August 7, 2023
9 mins read

ዉኃን ምን አጮኸዉ ቢሉ ድንጋይ አሉ !

 

ሁላችንም ሠዉ ሆነን የጠፈጠርን ኢትዮጵያዉያን በራሳችን አገር እና ወገን ለዕድሜ ልክ  አሳር እና እስር የዳረገን ምን እና ማን እንደሆነ እንኳን ማገናዘብ አጥቶን ኢትዮጵያ አገራችን ከረጂም ዓመታት ጀምሮ ለብዙኃን ኢትዮጵያ ጣራ አልቦ አሰር ቤትሆና ቆይታለች ፡፡

ይህም በጥቂቶች እና በጥላቻ በሰከሩ ስግብግቦች ማን አለብኝነት እና ንቀት የቀንድ አዉጣ ፖለቲካ ከዕዉነት መለየታቸዉን መስማት በማይፈልጉት የተወለደ የአገር እና ህዝብ መከራ ነዉ ፡፡

ኢህአዴግ ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የፖለቲካ ስርዓትን በመጠበቅ የጭቆና እና አድሎ ስርዓትን በማዘርጋት እና በማጥብቅ በዜጎች ላይ ወዳጂ እና ጠላት አድርጎ የመፈረጂ አባዜ ከራሱ ዉጭ አገሪቷ ችግር እና የዜጎች የመከራ ዘመን መራዘም እንደ ጊዜ መግዣ በማድረግ የሕዝቡን ዕሮሮ የቁራ ጩኸት እያለ ራሱን በራሱ ቁራ አድርጎ ይኸዉ አስከዛሬ ቀጥሏል፡፡

ዛሬ ላይ ስለ ሠላም አስፈላጊነት እና ጦርነት ክፋት ኢህአዴግ ሲናገር መስማት የተለመደ ቢሆንም ሌሎች ስለ ሠላም እና ጦርነት እንናገር የሚሉ ከየትኛዉም ቡድን፣ተቋም ሆነ ክፍል ሲናገሩ መስማት ግን እጂግ ያሳዝናል ፡፡

ለዚህም ኢህአዴግ የቀድሞዉን መንግስት ህዝባዊ መዋቅር በኢትዮጵያ ጠል አካላት ትብብር አፍርሶ ሽግግር መንግስት በሚል ሽግግረ -ኢህአዴግ ሲመሰርት የኢትዮጵያን ምሁራን ወክለዉ ከተገኙት ፕ/ር አስራት ወ/የስ እና መኮንን ቢሻዉ በቀር ያኔም ሆነ አሁን ያሉ እና የነበሩት እንደሚያወቁት  ትምክህተኛ ምሁር ተብለዋል፡፡

ይህም የሽግግር መንግስቱን ሲመሩ የነበሩት ሟች ያሉትን ይዞ ከላይ የተጠቀሱትና ሥራቸዉ ህያዉ ሆኖ የሚኖሩት ኢትዮጵያዉያን አገር ለማፍረስ ለመስማማት እና ሽግግር መንግስት ለመመስረት በለመስማማታቸዉ መድረክ ረግጠዉ እንደ ወጡ ስልጣንም ፣ጥቅምም ሆነ መኖር ሳያጓጓቸዉ ወደ ኋላ አለማለታቸዉን ታሪክ እና ትዉልድ አይዘነጋዉም ፡፡

እዚህ ላይ ሁላችንም መረዳት ያለብን ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ፣አብሮነት ፣ ሠላም እና የጦርነት አስከፊነት ለመናገር የህሊናም ሆነ የህግ ልዕልና ያልነበራቸዉ ከዚያ አስካሁን ለአገር እና ለህዝብ ሳይሆን ለቡድን እና ለግል ጥቅም የፖለቲካ ስርዓት አምላኪ እና ተላላኪ ድርጂቶች፣ ተቋማት እና ግለሰቦች ዝም ብለዉ አገሪቷ እና ህዝቦች ከዚያ የሽግግር ጊዜ የኢትዮጵያ የጥልመት ዘመናት መባቻ ጀምሮ አስካሁን ያጨበጨቡ በአቋማቸዉ ቢቆሙ ይሻላል፡፡ በምንም መንገድ የሠላም እና የአንድነት ሀዋርያ ሊሆኑ አይችሉም ፡፡

ለዘመናት ዜጎች በተለይም ብዙኃኑ የኢትዮጵያ ህዝብ አካል የሆነዉ የዓማራ ህዝብ በትዉልድ አገሩ ለሶስት አሰርተ ዓመታት በስደት ፣በሞት እና በዘመናዊ ባርነት የበይ ተመልካች ሲሆን አንድም ዓለማዊ ሆነ ኃይማኖታዊ ድርጂት ድርጊቲቱን በስሙ ጠርቶ መሞገት ቀርቶ ጉዳዩን ፍትኃዊ እና ተፈጥሯዊ አድርጎታል፡፡

ሠዉ በሰዉነቱ እና በማንነቱ ሲሞት ሠዉ ሞተ ተብሎ ሳይሆን …….ብሄረሰብ ሞተ ከማለት ዉጭ አንድም በህዝብ እና በአገር ሀብት የሚንቀሳቀስ የመገኛኛ ብዙኃን አስከዚህ ሠኣት ለህዝብ ጆሮ አድርሶ አያዉቅም ፡፡

ሌላዉ ቀርቶ ለሠዉ ልጆች ሠባዊ መብት መከበር እንሰራለን የሚሉ እና ገለልተኛ ተቋማት እንኳ ከዚኅ በኋላ ተመጣጣኝ ግድያ፣መፈናቀል….ይሁን ሲሉ እንጂ ይህ ጉዳይ የዚህ ተጠያቂነት ነዉ ብለዉ ከዳር ሲደርሱ አይታወቅም ፡፡ ለአስረጂነት በጥቂቱ የትናንቱን የ17 ልጆች ፣ የመንገድ ላይ ተፍኖ የቀሩት ዜጎች ምንነት እና ደህንነት የት ደረሰ የሚል ካለ ህዝብ ፊት ይቁም ፡፡

ዜጎች ስለ ሠባዊ ክብራቸዉ ፣ ስለ አገራቸዉ ፣ ስለ ህዝባቸዉ ፣ ስለ ማንነታቸዉ፣ ስለ ዕምነታቸዉ …..ለዓመታት ሲሳደዱ ፣ ሲዋረዱ ፣ሲታረዱ ፣ሲሞቱ……ከህዝብ እና ከአገር መከራ ፊት የቆመ አይደለም ለምን ያለ የማህበረሰብ ፣የኃይማኖት እና የፖለቲካ ድርጂት መሰረታቸዉ አገር እና ህዝብ ሆኖ በምን ቸገረኝነት እና በአድር ባይነት ማየታቸዉ ዛሬ ለምንገኝበት ዝቅጠት ምክነያት ከመሆን በላይ እንኳን የመከራ ቀንበር ተሸካሚ ህዝብ ሰይጣን ዕምነቱን እንደሚነሳቸዉ አይጠረጠርም ፡፡ ለምን ለሚል ለራሱ አገር እና ሠዉ የማይሆን ሠባዊ ፍጡር ለአጋንት ሊሆን አይችልም ፡፡

በድምሩ ዛሬ ስለ ሠላም ፣ ዕርቅ ፣ጦርነት የሚያወሩ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያዉቃቸዉ እና የሰለቻቸዉ መሆኑን ዕልፍ አዕላፍ ማስረጃዎች መኖራቸዉ መጥቀስ ሳያስፈልግ በዚህች አገር ላይ ደካሞችም ብዙኃን እና አገሬ ብለዉ የሚኖሩ እና የሚጮሁ ስለሆነ ጩኸታቸዉን መስማት እና ራሳቸዉን ለይቅርታ እና ለተጠያቂነት ማዘጋጀት አለባቸዉ ፡፡ እነማን ነበሩ በሰላማዊ መንገድ ለአገራቸዉ እና ለህዝባቸዉ ሲሉ ሲታገሉ ሲያታግሉ ዕድሜ ዘመናቸዉን ሲሳደዱ ፣ሲዋረዱ ፣ሲታሰሩ ሲፈቱ ኖረዉ የሞቱ ፤የተንገላቱ …..? ይህን ለትዉልድ እና ለታሪክ መተዉ ነዉ ፡፡

ሁላችንም ባለችን አንዲት አገር ተከባብረን እና ተብረን ለመኖር ብቸኛዉ እና ወቅታዊ መድኃኒት ዕዉነት እና ዕዉነትን ለመናገር እና ለመተግበር ድፈረት እንጂ ስብከት እና ብልጣብልጥነት የቀንድ አዉጣ ፖለቲካ ነዉ እና በቃን ስሙን ፤ተቀበሉን ብሎ ፈሊጥ ለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዉያን አይጠቅምም፡፡

ሁላችንም  ፍርኃትን፣አድር ባይነት ፣ክፋትን ፣ምቀኝነትን እና ስግብግብነትን  በድፍረት በቃን አለማለታችን  የመከራ ጊዜን ከማራዘም ዉጭ የአገሪቷንም ሆነ የህዝቧን የመከራ ቀንበር ያጠነክረዋል እንጂ አይሰብረዉም ፡፡

የኃይማኖት ተቋማት ታላቆችም ሠወችንም ሆነ ጥቅም ማጣትን በመፍራት ሆነ በማዳላት ዝምታን አስካሁን መምረጣቸዉ መቆም እና ለህዝብ እና ለአገር በሚበጂ ጉዳይ ላይ ያገባናል የሚሉበት ጊዜ አሁን ነዉ፡፡

አንድነት ኃይል ነዉ !

 

Allen!

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ “ ሰው የሰነፎችን ዜማ ከሚሰማ ይልቅ የጠቢባንን ተግሣጽ መስማት ይሻለዋል። ”   — መክብብ 7፥5 እስቲ ቆም ብለን በማሰብ  ራሳችንን እንፈትሽ ።  እንደ ሰው ፣ የምንጓዝበት መንገድ ትክክል ነውን ? ከቶስ ሰው መሆናችንን እናምናለንን ? እያንዳንዳችን ሰው መሆናችንን እስካላመንን ጊዜ ድረስ ጥላቻችን እየገዘፈ

 ለሀገር ክብርና ብልፅግና ብለን ፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ ህሊናችንን ከጥላቻ እናፅዳ

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
Go toTop