠገናው ጎሹ የአቤ ጎበኛው አልወለድም ለወገኖቹ መብት መከበር ሲል ባደረገው ጥረት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ ይሙት በቃ በፈረዱበት ጊዜ በምላሳቸው መልካም  አድርጎ ስለ መገኘት እያወሩ በድርጊት ግን ተቃራኔውን የሚያደርጉ ሁሉ

ወዮ ለመከረኛው የአገሬ ህዝብ እንጅ  ታየማ ታየ ነው

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

Go toTop