ሱዳን ውስጥ በጦርነት መካከል የሚገኙትን ወገኖችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የመሚደረግ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም

በአሁኑ ወቅት ጎረቤት ሀገር ሱዳን በከፋ ጦርነት ውስጥ በመሆኗ ምክንያት በዚያ ለረጅም ዘመናት በስደት የሚኖሩት ወገኖቻችን ለከፋ አደጋና ችግር ተጋልጠው ይገኛሉ። እስከ አሁን ድረስ ወገኖቻችንን ከዚህ አሰቃቂ አደጋ የሚታደጋቸውና ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ የሚረዳቸው ከኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ ከሌላ ዓለም አቀፍ ተቋም በኩል ድጋፍ አልተገኘም።

ስለሆነም በውጭ ሀገር የምንኖር ኢትዮጵያውያን በዚህ የከፋ አደጋ ውስጥ የሚገኙትን ወገኖቻችን የመታደግ ግዴታና ሃላፊነት አለብን ብለን በፅኑ እናምናለን።

በአሁኑ ሰአት ልሳነ ግፉዓን ድርጅት ከጥቂት ለጋሾች ባገኘው መጠነኛ የገንዘብ ድጋፍ 300 ወገኖቻችንን ማውጣት የቻለ ሲሆን በቀጣይም አቅም በፈቀደ መጠን ቀሪ ወገኖቻችንን ለመታደግ ጥረት በመማድረግ ላይ ይገኛል።

ስለሆነም ቅዳሜ June 17, 12:00 PM (Noon) EST ባዘጋጀነው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ወገናዊ ድጋፋችሁን በማድረግ የወገንዎን ውድ ህይወት እንዲታደጉ በአክብሮት ጠርተነዎታል።

ተጋባዥ እንግዶቻችን

  1. አቶ አሸተ ደምለው – የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
  2. ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ – የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ም/አስተዳዳሪና የሰላምና ደህንነት ኃላፊ

ወደ ስብሰባው ለመግባት የሚከተለውን የዙም ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ።

Join Zoom Meeting፡ https://us02web.zoom.us/j/86957160144

                Meeting ID: 869 5716 0144

One tap mobile፡

+13017158592,,86957160144# US (Washington DC)

+13052241968,,86957160144# US

#image_title

ተጨማሪ ያንብቡ:  "የአሸናፊነታችንን አይቀሬነት ቅርብ የሚያደርገው ውስጣዊ አንድነታችን እና የማይናወጥ ጽናታችን ነው!" አቶ ግዛቸው ሙሉነህ

1 Comment

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share